አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የቅጣት ማክበጃ ምክንያት (aggravating circumstance)
--------------------
ሰላም ጤና ይስጥልን ውድ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ የፌስቡክ ገጽ ተከታታዮቻችን እንዴት ናችሁ ለዛሬ አንድ ሰው በማወቅም ይሁን ባለማዎቅ በሰራው ወንጀል ፍርድ ቤት ቀርቦ በሚከራከርበት ሰዓት ዐቃቤ ሕግ የቅጣት ማክበጃ ምክኒያቶችን አቀረበ ሲባል እንሰማለን ለመሆኑ የቅጣት ማክበጃ ምክኒያቶች ምንድን ናቸው?
የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች በሁለት ይከፈላሉ እነኚህም ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት እና ልዩ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች ናቸው፡፡ ለዛሬ ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶችን በተመለከተ ያዘጋጀንላችሁ አጭር ገለጻ እነሆ….ከወዲሁ መልካም ንባብ ተመኝን፡-
ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች የምንላቸው በወንጀል ህጋችን በአንቀጽ 84 ስር የተዘረዘሩት ናቸው፡፡
የወንጀል ህጋችን አንቀጽ 84(1) ከፊደል ተራ ሀ-ሠን እንደሚከተለው ተመልክተናቸዋል፡፡

ሀ/ ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በከሀዲነት ወይም በወስላታነት ወይም በወራዳነት ወይም መጥፎ አመልን በሚያሳይ ምቀኝነት፣ጥላቻ፣ ስግብግብነት፣ መጥፎ ነገርን ለመስራት ወይም ሰውን ለመጉዳት ፍጹም ፍቃደኛ በመሆን ወይም በተለየ ክፋት ወይም በጨካኝነት እንደሆነ ይላል
ወንጀል ታስቦ ወይም በቸልተኛነት ሊፈጸም ይችላል፡፡ከላይ የምንመለከተው ወንጀልን አስበው እና ሆነ ብለው የሚፈጽሙ ሰዎች በፈጸሙት ወንጀል ማግኘት ካሰቡት ያልተገባ ብልጽግና በተጨማሪ ወንጀሉን ለማድረግ ካነሳሳቸው ወይም ምክንያት ከሆናቸው ነጥብ አንጻር የወንጀል አድራጊውን አደገኛነት የሚያመላክት እንደሆነ ፍ/ቤቶች ከላይ በተዘረዘሩት የማክበጃ ምክንያቶች መሰረት ቅጣትን ሊያከብዱ ይችላሉ፡፡በዚህ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ስር የተለያዩ ምክንያቶች የተዘረዘሩ ሲሆን በዚህ ድንጋጌ መሰረት ቅጣትን ለማክበድ ከመካከላቸው የአንዱ መሟላት በቂ ነው፡፡ይህም ማለት ተከሳሽ ወንጀሉን ያደረገው በከሃዲነት ወይም በወስላታነት ወይም በምቀኝነት ወይም በጥላቻ ከሆነ ከነዚህ መካከል አንዱ በወንጀል አድራጊው ወንጀል አደራረግ ውስጥ ከተገኘ በቂ ነው ማለት ነው፡፡እምነቱን በጣለበት ወዳጁ ላይ፣ በተበዳዩ ላይ ባለው የግል ጥላቻ ወይም በምቀኝነት(ጥቅም ለማግኘት ብቻ ሳይሆን አንድ ሰው ጥቅም እንዳያገኝ በማሰብ) ወዘተ ወንጀልን ማድረግ በአብነት ሊነሱ ይችላሉ፡፡

ለ/ ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ስልጣኑን፣ ተግባሩን ወይም የተጣለበትን እምነት ወይም ሀላፊነት ያለአግባብ በመገልገል እንደሆነ
ባለስልጣናት ወይም የመንግስትን ስራ ለመስራት ወይም ለመምራት ስልጣን ወይም እምነት የተጣለበት ሰው ስራውን በታማኝነት እና በቅንነት መፈጸም አለበት፡፡በተጨማሪም ይህንኑ ስልጣን ተገን በማድረግ ለራሱም ሆነ ለሌላው ጥቅም ለማስገኘት ወይም በሌላ ሰው ጥቅም ወይም መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ አንድን ወንጀል ከፈጸመ ቅጣት ሊከብድበት እንደሚገባ የወንጀል ህጉ ይደነግጋል፡፡ይህ የሆነበት ምክንያት ሰዎች ስራ ፈጻሚዎች የሚነግሯቸውን ወይም እንዲያደርጉ የሚያዟቸውን ነገር ሁሉ ስለሚቀበሉ እና ትዕዛዙን መቀበል ካልቻሉ ደግሞ የሚፈልገውን አገልግሎት ላናገኝ እንችላለን ከሚል የአማራጭ ማጣት ሀሳብ ምክንያት ለጉዳት ሊዳረጉ ይችላሉ፡፡ወንጀል አድራጊውም እምነት ሲጣልበት እምነቱን ወይም አደራውን በተገቢ መንገድ መወጣት አለበት፡፡

ስራውን የሠጠው ሰው እምነቱን የጣለበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ጠባቂ የሌለው በመሆኑ ስልጣኑን ወይም ሀላፊነቱን ለግል ጥቅሙ ለማዋል አይችልም፡፡ሰነዶችን በህገ-ወጥ መንገድ ለማይገባው ሰው የሰጠ የመዝገብ ቤት ወይም የአገልግሎት መስጫ ተቋም ሰራተኛ፣ ሌላውን ሰው ከህጋዊ ቅጣት ወይም ክፍያ ለማዳን ሲል ወንጀልን የፈጸመ የትራፊክ ፖሊስ ወይም መርማሪ ፖሊስ እና የመሳሰሉት በምሳሌነት ሊነሱ ይችላሉ፡፡በመሆኑም ከላይ የጠቀስነውን ሁኔታ ተሟልቶ ሲገኝ እንደ አንድ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ተወስዶ ቅጣትን በአንድ እርከን ከፍ ሊያደርግ የሚችል ምክንያት ነው፡፡

ሐ/ ወንጀለኛው በቀድሞ ጥፋተኛነቱ ወይም ወንጀልን ማድረግ ሙያ ወይም ልማድ አድርጎ መያዙ፣ ወይም የወንጀሉ አፈጻጸም ዘዴ፣ ጊዜ፣ ቦታና የአፈጻጸም አኳሀን፣ በተለይም በሌሊት ወይም በሽብር ወይም በሁከት ለአደጋ ሽፋን ወይም በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ ወንጀሉን በማድረግ የተለየ አደገኝነቱን አሳይቶ እንደሆነ
በዚህ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት ስር ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ እነኚህም፡-ወንጀልን ማድረግ ሙያው ወይም ልማዱ አድርጎ መያዝ ወንጀል አፈጻጸም ዘዴ፣ጊዜ፣ቦታ እና የአፈጻጸም አኳሀን ወንጀልን በጦር መሳርያ ወይም በሌላ አደገኛ መሳርያ መፈጸም ናቸው፡፡

ወንጀል ማድረግን ሙያው ወይም ልማድ አድርጎ መያዝ ማለት ተከሳሹ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት ተመሳሳይ ወይም የተለያዩ ወንጀሎችን በማድረግ የሚታወቅ እና ፍርድ ቤቶች የዚህን ሰው ጉዳይ ተመለክተው በሚሰጡት የመጨረሻ ውሳኔ ጥፋተኛ እያሉት ቅጣት የጣሉበት እና በማረሚያ ቤት ገብቶ የእስር ጊዜውን አጠናቆ ከወጣ በኋላም ወንጀልን ማድረግ ባለማቆም ወንጀልን ፈጽሞ የተገኘ እንደሆነ ነው፡፡የወንጀል ህጉ በአንቀጽ 67 ስር ስለደጋጋሚነት ያስቀመጠው ድንጋጌ የተካሳሹን የቀድሞ ባህሪ በቅጣት ማክበጃነት ልንጠቀም እንደምንችል ይደነግጋል፡:

ሌላው ወንጀል አድራጊው ወንጀሉን ለማድረግ አስቀድሞ በማሰብ ተጎጂው እራሱን እንዳይከላከል ወይም ሰው እንዳይደርስለት ወይም ማስረጃ እንዳይገኝበት ለየት ያለ ቦታ በመምረጥ፣ ወይም ሰው በማይንቀሳቀስበት በሌሊት ጨለማን ተገን በማድረግ የፈጸመው እንደሆነ ወይም የወንጀል አድራጊውን አደገኛነት በሚያሳይ ጨካኝነት ወይም በተለየ ስልት ወንጀልን ከፈጸመ፡፡ሌሊት የሚለው ሀረግ ከስንት ሰዓት ጀምሮ እንደሆነ አሻሚ ቢሆንም በተለምዶ ፍርድ ቤቶች ከሌሊቱ 6፡00-12፡00 ድረስ ያለውን የጊዜ ገደብ በሌሊትነት ወስደው ቅጣት ያከብዱበታል፡፡

ሶስተኛው ምክንያት ወንጀልን ለመፈጸም ወንጀል አድራጊው የተጠቀመባቸው መሳርያዎች ናቸው፡፡ ወንጀልን ለመፈጸም ጥቅም ላይ የሚውል መሳርያ የወንጀል አደራረግን ከባድነት ያሳያሉ፡፡በመሆኑም በእጅ ወይም በዱላ የውንብድና ወንጀልን የፈጸመ ሰው እና የስለት ወይም የጦር መሳርያዎችን ተጠቅሞ ይህንኑ ወንጀል የፈጸመ ሰው የወንጀል ማድረግ አደገኛነቱ እኩል ሊሆን አይችልም፡፡በመሆኑም ተከሳሽ ወንጀሉን ለመፈጸም የተጠቀመው መሳርያ በወንጀል ማቋቋሚያነት በልዩ ህጉ ካልተወሰደ በስተቀር በቅጣት ማክበጃ ምክንያትነት ይወሰዳል፡፡
መ/ ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው ወንጀል ለመፈጸም በተደረገ ስምምነት መሰረት ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን ወይም ወንጀል ለመፈጸም ከተቋቋመ ቡድን ጋር በመስማማት ወይም አባል በመሆን ይልቁንም እንደ ወንጀል ቡድን ሹም ወይም አደራጅ ወይም መሪ በመሆን እንደሆነ
በየትኛውም ምክንያታዊ አስተሳሰብ በአንድ ሰው መብት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች በተናጠል እና በቡድን ወይም ከአንድ በላይ በመሆን መፈጸሙ በተጎጂው ስነልቦና ላይ የሚያደርሱት ተጽዕኖ አንድ ሊሆን አይችልም፡፡በመሆኑም ወንጀልን ለመፈጸም ከሌላው ጋር ወይም ለዚሁ አላማ ከተደራጀ ቡድን ጋር በአባልነት በመስማማት ወንጀልን ማድረግ ቅጣትን ሊያከብድ የሚችል በቂ ምክንያት ነው፡፡
ሠ ወንጀለኛው ወንጀሉን ያደረገው በዕድሜው፣ በጤንነቱ፣ በኑሮው ወይም በስራው ሁኔታ ልዩ ጥበቃ በሚያሻው ሰው ላይ በተለይም ለመከላከል አቅም በሌለው፣ መንፈሰ ደካማ፣ በሽተኛ ወይም አካል ጉዳተኛ ፣ እስረኛ ወይም በቅርብ ዘመዱ ላይ ወይም የበላዩ ወይም የበታቹ በሆነ ሰው ላይ፣ በህግ በተቋቋመ ባለስልጣን ወይም የስራ ግዴታውን በማከናወን ላይ በሚገኝ በአንድ የህዝብ አገልጋይ በሆነ ሰራተኛ ላይ እንደሆነ ነው ሲል ይደነግጋል፡፡
ውድ አንባቢያን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁን አተታ በዚሁ አበቃን በቀጣይ ልዩ የቅጣት ማክበጃ ምክኒያቶች ምንድናቸው የሚለውን ይዘንላችሁ እንቀርባለን ሰላም፡፡
ጠ.አቃቤ ህግ
ሀሰተኛ ወይም አስጠቂ ምስክርነት መስጠት የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት
ሰላም ጤና ይስጥልን እንደምን አላችሁ የፅሁፋችን አንባቢዎች ዛሬ ደግሞ ስለ ሀሰተኛ /አስጠቂ/ ምስክር ምንነት ላይ ማብራሪያ ልንሰጣቹ ወደናል፡፡
አንድአንድ ሰዎች ያላግባብ ግለሰቦችን ለመጉዳት ወይም ለመጥቀም ሲሉ ሀሰተኛ /አስጠቂ/ ምስክርነቶችን ሲሰጡ ይስተዋላል፤ ታዲያ እኛም ሀሰተኛ ወይም አስጠቂ ምስክርን አስመልክቶ ያላችሁን ግንዛቤ ለማዳበር ጽሁፋችንን አዘጋጅተናል፡፡
በመሆኑም አስጠቂ ምስክር ሲባል ምን ማለት ነው? በሀሰት መመስከርስ ምን ያስቀጣል? የሚሉትን ለናንተ ለማስቃኘት ወደናል፡፡ ሀሰተኛ ወይም አስጠቂ ምስክር ማለት ከቃሉ ትርጓሜ ስንነሳ በሀሰት መመስከር ወይም ይመሰከርልኛል ብለን ካመጣነው ጭብጥ በተለየ እና ክሱን በሚጎዳ መልኩ መመስከር፣ ማስጠቃት፣ መጉዳት የሚለውን ትርጓሜ ይሰጠናል።

በሀገራችን አስጠቂ ወይም ሀሰተኛ ምስክርነትን አስመልክቶ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፊ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 452 ስለ አንድ ተከራካሪ ወገን የሚሰጠው ሀሰተኛ ቃል፡ 453 ስለ ሀሰተኛ ምስክርነት አስተያየት ወይም ትርጉም፡ 454 ላይ ቃልን ስለማቃናትና መለወጥ እያለ በተከታታይ ድንጋጌዎች ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ድንጋጌዎች በወንጀል የሚያስቀጡ ድርጊቶች መሆናቸውን የደነገገ ሲሆን፤ በዋናነትም አሁን ላይ በብዛት የተበራከተ በወንጀል ጉዳዮች ላይ ምስክሮች አንድን ድርጊት አይተው በፖሊስ ጣቢያ ምስክርነታቸውን ከሰጡ በኋላ ችሎት ቀርበው እንዲመሰክሩ ሲጠሩ ግን በተለያየ ምክንያት፦ ተከሳሾችን በመፍራት፣ ከተከሳሽ ጋር በመታረቅ ወይም መደለያ በመቀበል አስቀድመው በፖሊስ ጣቢያ የሰጡትን ቃል በመለወጥ ተከሳሽን ከቅጣት ሲያስመልጡ ይሰተዋላል።

በወንጀል ጉዳይ አንድ ግለሰብ ምስክር ሆኖ ከክስ በፊት ለፖሊስ የሰጠውን ቃል ፍርድ ቤት በቀረበ ጊዜ ከሚያውቀው ማስረጃ የቀየረ፣ የቀነሰ ወይም የጨመረ እንደሆነ በዚህ ጊዜ ዐቃቤ ህግ ለዳኛው ምስክሩ አስጠቂ ነው ብሎ ካሰወቀ እና መሪ ወይም መስቀለኛ ጥያቄ እንዲፈቀድለት ከጠየቀ ምስክሩ በፖሊስ ጣቢያ የሰጠውን ቃል አቅርቦ በመመልከት ዐቃቤ ህግ መስቀለኛ ጥያቄ እንዲጠይቀው ይፈቅዳል፤ ይህ መሪ ጥያቄ ምስክር ቀድሞ ለፖሊስ የሰጠውን ቃል መሰረት በማድረግ የሚጠየቅ ይሆናል፤ ይህ የሚረዳው ምስክር ተቃራኒ የሆኑ ነገሮችን እየተናገረ ስለመሆኑ ለፍርድ ቤቱ ለማረጋገጥ እና በመሪ ጥያቄ እውነቱን ለማዋጣት ይጠቅማል ማለት ነው። የሀገራችን የሥነ-ስርዓት ህግ መሪ ወይም መስቀለኛ ጥያቄን አስመልክቶ በግልፅ የተቀመጠ ባይሆንም የወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 137 /2/ ላይ በዋና ጥያቄ መሪ ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ከፈቀደ ሊጠየቅ የሚችል ስለመሆኑ ያስቀምጣል ከነዚህም ውስጥ አስጠቂ ምስክርነት አንዱ ነው።

የአስጠቂ ምስክርነት ቃል በራሱ ምስክርነት ተከሳሽን በሚጠቅም መልኩ የተሰጠ እንደሆነ ምስክሩ ልክ እንደመከላከያ ምስክር ስለሆነ አመሰካከሩ መስቀለኛ ጥያቄ በመጠየቅ እውነታውን ለማውጣት ጥረት ያደርጋል።

ከዚህ ድርጊት ጋር በቀጥታ ተያያዥነት ያለው የወንጀል ህግ አንቀፅ 453 ላይ ድርጊቱ ወንጀል ስለመሆኑ የተደነገገ ሲሆን ይኽውም ምስክሮች ማንኛውንም ተከራካሪ ወገን ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት በማሰብ ሀሰተኛ ምስክርነት ከሰጡ እና እውነቱን ከደበቁ ያሰቡት ባይሳካ እንኳን በቀላል እስራት ወይም ከ5 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን በዚህ የምስክርነት ቃልም ውጤቱ ተገኝቶ ከሆነ ማለትም ተከሳሹ በአስጠቂው ምስክር ምክንያት ነፃ ቢወጣ ከ10 ዓመት ባልበለጠ ፅኑ እስራት ያስቀጣል፤ በተቃራኒው ደግሞ ተከሳሹ በመስካሪው ድርጊት ምክንያት የጥፋተኝነት ውሳኔ የተላለፈው በንፁህ ሰው ወይም ተከሳሽ ላይ ከ10 ዓመት በላይ ፅኑ እስራት ተፈርዶበት ከሆነ ተከሳሽ በተቀጣው ቅጣት ልክ ሀሰተኛ ምስክሩ ሊቀጣ ይችላል ማለት ነው ።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በወንጀል የተደነገገው ሀሰተኛ የሆነ አስተርጓሚነት ሲሆን በሀሰት መተርጎምም ራሱን ችሎ በወንጀል የሚያስቀጣ ድርጊት ነው ። ሀሰተኛ ወይም አስጠቂ ምስክርነት ዋነኛ ጉዳቱ በተለይም በወንጀል ጉዳዮች ላይ ሰዎች ባልፈፀሙት ወንጀል እንዲቀጡ ወይም ወንጀል ፈፃሚዎች ከቅጣት እንዲያመልጡ በማድረግ ፍትህን ለማዛባት የሚከናወን በመሆኑ በጥንቃቄ የሚታይ ጉዳይ ነው።

የተከበራችሁ የፅሁፋችን አንባቢዎች እንድንጽፍላቹ የምትፈልጉት የህግ ማብራሪያ ካለ በአስተያየት መስጫው ላይ ብታስቀምጡ ምላሻችንን ታገኛላቹ፡፡
ጠ.አቃቤ ህግ
Create your Twitter account! #Share us your twitter account.
we will follow you‼️
We will follow you!
#Twitter
@ALE_lawsocieties
በቤት ኪራ ጭማሪ ለተሰቃየ መልካም ዜና!
የቤት ኪራይ መጨመር በህግ ያስቀጣል ላልሰሙት አሰሙ!

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪን ለመገደብ በወጣ ደንብ ላይ የተሰጠ መግለጫ!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማችን የኑሮ ውድነት እየተባባሰ እንደመጣ የሚታወቅ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱ በአብዛኛው አሳማኝ እና ምንም አይነት ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው በሰውሰራሽ ምክንያቶች የተፈጠረ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱም የከተማችንን ነዋሪ ለከፍተኛ ችግር ዳርጓል፡፡
በሰሜን የሃገራችን ክፍል ሃገር በማፍረስ ተግባር ላይ የሚገኘውን የአሸባሪው ህወሃት እንቅስቃሴ ለማክሸፍ እየተደረገ ካለው ዘመቻ ጋር ተያይዞ የከተማችን ነዋሪ በገንዘብ መዋጮ፤ ለሠራዊት የሚሆን ስንቅ በማዘጋጀት፤ ደም ልገሳ እስከ ህይወት መስዋዕትነት እየከፈለ ባለበት በዚህ ወቅት ጥቂት ስግብግብ ግለሰቦች በተቃራኒው ቆመው ከኢትዮጵያዊነት ጨዋነት ፍፁም ባፈነገጠ መልኩ አሁን ካለው ችግር ላይ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የተለያዩ ተግባራት ውስጥ ገብተው ይገኛሉ፡፡
መንግሥት እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመቅረፍ ከውጭና ከውስጥ ያሉ ጫናዎችን ተቋቁሞ ሀገር የማፍረስ ተግባር እንዲከሽፍና የዜጎች የኑሮ ጫና እንዲቀንስ የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል፡፡
በዚህም መሠረት እስከታችኛው የማኅበረሰብ ክፍልን የሚያሳትፍ የኢኮኖሚ አሻጥሩን ለመቀልበስ የተቋቋመው ግብረይል በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥም ግብረሃይሉ ባካናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች በመታየት ላይ ይገኛል፡፡
ከመሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች ባሻገር አለግባብና የወቅቱን ሁኔታ ያላገናዘበ የቤት ኪራይ ጭማሪ የነዋሪውን ሕይወት በእጅጉ እየፈተነው ይገኛል፡፡
ይህም ወቅታዊ ሁኔታን በመጠቀም አላግብ ለመክበር የሚደረግ ከኢትዮጵያዊ ጨዋነትና መተሳሰብ ጋር በፍፁም የሚቃረን ተግባር ነው፡፡
በ2012 ዓ.ም የኮቪድ 19 ወረርሽ በሀገራችን መገኘቱ ተከትሎ በርካቶች ችግር ውስጥ በገቡበት ወቅት የከተማችን ነዋሪዎች እርስ በእርስ ከመረዳዳትና ማዕድ ከመጋራት አልፎ በርካታ ቤት አከራዮች የወራት የቤት ኪራይ ዋጋ ለተከራይ በራሳቸው ተነሳሽነት ቀንሰው ችግሩን በጋራ ለመፍታት ኢትዮጵያው የመረዳዳት እሴታችን የታየበት እንደነበር ይታወሳል፡፡
ይህም በወቅቱ በሕግ ተቀምጦ የነበረውን የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር የሚከለክለውን ድንጋጌ ሳይጨምር ነው፡፡
አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት በቤት ክራይ ላይ ዋጋ ጭማሪ መታየቱን ነዋሪዎች ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው፡፡
ስለሆነም አሁን እየታየ ያለውን አላግባብ የሆነ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ለመገደብ የነዋሪውን ቅሬታ ምላሽ ለመስጠት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቀን 18/12/13 ባደረገው መደበኛ ስብሰባው የቤት ኪራይ ጭማሪን ለ90 ቀናት ለማገድ በቀረበ ደንብ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡
በዚህም መሠረት ደንቡ ከፀደቀበት 18/12/13 ዓ.ም ጀምሮ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ለ90 ቀናት የተከለከለ ሲሆን በቀጣይም ታይቶ ለተጨማሪ ቀናት ክልከላው ሊራዘም ይችላል፡፡
ደንቡን በመተላለፍ ጭማሪ የተደረገበት ተከራይ አቤቱታውን በፅሑፍ ለወረዳው ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት በማቅረብ መፍትሄ እንዲያገኝ የሚቻልበት ሥርዓት በደንቡ ተደንግጓል፡፡
በዚሀ መሰረት በሚቀርቡ አቤቱታዎች ላይ ማጣራት ተደርጎ ጭማሪ ባደረገ አካል ላይ በደንቡ ተዘርዝሮ በተቀመጠው መሰረት ተጠያቂ የሚደረግ ይሆናል፡፡
ምንም እንኳን ይህ ደንብ የወጣው ዜጎችን ካላስፈላጊ ጫና ለመከላከልና ጥፋተኞችን ተጠያቂ ለማድረግ ቢሆንም ህብረተሰባችን በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት ችግሮችን በመተሳሰብና በመደጋገፍ ለማለፍ ያሳየውን ኢትዮጵያዊ የጨዋነትና አብሮነት እሴቶቹን በማዳበር ይህን ወሳኝና አስቸጋሪ ጊዜ በጋራ ማለፍን ማዕከል በማድረግ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ነሐሴ 22 ቀን 2013
አዲስ አበባ፤
አዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት
የውጭ ሀገራት አንድ ሉአላዊት ሀገር እርዱኝ ሳትል ወይም ሌላ አካል ጣልቃ ገብቶብኛል እርዳታ እፈልጋለሁ ባላለችበት ሁኔታ ጣልቃ ሊገቡ የሚችሉበት international treaty አለ?save human right issue
selam ale tena yisetelegn ebakihin erdata felege nwu yekebel bet wust nwu yeminorewu keasadageye gar eso condomiya dersat ena ene bete endagegn yemiyadergegn hig ale malet memerya ebakine
ቢያውቋቸው ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ወሳኝ #ድረገፆች

ኢንተርኔት እንደዓለም ዳርቻ እጅግ ጥልቅ በሆነበት በአሁን ሰዓት ሁሉንም የድረገፅ አይነት
አውቆ መጠቀም ምናልባትም በዓለማችን በሚገኙ እያንዳንዱ ቦታዎች ተዘዋውሮ
እንደመጎብኘት እጅግ ሊከብድ ይችላል፡፡ ታዲያ እነዚህ ጥበብን፣ እውቀትን፣ ልምድን እና
በጠቅላላውም ህይወትን ለመቀየር የሚያስችሉትን፤ ወሳኝ ድረገፆች አውቆ ለመጠቀም
የሌሎች ጠቋሚነት እጅግ ወሳኝ ሆኖ ሊገኝ ይችላል፡፡ በመሆኑም ለዛሬ ከዚህ በፊት
የማያውቋቸው ነገር ግን ከዚህ በኋላ ቢያውቋቸው እጅግ ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ድረ
ገፆችን ከተለያዩ ምንጮች አሰባስበናል፡፡
ያወቁትን ሌሎች እንዲያውቁት ብታደርጉ የበለጠ ያተርፋሉ!!!
1. ከሌላው ዓለም ህዝብ ጋር ጥበብን፣ አውቀትን እና ልምድን ለማጋራትና ለማንሸራሸር
MentalFloss.com
Lifehacker.com
https://www.quora.com/
https://medium.com/
Lumosity.com
2. አዲስ ነገር መማር ሲፈልጉ
• Make code (Microsoft MakeCode) {Must visit!}
• Guitar ( https://www.justinguitar.com/ ) {you can thank}
• Duolingo (Learn a language for free)
• Tutorials Point (Tutorials)
• Experiments with Google
3. ለግራፊክስ ዲዛይነሮች ከphotoshop ውጭ ሌላ አማራጭ ሲፈልጉ
• Free Pik ( https://www.freepik.com/ )
• Flaticon ( https://www.flaticon.com/ )
• Adobe colour picker (Adobe Color CC)
• Pexels ( https://www.pexels.com/ )
• Video Pexels (Free stock videos - Pexels Videos)
• Canva (Amazingly Simple Graphic Design Software
4. ከEmail ውጭ ሌላ አማራጭ ይኖር ይሆን ካሉ
www.bluebottle.com
http://mail.yahoo.com
http://gmail.google.com
www.hotmail.com
www.walla.com
5. የጤናዬ ጉዳይ ያሳስበኛል ካሉ
www.nelh.nhs.uk
www.hpa.org.uk
www.food.gov.uk
www.bmj.com
www.avert.org
6. ሲደብሮትና እና ራሶን ለማንቃት ሲፈልጉ
• Ted ( https://www.ted.com/
www.7billionworld.com
www.beesbeesbees.com
www.sanger.dk
✳️ ጠቃሚ የመጽሐፍ ድረ ገጾችን እንጠቁማችሁ

◽️ http://gen.lib.rus.ec/
ይህ ድረ-ገጽ ማንኛው አይነት መፅሀፍ ማውረድ የሚያስችሎት
ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠር መፅሀፎች አሉት በዉስጡ
ከሚግኙ መፅሀፎች መካከል
🔺የትምህርት መፅሀፎች፤
🔺የሳይኮሎጂ መፅሀፎች፤
🔺ፍልስፍና መፅሀፎች ፤
🔺የታሪክ መፅሀፎች ይገኙበታል፡፡

◽️ http://sci-hub.org/
ይህ ድህረ-ገጽ ከ64 ሚሊዮን በላይ የጥናት ወረቀት የሚገኝ ሰለሆነ በቀላሉ ማዉረድ ይቻለሉ፡፡ በዚህ ድረ- ገጽ የተለያዩ መጻፎች በተለያ ምርጫ እና አይነት ያገኛሉ።

◽️ https://bookboon.com/
ይህ ድረገጽ ማንኛው አይነት የነጻ መጻፍ የሚያገኝበት
ሲሆን በየትኛዉም የክፍል ደረጃ ላሉ ተማሪዎች አንዲዉም በማንኛው የስራ ሁኔታ ላይ ላሉ ሰዎች ጠቃሚ ድርገጽ ነው፡፡

◽️ http://bookzz.org/ ቡክዚ አለማችን ለይ ትልቅ የመጻሀፍ ላይብረሪ ያለው ሲሆን በአማካኝ 2.6 ሚሊዮን መጻሀፍ በ ድረገጹ ይገኛል።

ይህ ድረገጽ ብዙ የቴክኖሎጂ መጽሀፍት ያሉት ሲሆን የፕሮግራሚንግ፤ ግራፊክስ፤ የኮምፒተር አጠቃቀም እና
የተለዩ የትምህርት መጻሃፎች ያገኛ
የተለያዩ ኮርሶችን መማር እና ማወቅ ለምትፈልጉ በሙሉ ማለትም ለምሳሌ #Programming , #Web_Development , #Networking እና ሌሎችም...(ከታች ያሉትን ሳይቶች ይጠቀሙ)

1. www.codecademy.com
2. www.lynda.com
3. www.udemy.com
4. www.udacity.com
5. www.coursera.org
6. www.w3schools.com
7. www.thenewboston.org
8. www.programmr.com
9. www.codeavengers.com
10. www.codeschool.com
11. www.learnstreet.com
12. www.teamtreehouse.com
13. www.sqlzoo.net
14. www.codehs.com
15. www.teamtreehouse.com
16. www.html5rocks.com
17. www.codepen.io
18. www.sitepoint.com
19. www.tutorialspoint.com
20. www.javatpoint.com
21. www.cplusplus.com
22. www.learncpp.com
23. www.tutorialspoint.com
24. www.cprogramming.com
25. www.stackoverflow.com
26. www.learncodethehardway.org
27. www.bloc.io
28. www.howtocode.io
29. www.edx.org
30. www.instructables.com
31. www.developer.apple.com
32. www.developer.android.com
33. www.developers.google.com
34. www.developer.mozilla.org
35. www.msdn.microsoft.com
36. www.decompera.com
37. www.www.developphp.com
38. www.quackit.com
39. www.htmlite.com
40. www.siteduzero.com
41. www.dreamincode.net
42. www.phpbuddy.com
43. www.php.net
44. www.microsoftvirtualacademy.com
45. www.professormesser.com

ያወቁትን ማሳወቅ ብልህነት ነውና ጓደኞቻችንን አባል በመሆን ይጠቀሙ ዘንድ ጋብዙ። finally #Share
via Mastewal click Ethiopian law
NYALA INSURANCE S.C.

JOB TYPE Employee

JOB STATUS Full Time

ANNOUNCED

30 August, 2021

JOB TITLE; Legal Secretary

JOB LOCATION

Addis Ababa, Ethiopia

JOB PRESENTATION

Nyala Insurance Share Company (NISCO) wants to hire a qualified, competent, and motivated candidate for the following position on a permanent basis: 

Qualification and Experience:

 Diploma in Office Management and Secretarial Science

Two (2) years in office administration or secretarial function preferably in courts and/or insurance companies.

Post available. One

Duty station: Addis Ababa

Remuneration: 

Nyala Insurance offers a competitive and attractive remuneration package.

Age: Not more than 35

 Soft qualities required:

integrity, quick to respond, cooperative, and stress tolerance. 

VALID TILL 4 Sep, 2021
NYALA INSURANCE S.C.

Position: LEGAL SECRETARY

Job Time: Full-Time

Job Type: Permanent

Place of Work: Addis Ababa, Ethiopia

Application Deadline: Oct, 4/2021 (4 days left)

Nyala Insurance Share Company (NISCO) wants to hire a qualified, competent, and motivated candidate for the following position on a permanent basis: 

Qualification and Experience:

 Diploma in Office Management and Secretarial Science

Two (2) years in office administration or secretarial function preferably in courts and/or insurance companies.

Post available. One

Duty station: Addis Ababa

Remuneration: 

Nyala Insurance offers a competitive and attractive remuneration package.

Age:Not more than 35

 Soft qualities required:

integrity, quick to respond, cooperative, and stress tolerance. 

How to apply

Interested applicants who fulfill the above requirements are invited to submit their application with a non-returnable copy of CV and credentials to the under-mentioned postal address or in person at our HO (Protection House) 3rd floor Room No. 307 located around 22 Mazoria Mickey Leland Road.

N.B. Only short-listed applicants will be contacted and invited for an interview.
NYALA INSURANCE S.C. (NISCO) PROTECTION HOUSE P. 0. Box 12753 Addis Ababa
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
🔴🔴🔴አዲስ ወደዚህ ግሩፕ የምትገቡ ውድ ቤተሰብ እዚህ ግሩፕ ላይ ምንም ነገር ከመፃፋችሁ በፊት 5 ሰው ወደ ግሩፑ መቀላቀል አለባችሁ።🔴🔴🔴