አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Each Of Us Has A Finite Amount Of Time, Energy, And Money;
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties

ALE (አለ) law societies 🔴
ALE (Alternative Legal Education)
All in one, for all.🔴
አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)
ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴
There is free legal aid. ነፃ የሕግ ድጋፍ አለ።

For discussion @ALE_lawsocieties

For more Contact us: @LawsocietiesBot
https://t.me/lawsocieties
በይርጋ የማይታገዱ የፍትሀብሄር ጉዳዬች
=======//////========

የይርጋ መሰረታዊ ዓላማ ማንኛውም በህግ በግልፅ የተደነገገ መብትና ግዴታ በህጉ በተወሰነው ወይም በተገደበው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ላለው አካል እንዲቀርቡ ግዴታን በማስቀመጥ መብቴ ተጣሰብኝ የሚል ወገን ዳተኛ ሳይሆን በትጋት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል መሆኑ ይታወቃል።

ነገር ግን አንዳንድ ጉዳዬች ከንብረቶቹ ልዩ ባህሪና የመንግስት ፖሊሲ አንፃር ህግ አውጪው በይርጋ እንዳይታገዱ አድርጎ ያስቀመጣቸው የፍትሀብሄር ጉዳዬች አሉ። ከእነዚህ መካከል፦

#የመፋለም ክስ ( petitory action)
~~××××××~~~~~

ለባለሀብቱ የባለቤትነት መብት ከሚሰጣቸው መብቶች መካከል ንብረቱ ያለ እርሱ ፈቃድ ከህግ ውጪ በሌላ ሰው ወይም ሀይል ከተወሰደ ንብረቱን ካለበት ድረስ በመከታተል የማስመለስ ወይም የመፋለም መብት አንዱ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 ድንጋጌ ያስረዳል፡፡

ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን” በሚል ርዕስ ስር በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1192 የተመለከተው በሚንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት በአስር ዓመት የጊዜ ወሰን /ይርጋ/ ቀሪ የሚሆንበትን አግባብ ያመላከተ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት በይርጋ ቀሪ እንደሚሆን ግን አያሳይም፡፡

ድንጋጌው የሚንቀሳቀስ ንብረትን የባለሀብትነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ ካስቀመጠ በኋላ ስለማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ቀሪ መሆን በዝምታ ያለፈው ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት በሌለው በፍ/ብ/ህግ አንቀፅ 1845 ስር የተመለከተው ተመሳሳይ የ10 ዓመት የይርጋ ጊዜ ተፈፃሚ እንደሆን ተፈልጎ ካለመሆኑ በላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሚንቀሳቀስ ንብረት በተለየ ሁኔታ የዘላቂነት ባህሪ ያለው እና ከትውልው ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በመሆኑ የባለሀብትነቱ መብት ቀሪ የሚሆነው በይርጋ ሳይሆን በሌሎች ሁኔታዎች( አንቀፅ 1168....) ይሆን ዘንድ ተፈልጎ የተቀመጠ ድንጋጌ መሆኑን እንገነዘባለን።

በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም ክስ (petitory action) በይርጋ ቀሪ አይሆንም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰ/መዝ/ቁ 43600)

N.B= ይህ ሲባል ግን ከውርስ፣ ከሽያጭ፣ ከስጦታና ከሌሎች ውሎች በመነጨ በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ክርክር ይርጋ የለውም ማለት የሚቻል ሳይሆን ለጉዳዩ አግባብነት ባላቸው ህጎች በተቀመጡ የይርጋ ጊዜዎች የሚስተናገዱ ይሆናል።

#ህገ ወጥ ውል (unlawful contrat)
~~~×××××~~~~~~

እንድ ውል የፀና ውል ለመሆን መሟላት ከሚገባው አንዱ ነጥብ ውሉ ህጋዊ በሆነ ጉዳይ ላይ የተመሰረተ መሆን የሚገባው እንደሆነ የፍ/ብ/ህግ 1678 ይደነግጋል። አንድ ውል ህገ ወጥ ውል ነው የሚባለው ደግሞ ተዋዋዬቹ የተዋዋሉበት መሰረታዊ ጉዳይ ዓላማ በመሰረታዊና ሞራላዊ ይዘቱ ተዋዋይ ወገኖች ስምምነት በማድረግ መብትና ግዴታ እንዲፈጥሩበት በህግ ያልተፈቀደ ወይም በህግ ክልከላ የተደረገበት ሆኖ ሲገኝ ነው።

አንድ ውል የተመሰረተበት መሰረታዊ ጉዳይ (object of contract) በህግ ክልከላ የተደረረበት በሆነ ጊዜ ውሉ በህግ ፊት እንደሌለና ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት የማያስከትል (null and void contrat) እንዲሁም ችግሩን በማስተካከል ህጋዊ ውጤት እንዲኖረው ማድረግ የማይቻል ነው። ለምሳሌ፦ የመሬት ሽያጭ ውል፣ በሰው ለመነገድ የተደረግ ውል፣ ወንጀል ለመፈፀም የተደረገ ውል......
ህገ ወጥ የሆነውን ውል ውድቅ ለማድረግ ደግሞ በህጉ የተደነገገው የይርጋ ጊዜ ገደብ መቃወሚያ ሊቀርብ የማይችልና ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በይርጋ የሚታገዱ አይደሉም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 43226)

N.B= ይህ ሲባል ግን የህጉን መስፈርት ያላሟሉ ውሎች (illegal contract) ከህገ ወጥ ውል በተለየ ሁኔታ ታይተው የይርጋ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የሚሆንባቸው መሆኑን መረዳት ይገባል።

#የመንግስትን መሬት የማስመለስ ክስ
~××××××~~~~~~

ግለሰቦች በፌደራሉ እና በክልሉ መንግስት በወጡ የገጠር መሬት አጠቃቀም እና አስተዳደር አዋጅ በሚደነግጉት መሰረት በህጋዊ መንገድ ሳይሰጣቸው ከህግ ውጪ የወል ወይም የመንግስትን መሬት ይዘው መቆየታቸው እና የመሬቱ ባለይዞታ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ማግኘታቸው የመሬቱ ህጋዊ ባለይዞታ ሊያደርጋቸው አይችልም። በወረራ የተያዘ የመንግስት መሬትም ይርጋ የሌለው መሆኑን የአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 በግልፅ ያስቀምጣል።

በመሆኑም ከህግ ውጭ በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ መሬቶችን መኖራቸውን ሲረዳ መሬት አስተዳደርም ሆነ የመንግስት ወኪል የሆነ አካል መሬቶቹን ለማስመለስ የሚያቀርበው ክስ በይርጋ የሚታገድ አይደለም። (የፌ/ጠ/ፍ/ቤት/ሰ/መዝ/ቁ 93013 እና 96203 ያልታተሙ)

#በህገ ወጥ መንገድ የተያዘ የግለሰብ ይዞ መሬት
~~××××××~~~~~~

ከላይ እንደተመለከትነው ህገ ወጥ ውልን መሰረት አድርጎ የግለሰብን መሬት በያዘ ሰው ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የሌለው መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በአብክመ የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 መሰረት ህጉ በማይፈቅድበት መንገድ በሀይልም ሆነ በህገ ወጥ አግባብ የገጠር መሬትን ይዞ የተገኘ ግለሰብ ላይ የሚቀርብ ክስ ይርጋ የለውም።

N.B= በህገ ወጥ መንገድ የሚለው ሀሳብ በህግ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን የያዘን በሚመለከት እንጂ የህጉን መስፈርት ባላሟላ ውል ወይም ተግባር (illegal contrat) አማካኝነት የተያዘን መሬት የሚመለከት አይደለም። ምክንያቱም መሬቱን የያዘው በህጉ በተፈቀደ የውል ተግባር ሆኖ የሚፈለገውን ፎርማሊቲ ወይም መስፈርት አለማለቱ ብቻ አያያዙ ህገ ወጥ ነው የሚያስብል ስላልሆነ ነው።

#የአደራ ውል
~×××

አደራ ተቀባይ በአደራ የሚጠብቀውን ዕቃ የሚመልስበት የጊዜ ገደብ በውል ተመልክቶ ከሆነ ይህ ጊዜ ሲያበቃ ዕቃውን መመለስ ያለበት ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2781(1) የተመለከተ ሲሆን በውል ላይ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ ከሌለ ግን አደራ ሰጪው እንደጠየቀ ወዲያውኑ እንደሚመለስ በፍ/ብ/ህ/ቁ 2989(1) ስር ተመላክቷል።

ከእነዚህ ድንጋጌዎች ለመረዳት የሚቻለው አደራ ተቀባይ ዕቃውን የሚመልስበት የጊዜ ገደብ ከሌለ በቀር አደራ ሰጪው በአደራ እንዲቀመጥ የሰጠው ዕቃ ያለምንም የጊዜ ገደብ በማንኛውም ጊዜ እንዲመለስለት መጠየቅ የሚችል መሆኑን ነው።

#የውርስ ሀብት ክፍፍል
~~~~××××~~~~

ወራሾች ተለይተው እና የውርስ ሀብቱ ድርሻ ታውቆ ነገር ግን ክፍፍል ሳይደረግ የቆየን የውርስ ሀብት በማናቸውም ጊዜ መጠየቅ እንደሚችልና በይርጋ የሚታገድ እንዳልሆነ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1060 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።

እንዲሁም ከውርስ ሀብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የውርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ ለክርክሩ ምክንያት የሆነውን የውርስ ንብረት በጋራ ይዞ ከቆየ ሰው ላይ የውርስ ድርሻዬን ልወቅ ወይም ይለይልኝ ጥያቄ በይርጋ ይታገዳል የሚባልበት አግባብ የለም።

#የድምፅ ብክለት
~×××~~
የድምፅ ብክለት ክልከላ ባለቤቱ ስራውን የሚፈፅመው በራሱ ንብረት ወይም ቤት ውስጥ ቢሆንም ድርጊቱ ሌላውን ጎረቤት እንዳይረብሽ፣ እንዳያውክ፣ ወይም ችግር እንዳያስከትል በማድረግ መብቱን ይጠቀም ዘንድ ህጉ ያበጀው የባለቤትነት መብት አጠቃቀምን አድማስ የሚወስን ስርዓት መሆኑን ከአንቀፅ 1226 እና ተከታዬቹ ድንጋጌዎች መረዳት ይቻላል።

ይህን ችግር ለማስወገድ የሚቀርበው አቤቱታ ከፍ/ብ/ህ/ቁ 1149 ስር ከተመለከተው በይዞታ ላይ ሁከት መፍጠር ተግባር የሚለይ ሲሆን አንዴ የተፈጠረ የድምፅ ብክለት እንዲቀጥል የሚደረግበት አግባብ ስለሌለ በይርጋ የሚታገድ አይደለም።
Source:- The Voice of Justice page
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የአ/አ/ከ/አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በሚሰጠው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ላይ ካርታው ‹‹በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፈቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› የሚል ማሳሰቢያ ማስቀመጡ ከንብረት መብት አንፃር ያለው ህጋዊነትና ፋይዳው
*******************************************
ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፌዴራል ህጎች ተፈጻሚነት መከታተያ ዳይሬክቶሬት ጥናት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል ከላይ በርዕሱ ላይ በተመለከተው ጉዳይ ዙሪያ የስራ ክፍሉ ያዘጋጀውን አጭር ሀተታ እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡

የአ/አ/ከ/አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የነባር ባለ ይዞታነትና የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ፣ የነባር ይዞታ ተነጻጻሪ ካርታ፣ ግንባታው የተጠናቀቀ የሊዝ ይዞታና የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ (አረንጓዴ ቀለም ያለው)፣ የሊዝ ተነጻጻሪ ባለይዞታና የቤት ባለቤትነት ካርታ እና ግንባታው ለተጀመረ የሊዝ ባለይዞታነትና የቤት ባለቤትነት ካርታ (ቢጫ ቀለም ያለው) ተራ ቁጥር ላይ ለተዘረዘሩት የካርታ አይነቶች በጀርባቸው ላይ የተቀመጠው ማሳሰቢያ ‹‹በዚህ ካርታ ላይ የሰፈረው ቦታ/ይዞታ በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› ሲል በነባር ይዞታ ተነጻጻሪ ካርታ ላይ ግን ‹‹በዚህ ካርታ ላይ የሚገኝ ንብረትን በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል እውቅና ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም የሚል ይዘትን አስቀምጧል፡፡ ይህም ካርታን ለመያዣ ለመጠቀም የሚመለከተውን አካል ፍቃድ ማግኝት ወይስ ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው? ይህ የሚያስፈልገውስ ለይዞታው ብቻ ወይስ ካርታው ላይ ለሰፈረው ለማንኛውም ንብረት ነውን ? ለሚለው ጥያቄ ወጥ በሆነ መልኩ ምላሽ የማይመልስ፣ የተለያየ ይዘት ያለው ማሳሰቢያ በተለያየ ጊዜ በካርታዎች ላይ የሚቀመጥና በተጠቃሚዎች ላይም የተለያየ ግዴታ እና መብት የሚጥል መሆኑን ያመላክታል፡፡

የዚህን ማሳሰቢያ ህጋዊነትና አላማን በተመለከተ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ ምዝገባ ጽ/ቤት ህጋዊ አስተያየት እንዲሰጠበት በጠየቀው መሰረት ካርታውን የሚያዘጋጀው የአ/አ/ከ/አስ/መ/ል/ማ/ቢሮ በቀን 27/02/2011 በቁጥር ይአሰ/45/2011 ማብራሪያ ሲሰጥ ካርታን እንደመያዣ መጠቀም የሚችሉት ከብሄራዊ ባንክ በኩል እውቅና ያገኙ የፋይናንስ ተቋማት ብቻ መሆናቸውን፤ ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል ግንኙነት ካርታን ማስያዝ እንደማይቻል፤ ለዚህ የህግ መሰረቱም የይዞታ አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 12/2004 አንቀጽ 33 መሆኑን፤ ‹‹በህጋዊ መንገድ ስልጣን ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጭ ለመያዣነት አያገለግልም›› በሚለው ማሳሰቢያ ውስጥ ስልጣን የተሰጠው አካል ማለት የይዞታ አስተዳደር የሽግግር ጊዜ አገ/ፕ/ጽ/ቤት እንደሆነና ከዚህ አካል ፍቃድና እውቅና ውጭ ለየትኛውም አገልግሎት ካርታን መጠቀም እንደማይችል፤ የማሳሰቢያው አላማም ብሄራዊ ባንክ እውቅና ከሰጣቸው ተቋማት ውጭ ንብረትን በመያዣነት እየያዙ ብድርን ለመስጠት የሚንቀሰቀቀሱ ተቋማትንና አራጣን ለመከላከል የተቀመጠ አሰራር እንደሆነ አብራርቷል፡:

በየካርታዎች ላይ የተቀመጠው ማሳሰቢያ ይዘትና የተሰጠውን ማብራሪያ ይህ ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረትን አጠቃቀም ከሚደነግጉ አለማቀፋው እና ሃገራዊ ህጎች ጋር ያለው ተስማሚነት እስከ ምን ድረስ ነው?፤ የማሳሰቢያውና የአሰራሩ ምንጭ በትክክልስ መመሪያ ቁ.12/2004 ሊሆን ይችላል? በንብረት የመጠቀም መብት ላይ ገደብ የሚያስቀምጥ ከመሆኑ አንጻር በህጎች ላይ የተቀመጠውን የገደብ አጣጣል መርህ የተከተለ ነው? ፤ በማብራሪያው እንደተቀመጠው ማሳሰቢያውና አሰራሩ አራጣን የመከላከል ሚና አለው? ይህስ ተግባር የሚያከናውን ሌላ ተቋም የለምን? የመመሪያ ቁ.12/2004 አንቀጽ 33 ድንጋጌ ይዘት ፈቃጅ ወይስ ከልካይ? ይህ አንቀጽስ በውል የሚቋቋም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ መለከታል? የሚለውን መመርመር አስፈላጊ ነው፡፡ የንብረት መብት ህገ-መንግስታዊ እውቅና ሊሰጣቸው ከሚገባ መብቶች አንዱ እንደመሆኑ መጠን የ1987ቱ የኢትዮጲያ ህገ-መንግስትም በምዕራፍ ሶስት ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነጻነቶችን እውቅና የሰጠ ሲሆን ማንኛውም የኢትዮጲያ ዜጋ ጉልበቱን ፤ የመፍጠር ችሎታውን እና ካፒታሉን ፈሰስ አድርጎ ያገኘው ንብረት ላይ የግል ባለቤትነት መብቱ የተጠበቀና የመሽጥ፤የማውረስና በማንኛውም መልኩ የማስተላለፍ (በዋስትና የማሳዝ) መብት ያለው መሆኑን ደንግጓል፡፡ ይህ መብቱ ሊገደብ የሚችለው የሌሎችን መብት ከተቃረነ ወይም መገደቡ የህዝብ ጥቅምን ለመጠበቅ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ባለ መብቱ ለሚደርስበት መጉላላት በቂ ካሳ ከተከፈለው እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡

መሬትን በተመለከተ የባለቤትነት መብቱ የመንግስትና የህዝብ ሲሆን ከገጠርና ከኢንቨስትመንት መሬት በተቃራኒ የከተማ መሬትን እንዴት ማግኝት ይቻላል? ይህ ህገ-መንግስት ከመውጣቱ በፊትም ሆነ በኋላ የከተማ መሬት የያዙ ሰዎች መብት እስከምን ድረስ ነው? የሚለውን ግን ሳይመልስ አልፎታል፡፡ የ1952ቱ የፍትሐብሄር ሕግ ህገ-መንግስቱ ከመወጣቱ በፊት እንደመውጣቱ መጠን የማይንቀሳቀስ ንብረትን (መሬትን ጨምሮ) መሸጥ፤ መለወጥ፤ማከራየት እና ለብደርም ሆነ ለሌላ እዳ እንደመያዣ መጠቀም እንደሚቻል በዝርዝር ደንግጓል፡፡ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በሶስት መልኩ ማለትም በህግ፤ በፍርድ ቤትና በውል ሊቋቋም ይችላል፡፡ ከህግ የሚመነጭ መያዣ ከተዋዋይ ወገኖች መካከል አንዱ ወገን ግዴታውን ባይወጣ ሌላው ወገን ጥቅሙን ስለሚያስከብርበት መንገድ ሳይዋዋሉ በቀሩ ጊዜ ህጉ ክፍቱን ለመሙላት ያሰቀመጣቸው ሁኔታዎች ሲሆኑ ለምሳሌ አንድ የማይንቀሳቀስ ንብረት የሸጠ ሰው ላልተከፈለው የብር መጠንና በውሉ ላይ ላሉት መብቶች የሸጠው የማይንቀሰቀስ ንብረት እንደ መያዣ ሆኖ ያገለግለዋል ሲል ህጉ ደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍርድ ቤት ከሚሰጡ ትዕዛዞችና ውሳኔዎች የሚመነጭ መያዣ የሚቋቋመው ከፍርድ በፊትም ሆነ በኋላ በራሱ በፍርድ ቤቱ አነሳሽነት ወይም በከሳሹ (በፍርድ በለመብቱ) ጠያቂነት ለክርክሩ መነሻ የሆነው የማይንቀሳቀስ ንብረት ክርክሩ እስከሚያልቅ ድረስ ወይም ለፍርድ አፈጻጸም ሲባል እንደመያዣ ሆኖ ተከብሮ እንዲቆይ ሲል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በሚሰጥበት ጊዜ ነው፡፡ በውል የሚቋቋም የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ተዋዋይ ወገኖች ነጻ ፍቃድና ስምምነት መሰረት በተደረገ ወይም ለወደፊቱ በሚደረግ ውል ለሚደርስ /ይደርሳል/ ተብሎ ለሚጠበቅ የብር መጠን ልክ የማይንቀሳቀስ ንብረት እንደ መያዣ የሚያዝበት ተጨማሪ ውል ነው፡፡
ስለውል በጠቅላላው በሚደነግገው ክፍል የተቀመጡ የችሎታ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ባለእዳው አንድን የማይንቀሳቅስ ንብረት ለገንዘብ ጠያቂው በውል በመያዣነት ለመስጠት የሚችለው ንብረቱን የመሸጥ የመለወጥ መብት ካለው ወይም ሶስተኛ ወገንም ከሆነም ንብረቱን ስለባለዕዳው ለማሲያዝ የሚችለው ንብረቱን በስጦታ የመስጠት ችሎታ ያለው ከሆነ ብቻ ነው፡፡
የፍትሐብሄር ህጉ የማይንቀሳቀስ ንብረት የመያዣ ውል የሚቋቋምባቸው ንብረቶች በህግ እንደማይንቀሳቀስ ንብረት የሚቆጠሩ ተንቀሳቃሽ ንብረቶች እንደተጠበቁ ሆነው መሬትና ቤት ናቸው ቢልም አሁን መሬት የህዝብና የመንግስት ከመሆኑ አንጻር በቀጥታ ያለምንም ገደበ መሽጥ ወይም መለወጥ አይቻልም፡፡ ሆኖም ግን የከተማ ቦታን በሊዝ ያገኘ ግለሰብ ለቦታው በከፈለው የሊዝ ዋጋ ልክና የሊዝ ዘመን ድረስ ቦታውን ወይም ቤቱን ለውል ማሳዣ መጠቀም እንደሚችል በሊዚ አዋጅ 721/04 ተደንግጓል፡፡ ይህንንም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ሊዝ አፈጻጸም ደንብ ቁ.49/2004 እና መመሪያ ቁ.11/2004 በተመሳሳይ በግለጽ ደንግገውት ይገኛል፡፡

ለብድር ሆነ ለሌላ ውል ማስያዣ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሲያዝ ውል ለማረጋገጥና ለመመዝገብ ስልጣን በተሰጠው አካል (በአዲስ አበባ ደረጃ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኢጀንሲ) ቀርቦ በጹሁፍ ሆኖ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡ ይህ ያስፈለገበት ምክንያት በዋናነት የዜጎችን የግል ንብረት የማፍራት፣ የመጠቀም እና በሕጋዊ መንገድ የማስተላለፍ መብትን በማስከበር የፍትሕ ሥርዓቱን ለማገዝ የሕግ የበላይነትን ለማስጠበቅ፤ የመልካም አስተዳደርን እና የነጻ ገበያ ሥርዓት ግንባታን ለማሳለጥ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡ ሰነድ አረጋጋጩም ሰነድ ከማረጋገጡና ከመመዝገቡ በፊት የሰነዱ ይዘት ሕግን እና ሞራልን የማይቃረን መሆኑን የማረጋገጥ ስልጣንና ተግባር ያለው ሲሆን የማይንቀሳቀስ ንብረት የመያዣ ውል በአዋጁ መሠረት ሲመዘግብ በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የመያዣ ውል ሰነድና የማይንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ሁለት የሰው ምስክር መቅረቡን፤ እዳና እገዳ አለመኖሩን፣ ተዋዋዮች ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው ስለመሆኑ፣ የተዋዋዮች መታወቂያና ያላገባ ወይም ያገባ ማስረጃ፤ የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት፣ በመያዣነት የቀረበው ንብረት የባለቤትነት ማረጋገጫ ማስረጃ አስቀርቦና መርምሮ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ይህም ተበዳሪውም ሆነ አበዳሪው እንዳይታልልና ህግ-ወጥ ተግባር ውስጥ እንዳይሳተፍ የሚያደርግ ነው፡፡

ከህግና ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚመነጭ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ በውልና ማስረጃ ቀርቦ መረጋገጥና መመዝገብ አይጠበቅበትም ምክኒያቱም ከህግ ከሆነ ህጉን ጠቅሶ መብትን ማስከበር ስለሚቻል እንዲሁም ከፍርድ የመነጨ ከሆነም የማይንቀሳቀስ ንብረት አስተዳዳሪ ለሆነ አካል ንብረቱ እንዲታገድና ተከብሮ እንዲቆ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ማድረግ ብቻ በቂ ስለሆነ ነው፡፡ በተመሳሳይም ከባንክ ወይም ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ለሚደረግ የብደር ውል የማይንቀሳቀስ ንብረቱን እንደመያዣ የሰጠ ተበዳሪ በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ሄዶ መዋዋልና ማስመዝገብ ሳያስፈልገው ንብረት አስተዳደር ለሆነው (በአዲስ አበባ ደረጃ ለመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ) አካል የብድር ስምምነቱና የመያዣ ውሉ በባለንብረቱ የግል ማህደር ተመዝግቦ እንዲቀመጥ መድረጉ ብቻ በቂ መሆኑ በህጎች ላይ እና በቃለ -መጠየቅ ከሰበሰብነው መረጃ ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

በዚህም ምክኒያት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህንና ሌሎች አገልግሎቶችን የሚጠይቁ ባለጉዳዮችን ከሊዚ አዋጁ፤ ከደንቡና ከአፈጻጸም መመሪያው ጋር የተጣጣመና ወጥ የሆነ አገልግሎት ለመስጠጥ ያስችለው ዘንድ የይዞታ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁ.12/2004 ያወጣ ሲሆን ይህ መመሪያም በከተማ አስተዳደሩ የሚኖሩ ነዋሪዎች የካርታ ይሰራልኝ፤ የስም ይዛወርልኝ፤ ይዞታ ይከፈልልኝ እና ተያያዥ አገልግሎትን ምን ሲያሟሉ ያገኛሉ የሚለውን አስከ አንቀጽ 32 ድረስ ካስቀመጠ በኋል ዋስትናና እገዳ ይመዝገብልኝና ይሰረዝልኝ አገልግሎት እንዴት ይሰጣል? የሚለውን በአንቀጽ 33 ምላሽ የሰጠ ሲሆን የዚህ አገልግሎት ጥያቄ ቀጥታ ከነማን ሊቀርብ ይችላል የሚለውን በማሳያ መልኩ ሲደነግግ ‹‹የዋስትናና ዕገዳ ምዝገባ አገልገሎት ጥያቄ ከፍርድ ቤት፣ ከባንክ፣ ከኢንሹራንስና ሌሎች በሕግ አግባብ ስልጣን ከተሰጣቸው አካላት ሊቀርብ ይችላል።

“ዋስትናና ዕገዳ ምዝገባና ስረዛውም እንደሚከተለው ይፈጸማል›› በማለት አስቀምጦ እናገኝዋለን፡፡ በየካርታዎች ላይ እየተቀመጠ ያለው ማሳሰቢያና ካርታን እንደማስያዣ በመጠቀም ከግለሰብ መበደርን የሚከለክለው አሰራር የህግ መሰረቱ መመሪያ ቁ.12/2004 ነውን? የሚለውን ጉዳይ ስንመረምረው ከላይ ከተቀመጡት አለማቀፍ ህጎች፤ የ1987ቱ ህገ-መንግስት፤ የፍትሃብሄር ህጉ፤ የሊዚ አዋጁና በአዲስ አበባ ደረጃ የወጡ የሊዚ አፈጻጸም ደንብና መመሪያም ሆነ ራሱ መመሪያ ቁ.12/2004 በነባር ይዞታ ሆነ በሊዚ ለተገኘ ቦታ የተሰጠን ካርታ ባለይዞታው ለብደርም ሆነ ለሌላ ውል እንደማሳዣ ለመጠቀም የሚችለው በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል ሲፈቅድና ውሉም (የብደር ውልን ጨምሮ) ከብሄራዊ ባንክ እውቅና ካገኘ የፋይናንስ ተቋም ጋር ከተደረገ ብቻ ነው የሚል ቅድመ-ሁኔታን ያዘለ ገደብ /ክልከላን/ አላስቀመጡም፡፡ ይልቁንም ከላይ እንዳየነው በአለማቀፍ ህጎችና ስምምነቶች ላይ የተቀመጡ የሰብአዊ መብት (የንብረት መብትን ጨምሮ) ድንጋጌዎች ሲተረጎሙ መንግስትም ቢሆን መብቶችን በሚያጣብብና በሚያፈርስ መልኩ ሊተረጉሟቸው እንደማይገባ ተደንግጓል፡፡

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስትም ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው የአለማቀፍ የሰብአዊ መብት የስምምነት ሰነዶች ልክ እንደ ሀገሪቱ ህግ የሚቆጠሩ ሲሆን ሶስቱ የመንግስት መዋቅሮችም እነዚህን መብቶች የማክበር፣ የማስከበርና የማሳደግ (የማሟላት) ግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ህገ-መንግስቱ በዚህ መልክ ለንብረት መብት ጥበቃ የሚያደርግለት ከሆነ በየደረጃው የሚገኝ ህግ አውጭ፤ ህግ አስፈጻሚና ህግ ተርጓሚ ለአሰራር አመችነት ሲል ወይም በቸልተኝነት በግልጽ የህገ-መንግሰት ወይም ህገ-መንግስቱን መሰረት አድርገው የወጡ ህጎችን መሰረት (ድጋፍ) ያላደረገ ህግ በማውጣት፣ የህግ መሰረት የሌለው አሰራር በማስቀመጥና በአግባቡ የወጡ ህጎችንም ከወጡበት አላማ ውጭ በመተርጎም መብቶችን መገደብ ወይም ማስቀረት የህግ ውጤት የሌለውና እንዳልተደረገ የሚቆጠር ተግባር እንደሆነ ህገ-መንግስቱ ደንግጓል፡፡

የፌዴራሉ የሊዚ አዋጅም ሆነ የአ/አ/ከ/አስተዳደር ያወጣው የሊዚ አፈጻጸም ደንብና መመሪያ ካርታን ለማሳዣነት ለመጠቀም በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል ፍቃድ ያስፈልጋል፤ ይህ ስልጣን የተሰጠው አካልም የአ/አ/ከ/አስ/የይ/ጊ/ሽ/አገ/ፕሮጀክት ዴስክ ስለመሆኑም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት ማረጋገጫ ካርታን ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል መጠቀም አይቻልም የሚል የህግ ድንጋጌ አላስቀመጡም፡፡ የአግልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁ.12/2004 በመግቢያው ላይ ‹‹ሰነድ ያላቸው ህጋዊ ባለይዞታዎችና በህግ የከተማ ቦታ የሚፈቀድላቸው ሰዎች የሚጠይቋቸውን የተለያዩ መስተንግዶዎች ከሊዚ አዋጁና ደንቡ ጋር በተጣጣመ መልኩ ለመስጠት እንዲቻል›› በማለት ያስቀመጠውን አለማ ስናይም የሊዚ አዋጁን፣ የአፈጻጸም ደንብና መመሪያውን ሳይከተል ለተቀመጠ ማሳሰቢያና አሰራር የህግ መሰረቱ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ይልቁንስ ከመመሪያው ስያሜ ማለትም (የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ) ከሚለው ጀምሮ ከአንቀጽ 1 አስከ 32 ያሉ የህግ ድንጋጌዎች የካርታ አሰጣጥ፤የስም ዝውውር፤ የቦታ ክፍፍል የመሳሰሉት አገልግቶች በተገልጋዩ በሚጠየቁ ጊዜ እንዴት ይስተናገዱ የሚለውን እንደሚመልሱት ሁሉ አንቀጽ 33 ትም ከላይ እንዳየነው ፍርድ ቤቶች፤ባንኮች እና የኢንሹራንስ ተቋማት የማይንቀሳቀስ ንብረትን (ካርታን) ለፍርድ አፈጻጸምም ሆነ ለእዳ
ማስከበሪያ ሲይዙ በውልና ማስረጃ መዋዋልና ማስመዝገብ ስለማያስፈልጋቸው ቀጥታ ንብረቱን ለሚያስተዳድረው የአዲስ አበባ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ እግዱ ወይም የዋስትና ሰነዱ በባለ እዳው የግል የንብረት ማህደር እንዲቀመጥ ወይም እዳና እገዳው እንዲነሳ አግልግሎት በሚጠይቁበት ጊዜ አግልግሎቱ እንዴት ይሰጣል? የሚለውን ለመመለስና ይህን አገልግሎትስ እነማን ያገኛሉ ለሚለው በአብነት መልክ ያስቀመጠ እንጅ ካርታን የሚይዙት እነዚህ አካላት ብቻ ናቸው ባላለበት፣ መመሪያ እንደመሆኑ መጠን የፍትሃብሄር ህጉንና የሰነዶች ማረጋገጫ ምዝገባ አዋጅን መሻር በማይችልበትና በነዚህ ህጎች መሰረት በግለሰቦች መካከል ለሚቋቋም የብደር ውል ማስከበሪያ የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣን በግልጽ ባልከለከለበት፤ የማይንቀሳቀስ ንብረት ማረጋገጫ ካርታን ከመጠቀም ጋር ተያይዞ ለአ/አ/ከ/አስ/የይ/ጊ/አገ/ፕ/ዴስክ ስልጣን ባልሰጠበት ሁኔታ የመመሪያው አንቀጽ 33 በካርታዎች ላይ ለሚቀመጠው መብት ገዳቢ ማሳሰቢያና ከግለሰብ ጋር ለሚደረግ የብድር ውል ካርታን እንደ ማሳዣ መጠቀምን ለሚከለክለው አሰራር የህግ መሰረት የሚሆንበት አግባብ የለም፡፡

የማሳሰቢያውና የክልከላው አላማም ባለይዞታዎችን በብድር ስም ካርታን እንደመያዣ እየያዙ የአራጣን ስራ ከሚሰሩ ግለሰቦች ለመጠበቅና አራጣን ለመከላከል ነው ይባል እንጅ አራጣ ማለት አንድ ሰው የሌላውን ሰው ችግረኛነት፤ የበታችነት፤ ወይም ደካማነቱን አይቶ በህግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ካበደረው ወይም ተመጣጣኝነት የሌለውን ንብረት በምትኩ እንዲሰጠው ቃል(ውል) ያስገባው እንደሆነ ነው፡፡ ከጉዳያችን ጋር የሚያያዘው ተመጣጣኝ ያለሆነ (ከእዳው የበለጠ) ንብረት በመያዣ መያዝ ሲሆን ይህ ድርጊት በወንጀል የሚያስቀጣና በቀጥታ የፍትህ አካለት (የፖሊስ፤ የዓቃቤ ህግ መሰሪያ ቤትና የፍርድ ቤትን) የሚመለከት ከመሆኑ በተጫማሪ አበዳሪው ተመጣጣኝ ያልሆነ ንብረትን (መሬትና ቤት ሲሆን) በምትኩ እንዲሰጠው የሚያደርግ አሰገዳጅ ቃል (ውል) ተበዳሪውን ለማሰገባት ከላይ እንደተመለከትነው ይህ የተገባው ቃል ወይም ውል በውልና ማስረጃ መመዝገብ ይጠበቅበታል፡፡ መዝጋቢው አካልም (በአ/አ/ ደረጃ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኢጀንሲ) ከተሰጠው ስልጣንና ሃላፊነት መካከል የተዋዋዮችን ችሎታ ፤ ንብረቱን ወይም ካርታውን የሚያስዘው ግለሰብ ህጋዊ ባለቤትነትን፤ ንብረቱ ለምን ያህል የገንዘብ መጠን እንደተያዘ በውሉ መቀመጡን፤ ይህን ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው ከህግና /ለምሳሌ አራጣን ከሚከለክለው የወንጀል ህግ/ ከሞራል አንጻር የማይቃረን መሆኑን የማረጋገጥና የመመዝገብ ነው፡፡

ወንጀልን የመከላከል የሁሉም ግለሰብና ተቋም ድርሻ ቢሆንም በዋናነት ከላይ የጠቀስናቸው ተቋማት ሃላፊነት ሆኖ እያለ በህግ በግልጽ ይህን ወንጀል እንዲከላከል ግዴታ ባልተጣለበትና በካርታ አጠቃቀም መብት ላይ ገደብ የማስቀመጥ ስልጣን ባልተሰጠበት ሁኔታ አራጣን ለመከላከል ነው በሚል የዜጎችን በንብረት የመጠቀም ሰብአዊ መብት የሚገድብ የህግ መሰረት የሌለው ማሳሰቢያና ከልካይ አሰራር ማስቀመጡ አግባብ አይደለም፡፡

ውድ የፌስ ቡክ ገጻችን ተከታታዮች ከማብራሪያው ጥሩ ግንዛቤ እንደጨበጣችሁ እየተማመንን በቀጣይ በዚሁ የስራ ክፍል ጥናት የተደረገባቸው ጉዳዮች ላይ የቀረቡ ሀተታዎችን ይዘን የምንቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ቸር ቆዩን!
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza Lawyer)
Exit Exam ውጤት #በትንሽ ነጥብ ልዩነት ያልመጣላችሁ ውድ የህግ ቤተሰቦች ውጤት በወጣ በ15 ቀን ውስጥ remark (እንደገና ይታረምልኝ) ጥያቄ በህግ ት/ቤታችሁ በኩል በፅሁፍ በማመልከት መጠየቅ ትችላላችሁ። ለበለጠ መረጃ የህግ ት/ቤታችሁን ሄድ ፤ ዲን ወይም ሀላፊ በመጠየቅ እንደገና ለማሳረም መስፈርቱን የምታሟሉ ከሆነ ብቻ ሂደቱን ጠብቃችሁ እንድታመለክቱ እናበረታታችኋለን።
የመረጃው ምንጭ @lawsocieties #አለ #ALE
We go together‼️

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
🟢🟡🔴ክፍት ስራ ለህግ ተመራቂዎች
4 አመት የስራ ልምድ
አ.አ ን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
ክፍት ስራ ለህግ ባለሙያዎች🟢🟡🔴
Junior Attorney
(Legal Services Department)

https://t.me/lawsocieties

Hibret Bank


Hibret Bank invites applicants who meet the following qualification and experience requirements to apply for the vacant positions.
Job Requirement • Educational Qualification: LLB /Bachelor Degree in Law • Work Experience; 2 years relevant experience

How to Apply Interested applicants should apply in person along with non-returnable updated CV and copies of relevant credentials from the date of this vacancy announcement until February 12, 2021 to:
Hibret Bank S.C. Human Capital Business Partnering Department Mekwor Plaza Building, 4th floor Addis Ababa

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
JUNIOR ATTORNEY

https://t.me/lawsocieties

Hibret Bank

Addis Ababa

Full–time

Job Requirement LLB /Bachelor Degree in Law, 2 years relevant experience.
How to Apply Deadline: February 12, 2021 Interested applicants should apply in person along with non-returnable updated CV and copies of relevant credentials to: Hibret Bank S.C., Human Capital Business Partnering Department, Mekwor Plaza Building, 4th floor, P.O.Box 19963, Addis Ababa
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
𝐟𝐚𝐢𝐥𝐮𝐫𝐞 𝐰𝐢𝐥𝐥 𝐧𝐞𝐯𝐞𝐫 𝐨𝐯𝐞𝐫𝐭𝐚𝐤𝐞 𝐦𝐞 𝐢𝐟 𝐦𝐲 𝐝𝐞𝐭𝐞𝐫𝐦𝐢𝐧𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐭𝐨 𝐬𝐮𝐜𝐜𝐞𝐞𝐝 𝐢𝐬 𝐬𝐭𝐫𝐨𝐧𝐠 𝐞𝐧𝐨𝐮𝐠𝐡

Have an amazing day 💕

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
የስራ መደብ: የውል አስተዳደር ባለሙያ

ደመወዝ: 7071 ብር
ተፈላጊ ብዛት: 01
የስራ ልምድ: 04 ዓመት
የትምህርት ደረጃ: በህግ፣ ሲቪል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ላት
📌 📌 ሰለ ሰራው ሙሉ መረጃ ለማየት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ፡ 📌 📌

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties



https://ayerbayer.com/debark-university-job-vacancy-announcement-ayerbayer/
Legal Consultant
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties

International Foundation fo...

Addis Ababa

Full–time

PRIMARY FUNCTION/PURPOSE: The Legal Consultant is expected to support the legal team of the International Foundation for Electoral Systems (hereinafter ‘IFES’) on a range of issues including drafting electoral legal documents, training materials and providing other technical assistance to IFES’ support the National Election Board of Ethiopia (hereinafter ‘NEBE’) and the judiciary towards the successful conduct of the upcoming general elections in Ethiopia. MAJOR DUTIES & RESPONSIBILITIES Providing high level technical assistance and input in the area of legal and regulatory reform; this may include reviewing, updating, drafting and commenting on electoral and referenda legislation; institutional by-laws and proclamations, including technical topics such as inclusion, electoral dispute resolution and political finance (in English and Amharic); Developing and refining training manuals; Supporting NEBE and the judiciary on Election Dispute Resolution (EDR) matters; Giving technical support to legal trainings at NEBE HQ, the Federal Supreme Court as well as regional branches of the NEBE and regional courts; Supporting the IFES legal team in coordinating different electoral legal matters; Supporting implementation of activities as directed by the IFES legal team; Conducting research and analysis on assigned topics to support internal and external presentations, consultations and reports; and Undertaking ad-hoc tasks assigned by the IFES legal team, as required. Duration of Employment : -The duration of this employment is six (6) months. TRAVEL: Travel may be required.
Educational Requirements: SKILLS & SPECIFICATIONS Ability to establish, maintain and foster positive and harmonious working relationships; Ability to work effectively both independently and in a team environment and utilize initiative to direct own and others' activities; Ability to remain highly organized while handling multiple tasks under tight deadlines and show initiative, good judgment, and resourcefulness; Not be a... Required Experience: Senior Level (5+ years experience

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
Attorney I

#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties

Awash Bank

Addis Ababa

Full–time

Job Summary The Job holder is responsible for representing the Bank before judicial & quasi- judicial tribunals, rendering advises and drafting contracts and other legal documents, preparation of cases (pleading, defenses and petition), handling & processing foreclosure cases. Place of Work LL.B Degree in Law plus a minimum of Four (4) years of relevant banking experience. Place of Location Addis Ababa How to Apply Term of Employment: Permanent for all Positions Skills Requirement Knowledge of computer operation is mandatory Salary & Benefits: As per the Bank’s Salary Scale & Benefits Package Interested applicants, who fulfill the above requirement, are invited to apply via Online Job Application System; https://jobs.awashbank.com or send their non-returnable application with CV and copies of relevant documents through the following address within 7 consecutive days from the first date of this announcement on the website. N.B. * Incomplete applications will not be considered. Applicant should specify the place where he/she applies for or Duty Station. Awash Bank Deputy Chief Human Resources Management Office P.O. Box 12638 Addis Ababa
#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
ATTORNEY II

#ሼር #አለ #Share #ALE
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties

Awash Bank

Addis Ababa
Full–time

Job Requirement LL.B Degree in Law plus a minimum of Six (6) years of relevant banking experience. Place of Work: Addis Ababa How to Apply Deadline: February 15, 2021 Interested applicants, who fulfill the above requirement, are invited to apply through Online Job Application System or send their non-returnable application with CV and copies of relevant documents through the following address. Awash Bank, Deputy Chief Human Resources Management Office, P.O. Box 12638 , Addis Ababa • Applicant should specify the place where he/she applies for or Duty Station.

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
#feelgood
The real joy of Life is often found in small acts of kindness without any expectations of returns.
Treat people with kindness. Your simple act might be the only one making them happy in a Day.

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
The Procedure for Obtaining Equivalent Driving License in Ethiopia

Issuing Authority

Ministry of Transport

Issuance of Supporting Letter for Provision of Equivalent Driving License

Equivalent Driving License can be given to diplomats of other countries and staffs of international/ continental organizations with which the country has signed Memorandum of Understanding (MOU) and other foreign individuals authorized by Ministry of Finance and Economic Cooperation to get the Equivalent Driving License in order to driving vehicles in Ethiopia.

Service Description

Equivalent Driving License can be authorized and issued by the FDRE Ministry of Transport. It is given to foreign diplomats and staffs of international/ continental organizations that have signed an agreement with Ethiopia and their respective spouses or dependents.

Customers who want to get the service of issuance of supporting letter for provision of equivalent driving license should;

Fill and submit service application form for issuance of supporting letter for provision of equivalent driving license;

Attach Official service requesting letter, Note Verbal, signed by authorized higher official of service requesting embassy or international/continental organization;

Attach Diplomatic ID Card of the service requesting individual;

Attach Driving License of the service requesting individual;

Attach Interpretation of the Driving License, if it is prepared in a language other than English.

The Ministry of Foreign Affairs reviews the service request and if all requirements are met, prepares (cancel out “issues”) supporting letter to Federal Transport Authority for Provision of Equivalent Driving License.

Attach an official translation of the Driving License, if it is in a language other than English.

Service Request Form for Issuance of Supporting Letter for Provision of Equivalent Driving License

Surname of Applicant *

Given Name of Applicant *

Designation of Applicant *

Name of Country where the Driving License is Issued *

Level of the Driving License

Identification Number of Driving License

Language of Preparation of the Driving License

Attachment For The Note Verbal *

Attachment For sponsor’s ID Card *

Attachment For The Driving License of the Applicant

Attachment For The Interpretation of Driving License of the Applicant

Number of Note Verbal *

Application Date

Embassy or Organization *

Organization/Embassy

Tittle (Mr,…) *

If request is for Spouse

Wife/Husband

Title of Spouse

Spouse’s Surname

Spouse’s Given Name

Mobile *

Diplomatic ID Card Number of the Applicant *

via  Abrham Yohannes
https://chilot.me/2021/02/the-procedure-for-obtaining-equivalent-driving-license-in-ethiopia/

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
Senior Legal Officer at Belima International Business PLC/Daily Water


Company: Belima International Business PLC/Daily Water

Location: Ethiopia

State: Addis Ababa Jobs

Job type: Full-Time

Job Requirements

Law With LLB  Degree (knowledge of the Ethiopian Commercial Law  as well as private companies lab our law

Minimum of 4 years of experience as legal adviser or Attorney at law for 2 years of experience.
Method of Application

Duty station – Addis Ababa

Registration place

In front of Saint St. Lideta Church
at Dashen Bank Building 6th floor

Applicants Should submit their non returnable copies and all necessary Original Document with their application letter in person.

Tel +251-11-156-74-14 /251-11-156-76-67 /251-11-156-81-80 /251-11-155-00-28

Mail - applydailywater@gmail.com

Closing Date : 15th February, 2021

#ሼር #አለ #Share #ALE

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties

https://t.me/lawsocieties