አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
January 1
court annexed mediation public awareness.pdf
3.5 MB
በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 በአንቀፅ 45-48 ስር ስለተደነገገው በፌደራል ፍርድ ቤቶች አስገዳጅ ስለሆነው የፍርድ ቤት መር ማስማማት አገልግሎት ምን ያህል ያውቃሉ?

ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ የሕግ እውቀት alehig.com
January 2
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ የሕግ እውቀት alehig.com
January 2
Forwarded from ሕግ ቤት
Personal Data Protection Proclamation No. 1321-2024_Signed.pdf
2 MB
Proclamation no. 1321/2024 personal Data Protection proclamation

አዋጅ ቁ. 1321/2016 የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ
January 3
⚠️⛔️ባልና ሚስት በጋብቻ መካከል በየትኛውም ንብረት ላይ እርስ በራስ የሚያደርጉት የስጦታ ውል ፍርድ ቤት ቀርቦ ካልፀደቀ በቀር  በህግ ፊት ተቀባይነት የለውም
🔽ፌደራል ሰበር ሰሚ ፍ/ቤት በሰ.መ.ቁ. 158292 አስገዳጅ የሕግ ትርጉም‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 3
ኢንትረስት ሜዲካል IVF
ፀደቀ‼️በኢትዮጵያ የወንድ የዘር ፈሳሽ ልገሳ፣ የሰውነት አካል መለገስ እና በህክምና የታገዘ ሞት እንዲጀመር የሚፈቅደው ህግ ጸደቀ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና አገልግሎት እና አስተዳድር ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል። አዋጁ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ተጀምረው የማያውቁ እና አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ የጤና አገልግሎቶች እንዲጀመሩ የሚያደርግ ነው። ለአብነትም መዳን በማይችል እና በስቃይ ውስጥ…
➡️ የዘር ፍሬ በመለገስ ልጅ መውለድ እንዲቻል ለመፍቀድ ቀርቦ የነበረው የአዋጅ ድንጋጌ የለበትም።
የጤና አገልግሎት አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ " ለ3 ወር ያህል ውይይት ሲደረግበት ቆይቶ ከቀናት በፊት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ9 ድመጸ ተአቅቦ ፣ 1 ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል።

የዘር ፍሬን በመለገስ በቴክኖሎጂ በመታገዝ ልጅ መውለድ እንዲቻል እንዲፈቅድ በረቂቅ ሕጉ ተካቶ የነበረው አንቀጽ እንዲወጣ ተደርጓል።

ለጤና፣ ማኅበራዊና ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቶ ውይይት ሲደረግበት በነበረው ረቂቅ አዋጅ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና አገልግሎት የሚፈቅደው ድንጋጌ እንዲወጣ ተጠይቆ ነበር።

ድንጋጌው እንዲወጣ ያደረገው " ልጅ እንዲኖረው የፈለገ ምን ይሁን ? " ለሚለው ጥያቄ፣ የጉዲፈቻ ልጅ በበቂ ሁኔታ የሚገኝ መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ተነጋግሮበት በመወሰኑ ነው።

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ታደለ ቡራቃ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" ድንጋጌው ከረቂቁ እንዲወጣ የተደረገው ወላጆች ልጅ ለመውለድ ያላቸውን ፍላጎት ሳይሆን፣ ሕግ አውጪው የሚወለዱ ልጆች የማኅበረሰብ ቀውስ እዳያጋጥማቸው በማሰብ፣ ከእምነትና ከማኅበረሰብ መስተጋብር ጋር የተጣጣመ ሕግ መውጣት እንዳለበት ታስቦ ነው።

በተጨማሪም ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚጋጭ ድንጋጌ ማውጣት ስለማይፈቀድ ነው።

ለተጋቢ ባለትዳሮች ፍላጎት ሲባል ይህ ሕግ ወጥቶ የሚወለደውን ሕፃን መብት መጋፋት አያስፈልግም።

ይሁን እንጂ የፀደቀው ሕግ በጋብቻ የተጣመሩ ባለትዳሮች ያለ ልገሳ የራሳቸውን የዘር ፍሬ ብቻ በመውሰድ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና ማግኘት እንዲችሉ ፈቅዷል " ብለዋል።

ለፓርላማ ቀርቦ የነበረው ረቂቅ ሕግ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥነ ተዋልዶ ሕክምና አገልግሎት ተጠቃሚዎች፣ በሕጋዊ ጋብቻ የተጣመሩ ወይም ተፈጥሮአዊ በሆነ መንገድ ልጅ መውለድ የማይችሉ መሆናቸው በዘርፉ ባለሙያ ሲረጋገጥ እንደሆነ ይል ነበር፡፡

የምክር ቤት አባላት የዘር ፍሬን በሕጉ ከተፈቀደው ውጪ አሳልፎ የሰጠ አካል ከተገኘ በወንጀል ሕግ ተጠያቂ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

#tikvahethiopia
🔽🚨🚨🚨
🔴Attorney and Legal Consultant
ጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 4
በቻይና ያለው እጅግ ሀብታም ሰው "ሙዝ እና ገንዘብን በዝንጀሮ ፊት ብታስቀምጡ ዝንጀሮዎች ሙዙን ይመርጣሉ ምክንያቱም ገንዘብ ብዙ ሙዝ ሊገዛ እንደሚችል ስለማያውቁ ነው, እንዲያውም ሥራን እና ንግድን ለሰዎች ብታቀርቡ. መስራትን ይመርጣሉ ምክንያቱም አብዛኛው ሰው ቢዝነስ ከደመወዝ የበለጠ ገንዘብ እንደሚያስገኝ ስለማያውቅ ነው።
ብዙዎች ድሀ ከሚሆኑባቸው ምክንያቶች አንዱ የንግድ ሥራ እውቅና ባለማግኘታቸው ነው። በትምህርት ቤት ውስጥ ብዙ ጊዜ ያሳልፉ እንጅ ስለ ቢዝነስ እና ትርፉ የማወቅ እድል የላቸውም። በትምህርት ቤት ውስጥ የሚማሩት ለራሳቸው ከመስራት ይልቅ ለደሞዝ መሥራት ነው, ምክንያቱም ቢዝነስ ከደመወዝ ይሻላል, ቢዝነስ እድል ትርፍ ሊያስገኝልዎት ይችላል። mere google translation📲

The richest man in China said: "If you put bananas and money in front of monkeys, the monkeys will choose the bananas because they don’t know that money can buy many bananas. In fact, if you offer WORK and BUSINESS to people, they will choose to WORK because most people don’t know that a BUSINESS can generate more MONEY than a salary. One of the reasons why the poor are poor is because they are not trained to recognize business opportunities. They spend a lot of time in school, and what they learn in school is to work for a salary instead of working for themselves. Profits are better than salaries because salaries can allow you to make a living, but profits can generate you a fortune.

Welcome to Mikias Melak & Associates Law Office

🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 4
<<ሊገባን ይገባል አሁን እየተፋፈርን ስለሆነ ነው እንጂ ማንም ኑሮን እየተቋቋመው (Afford) እያደረገ አይደለም፡፡ከሁለትና ሦስት ዓመት በፊት 10 እና 15 ሺህ ደመወዝ የሚያገኙት ሠራተኞች ጥሩ ነበሩ፡፡አሁን ግን 30 ሺህ እና 40 ሺህ ብር ደመወዝ የሚያገኙት ጥሩ ደረጃ ላይ ናቸው አልልም፡፡ የቤት ኪራይ:የትምህርት ቤት ክፍያው:የኑሮ ውድነት ሰማይ ወጥቷል::>>

አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ
ለሪፖርተር ጋዜጣ ከሰጠው ቃለምልልስ የተወሰደ
January 5
የስራ_ማስታወቂያ_ዕጩ_ዳኛ_እና_ዐቃቤ_ሕግ.pdf
753 KB
ማስታወቂያ

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፍትሕ ባለሙያዎች ማሠልጠኛና የሕግ ምርምር ኢንስቲትዩት በክልሉ ሥር በሚገኙ ወረዳዎች ዳኛ ወይም ዐቃቤ-ሕግ ሆኖ ለመሥራት ለሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች ያወጣው ማስታወቂያ

ብዛት፡- 300
የመመዝገቢያ ጊዜ፡- ከታኅሳስ 30 እስከ ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም
January 7
Losing a top performer will cost far more than retaining them.
Pay people what they're worth.
January 7
በሀሰተኛ ዲግሪ ተቀጥሮ በዋና ስራ አስኪያጅነት ሲሰራ የነበረ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ!!
 
በሀሰተኛ ዲግሪ ተቀጥሮ በዋና ስራ አስኪያጅነት ሲሰራ የነበረ ግለሰብ በተከሰሰበት የሙስና ወንጀል ድርጊት በእስራት እና በገንዘብ እንዲቀጣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ወሰነ።

ተከሳሹ የማይገባ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ አዲስ ፋና ጠቅላላ ሸቀጣ ሸቀጥና ሆቴሎች ንግድ አክሲዮን ማህበር በሕዳር 6 ቀን 2012 ዓ.ም ባወጣው ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ ተከሳሽ ለውድድር ሲመዘገብ ተገቢው የትምህርት ዝግጅት እንደሌለው እያወቀና ይህንኑ ሁኔታ በመሰወር ማለትም በሐምሌ 25 ቀን 2001 ዓ.ም በዲግሪ መርሐ-ግብር ከአልፋ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው በማስመሰል ሰነዱን ለድርጅቱ ማቅረቡ ተጠቅሷል።

ከጥር 18 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በድርጅቱ የንግድ መምሪያ ስራ አስኪያጅ በመሆን እንዲሁም ከሚያዚያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 29 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ደግሞ የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆኖ በመስራት በአጠቃላይ የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ክፍያ ብር 715 ሺህ 190 ብር እንዲከፈለው በማድረግ በተጠቀሰው የገንዘብ ልክ ጥቅም ያገኘ መሆኑ ተመላክቶ በከባድ ማታለል የሙስና ወንጀል ተከሷል፡፡ፍርድ ቤቱ ማስረጃዎችን መርምሮና አመዛዝኖ በተከሳሹ ላይ የጥፋተኛ ፍርድ በመስጠት እንዲሁም የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሹን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ110 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
ኢትዮ-መረጃ

🔽🚨🚨🚨
🔴Attorney and Legal Consultant
ጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 8
ውሸት ለማናገር ቀላል ነች፣💎
እውነት ግን ለሚናገሩት ሆነ ለሚሰሙት ከባድ ነው
💎📸💎
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 9
Asset Recovery draft proc. Amharic from COM to HPR.pdf
1.1 MB
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንብረት ማስመለስ አዋጅ

በወንጀልና በሙስና የተፈራ ንብረት የማስመለስ  አዋጅ ጸደቀ
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው14ኛ መደበኛ ስብሰባው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል።

አዋጁ በሕገ-ወጥ መንገድ የተፈራን ንብረት ማስመለስ የሚያስችሉና የሕግ-ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዕጸገነት መንግስቱ በረቂቅ አዋጁ የተደረጉ ማስተካከያዎችና የተጨመሩ አንቀጾችን አስመልክተው ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በአዋጁ ላይ በአስረጅ፣ በህዝብና የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ግብዓት እንደሰበሰበ ገልጸዋል።

የንብረት ማስመለስ አዋጅ የመንግስትና የህዝብ ንብረትን ለማስመለስ የነበረውን የሕግ ክፍተት የሚሞላ እንደሆነ አስረድተዋል።

አዋጁ ዜጎች በላባቸውና በወዛቸው ንብረት እንዲያፈሩ የሚያበረታታ፣ በወንጀል ንብረት የሚያፈሩትን ተጠያቂ የሚያደርግ፣ የአገርን ዕድገት የሚያሳልጥ እንደሆነ አስተያየት የሰጡ የምክር ቤት አባላት አንስተዋል።

ግለሰቦች በወንጀልና በሙስና ያፈሩትን ንብረት የሚያስመልስ በመሆኑ በተፈጻሚነቱ ላይ ጥንቃቄ ማድረግና አስፈጻሚ አካላትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ እና የዜጎችን ንብረት የማፍራት መብት እንዳይጋፋ መታየት አለባቸው ያሏቸውን ጉዳዮች አንስተዋል።     

የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዕጸገነት መንግስቱ በአዋጁ ሃብት የማፍራትና የማውረስ ሕገ-መንግስታዊ መብትን የሚቃረን ድንጋጌ አለመካተቱንም አብራርተዋል።

የጸረ-ሙስና ትግል እንዲጠናከር የሚያደርግ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘና የተመዘበረ የአገር ሃብትን ለማስመለስ የሚያስችልና ሕገ-ወጥነትን የሚያስቆም አዋጅ እንደሆነም ጨምረዋል።

ምክር ቤቱ በአዋጁ አስፈላጊነትና ወቅታዊነት ላይ ዝርዝር ውይይት በማድረግ በ ሶሰት ተቃውሞ እና በአራት  ድምጸ  ታቅቦ  በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።
https://www.alehig.com/federal-democratic-republic-of-ethiopia-property-recovery-proclamation-approved/
January 9
የሚስትን የልደት ቀን መርሳት ያስቀጣል…
🔥🆕🚨
የዓለም ሀገራት የሚመሩበት እና የሚተዳደሩበት ሕግ አላቸው። አንዳንድ ሕጎች ግን አስገራሚ ናቸው። የሚከተሉት ሀገራት ሕጎች ደግሞ ከተለመደው ወጣ ካሉት መካከል ይጠቀሳሉ።


🚫 የሚስትን የልደት ቀን መርሳት

#ሳሞኣ በምትባል ደሴት ሀገር የሚስትን የልደት ቀን መርሳት ወንጀል ነው። በሀገሪቱ ሕግ ባል የሚስቱን ልደት ከረሳና ሚስትም ለፖሊስ ቅሬታ ካቀረበች ባል ከቅጣት አይድንም። ባል ለመጀመርያ ጊዜ ከሆነ የረሳው ከፖሊስ የቃል ማስጠንቀቂያ ይደርሰዋል። ነገር ግን በድጋሚ ከረሳ በእስራት የሚያስቀጣው ወንጀል ይሆናል።

🚫 ለልጅ በሕግ ያልተፈቀደ ስም ማውጣት

#አይስላንድ ሀገር ልጅ ስድስት ወር ሳይሞላው ስም ሊሰጠው ይገባል። የሚሰጠው ስም በሕግ የተመዘገበ አይስላንዳዊ ስም መሆን ይጠበቅበታል። ይህም በሕግ ይረጋገጣል። ስም መስጠትን በተመለከተ በሀገሪቱ ልዩ የሕግ ድንጋጌ ተፈጻሚ ይሆናል።

ለህጻኑ በብሔራዊ የሰዎች መዝገብ ላይ ያልተዘረዘረ ስም እንዲሰጠው ከተፈለገ፣ ስሙን ለማጽደቅ ለግል ስሞች ኮሚቴ ማመልከቻ ማቅረብ ይጠበቃል። ከዚያ በፊት ያልተመዘገበ አዲስ ስም እንደመሆኑ መጠን ለማስመዝገብም ተገቢውን ክፍያ መፈጸም ግዴታ ነው።

🚫 የቆሸሸ መኪና መንዳት

#ሩሲያ ውስጥ የቆሸሸ መኪና እየነዱ ከተያዙ ፖሊስ እርስዎን ለመቅጣት አያቅማም። ስለዚህ እስከ 2 ሺህ የሩሲያ ሩብል ቅጣት ለመክፈል ዝግጁ መሆን ይጠበቅቦታል። ከማሽከርከርዎ በፊት ማሳጠብ ግድ ነው። ይህ ሕግ በሩሲያ ብቻ ሳይሆን በፊሊፒንስ እና ቤላሩስ ተግባራዊ ይደረጋል።

🚫 ፓርላማ ውስጥ መሞት

#እንግሊዝ ፓርላማ ውስጥ መሞት የተከለከለ ነው፡፡ የፓርላማ አባላትን ጨምሮ በንጉሣዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ የሞተ ሰው ብሔራዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት የማግኘት መብት አለው የሚል አፈ ታሪክ በመኖሩ በዚያ መሞት ፈጽሞ የተከለከለ ነው። ስለዚህ ወደ እንግሊዝ ፓርላማ የሚገቡበት አጋጣሚ ካለ ስለ ሙሉ ጤንነትዎ እርግጠኛ ይሁኑ። ጥሩ ስሜት ካልተሰማዎት በጭራሽ ወደዛ አይጠጉ።

🚫 ማስቲካ መሸጥ እና ማኘክ

#በሲንጋፖር ለሕክምና ዓላማ ካልሆነ በስተቀር ማስቲካ መሸጥም ሆነ ማኘክ ሕገወጥ ነው። የሲጋራ ቁራጮች፣ የከረሜላ መጠቅለያዎችንም ሆነ ሌሎች መሰል ቆሻሻዎችን መጣልም የሚያሥቀጡ ተግባራት ናቸው። በትንሹ ከ500 ዶላር ያላነሰ ክፍያ ያስቀጣሉ። እንደ ድርጊቱ ተደጋጋሚነትም ቅጣቱ ይጨምራል።

🚫 በምሽት ማፏጨት

#በቱርክ በምሽት ማፏጨት የተከለከለ ነው። ይህም በድሮ ጊዜ በምሽት ማፏጨት ክፉ መንፈስ ይጠራል ተብሎ ስለሚታሰብ የወጣ ሕግ ቢሆንም አሁን ላይ በምሽት የድምጽ ብክለት እንዳይኖር ይረዳል በሚል እስካሁን ጥቅም ላይ ይውላል።
#FANA
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 11
#እንድታውቁት

ከተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክን ለመቆጣጠር የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ

ከፖሊስ በተሽከርካሪ ላይ የደረሰውን የጉዳት አይነት የሚገልጽ የፅሁፍ ማስረጃ ሳይቀበሉ ጥገና የሚያከናውኑ ጋራዦች / የጋራዥ ባለቤቶች / በወንጀል ህግ የሚጠየቁት እንዳለ ሆኑ የ20 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልባቸዋል።

አመታዊ የተሽከርካሪ ምርመራ ያላደረገ የተሽከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ ያሽከረከረ ማንኛውም ሰው 5,000 ብር ይቀጣል።

  የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖረው ተሽከርካሪ በማሽከርከር በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው 7000 ብር ይቀጣል።

ከባለቤትነት ወይም በይዞታው የተያዘውን ተሽከርካሪ የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለሌላው ሰው አሳልፎ የሰጠ ማንኛውም የተሸከርካሪ ባለንብረት 3,000 ብር ይቀጣል።

🚨የትራፊክ ግጭት ወይም ጉዳት አድርሶ በቦታው ላይ ያልቆመ ወይም ባደረሰው የትራፊክ ጉዳት የተጎዳውን እና ሕክምና የሚያስፈልገውን ሰው ወደ ህክምና በመውሰድ እንዲታከም ያላደረገ 👉 በወንጀል ህጉ መሰረት ይጠየቃል።

ወጣት አሽከርካሪዎች፣ ጀማሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ፣ የንግድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እና አደገኛ ጭነት የጫኑ አሽከርካሪዎች የአልኮል መጠን በትንፋሽ በየትኛውም መጠን ከተገኘ 2,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ታግዶበት ሳለ ያሽከረከረ 3,000 ብር ቅጣት ይጣልበታል።

አልኮል መጠን በትንፋሽ ውስጥ ፦
🍻 0.24 እስከ 0.6 ሚሊግራም/ሊትር 1,500 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.61 እስከ 0.8 ሚሊግራም /ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 0.81 እስከ 1.0 ሚሊግራም/ሊትር 2,000 ብር ያስቀጣል።
🍻 1.0 ሚሊግራም/ሊትር በላይ የተገኘበት 3,000 ብር ይቀጣል።

በተሽከርካሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ አካል የጨመረ ወይም ከተፈቀደለት ወንበር ውጭ ተጨማሪ ወንበር ወይም መቀመጫ የጨመረ የተሽከርካሪ ባለንብረት 400 ብር ይቀጣል።

የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሞተር እየሰራና በተሽከርካሪው ውስጥ መንገደኞች እያሉ ነዳጅ መሙላት 1,500 ብር ያስቅጣል።

ቴሌቪዥን ወይም ሌሎች ምስሎችን ተሽከርካሪ ውስጥ እየተመለከተ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የደህንነት ቀበቶ ሳያስር ወይም ተሳፋሪዎች የደህንነት ቀበቶ ማሰራቸውን ሳያረጋግጥ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተንቀሳቃሽ ስልክ በእጁ ይዞ እያነጋገረ፣ ወይም መልዕክት እየጻፈ እየላከ ወይም እያነበበ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ጫት ቅሞ ወይም እየቃመ ወይም አደንዛዥ ዕፅ ወስዶ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

የተሽከርካሪ የፊት ወይም የኃላ ሰሌዳ ሳይኖረው ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ለአውቶብስ ብቻ ተብሎ በተለየ መንገድ ላይ ያሽከረከረ 1,500 ብር ይቀጣል።

ቀይ መብራት የጣሰ 1,500 ብር ይቀጣል።

የትራፊክ ተቆጣጣሪ ትዕዛዝ ያልፈጸመ፣ ወይም የተሳሳተ መረጃ የሰጠ ወይም እንዲቆም ሲታዘዝ በእንቢተኝነት ሳይቆም የሄደ 1,000 ብር ይቀጣል።

የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ኖሮት ሳይዝ ያሽከረከረ ወይም የአሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱን ሳያሳድስ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከተፈቀደው ፍጥናት በታች ያሽከረከረ ወይም የቀኙን ጠርዝ ሳይዝ በዝግታ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

ከመጠን በላይ ድምጽ እያሰማ ወይም የጆሮ ማዳመጫ እያዳመጠ ያሽከረከረ 1,000 ብር ይቀጣል።

መንገድ ላይ ያለን ውሃ በተሽከርካሪው አማካኝነት እግረኛ ላይ እንዲረጭ ያደረገ 1,000 ብር ይቀጣል።

(ተጨማሪ የጥፋት ዝርዝር እና ቅጣቶቹን ከላይ ያንብቡ)
#tikvahethiopia
🔴Attorney and Legal Consultant
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ

We are delighted to connect with you! You can easily reach us through the following platforms to stay informed and access our legal services:

Website & Social Media
Linktree:📱📱📱📱📱📱📱📱  

              https://linktr.ee/alehig

📱Facebook:
https://www.facebook.com/AlehigOfficial/

📱Telegram Channel:⭐️
https://t.me/AleHig

🌐 📱📱📱📱Website: alehig.com


Direct Contact🔈⬇️✉️

📱WhatsApp: ✉️ +251920666595
📱Telegram:  ✉️ @MikiasMelak


Our Commitment
alehig.com
📊አለሕግ🔽
🔠🔠🔠    🔠🔠🔠
Alternative Legal Enlightenment & Services
🔼⭐️
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት


We provide expert legal advice, support, and resources on various laws, proclamations, regulations, and directives to empower and guide you.

Feel free to reach out anytime‼️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
January 12