African Leadership Excellence Academy
2.13K subscribers
2.38K photos
89 videos
6 files
104 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
#አሁን
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በፓን አፍሪካን ወጣቶች ጉባኤ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ማብራሪያ እየሰጡ ነው።
#አሁን
********
#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የ100 ቀናት ሳምንታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እየተደረገ ነው::
የዘርፍ ሀላፊዎችና ዳይሬክተሮች በሳምንቱ ውስጥ ያከናወኗቸው ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች እየቀረቡ ነው::
#አሁን #happening now

#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ አመራርና ባለሙያዎች ስለ #ኢ- ላይብረሪ #በአሜሪካ_ኤምባሲ ገለፃ እየተደረገላቸው ነው::

ገለፃው አካዳሚው እና ኤምባሲው በጋራ ለመስራት በተስማሙት መሰረት በዩ ኤስ የኢ- ላይብረሪ ዳታ ቤዝ ውስጥ የሚገኙ በርካታ መፅሀፍትን ለአመራር ልማት ፕሮግራም እና ለጥናትና ምርምር ስራዎች ለመጠቀም የሚያስችል ነው::

ከአካዳሚው የመጡ ሰላሳ አመራሮች እና ባለሙያዎች #በዩ_ኤስ_ኤምባሲ ውስጥ ስለ ኢ- ላይብረሪ አጠቃቀም ገለፃ እየተደረገላቸው ይገኛል::
#አሁን
#Happening_now

#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ፕሬዚደንት #ዛዲግ_አብርሃ በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተዘጋጀው የመጀመሪያው የአፍሪካ ከተሞች ፎረም ላይ ተገኝተው The Future of Urban Leadership በሚል ርዕስ ፅሁፍ እያቀረቡ ነው::

የመጀመሪያው የአፍሪካ ከተሞች ፎረም "ዘላቂ የከተሞች ልማት ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ 2063" በሚል መሪ ኃሳብ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ የአድዋ መታሰቢያ መካሄድ ጀምሯል።

በፎረሙ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ ከ47 በላይ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ከተሞች ከንቲባዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣ ተመራማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ለተከታታይ ሶስት ቀናት በሚካሄደው አህጉራዊ ፎረም በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም እና #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ የኢትዮጵያ ከተሞች ተሞክሯቸውን በማጋራት ከአቻ የአፍሪካ ከተሞች የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበት ይሆናል።
#አሁን
#Happening_now

#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ እና #የከተማ_እና_መሰረተ_ልማት_ሚኒስቴር
በጋራ ያዘጋጁት የተተኪ ወጣቶች ስልጠና #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ እየተሰጠ ነው::
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ #ወንድዬ_ለገሰ (ዶ/ር) በስልጠናው መክፈቻ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት አካዳሚው የወጣቶችን አቅም ለመገንባት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው ወጣቶች የወደፊት አገር ተረካቢ መሆናቸውን ተገንዝበው የመሪነት አቅማቸውን በሚያሳድጉ ተግባራት ውስጥ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ተናግረዋል::

ስልጠናው የአፍሪካን የወደፊት የከተማ አመራር ማብቃት (Future urban leaders for Africa) በሚል እየተሰጠ ሲሆን ተሳታፊዎቹም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት: ከተለያዩ ሲቪል ማህበራት: መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የተውጣጡ አንድ መቶ ወጣቶች እየተሳተፉ ነው::

በዘርፉ ልምድ ያላቸው ከፍተኛ አመራሮችና ሙሁራንና ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን ያካበቱትን ልምድና የህይወት ተሞክሮ ለውጣቶቹ አካፍለዋል::

#የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚን የሪፎርም: ማስፋትና ሽግግር ፕሮግራም #በእሸቴ_አበበ (ዶ/ር) ቀርቧል::
#Happening_Now
#አሁን
"አንድ ሃገር ሲያድግ በአካባቢው ላሉትም የማድግ እድል እና መነሳሳት እንደሚፈጥር የአውሮፓ እና የሩቅ ምስራቅ ሃገራት የዕድገት ጉዞ ማሳያ ነው፣ የኢትዮጵያ እድገት ለአፍሪካ ቀንድ አልፎም ለመላው አፍሪካ የብልጽግና ጉዞ መጀመሪያ መሆን ይችላል።" ዛዲግ አብርሃ
የአፍሌክስ ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ እና የሀገራችንን የብልፅግና ምስጢሮች በተመለከተ ለኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን አመራሮች በአካዳሜው የአመራር ልማት ማዕከል ስልጠና እየሰጡ ነው።
Just now ·
#Happening_Now!!!
#አሁን!
"የሰው ልጅ ትክክለኛ ውሳኔ መወሰን ከፈለገ ራሱን ማወቅ፣ የሰው ልጅ ተፈጥሮን መረዳት ይጠበቅበታል" ዛዲግ አብርሃ
👉የሰውን ልጅ ትክክክለኛ ውሳኔ የመስጠት አቅም ከሚቀንሱት ነገሮች አንዱ ኮግኒቲቨ ባያዝ ይባላል❗️
👉ኮግኒቲቨ ባያዝ ምንድነው
🔹ስሜታዊነት
🔹ማህበረሰባዊ ተጽዕኖ
🔹ደመነፍሳዊነት
🔹ልማድ
🔹ሌሎች፣ ሌሎች ጉዳዮች በውሳኔ ሰጪነታችን ላይ ያላቸው ተጽዕኖ ምን ይመስላል
የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ስነ
-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥን በተመለከተ ለገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች ስልጠና እየሰጡ ነው።