African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.54K photos
96 videos
6 files
119 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
🌍 Unlocking Africa's Best Potentials Through AFLEX 🌍

Africa, and Ethiopia in particular, hold vast untapped potential across many areas—politics, economics, culture, intellectual advancements, and natural resources. For far too long, these strengths have been locked away, underutilized and overlooked. But now, it’s time for a change.

AFLEX will play a pivotal role in unleashing Africa’s hidden greatness. Here’s how:
👍2
🔓 Unlocking through Research
AFLEX will conduct cutting-edge research to discover Africa’s most promising strengths and opportunities in politics, economics, and culture. This research will fuel new strategies for growth and development, putting Africa on the path to success.

💡 Generating Ideas
At AFLEX, we’ll bring together thought leaders, scholars, policy makers, and innovators to exchange ideas and generate fresh perspectives. Through collaboration, we will unlock breakthrough solutions to Africa’s challenges and pave the way for a brighter future.

📢 Sharing Knowledge
AFLEX will make sure these ideas and findings are shared and acted upon. By hosting forums, workshops, and continent-wide conferences, we’ll connect African leaders, the private sector, and civil society to collaborate and turn these ideas into reality. These platforms will ensure that Africa’s untapped potential is no longer ignored, but fully leveraged for progress.

It’s time for Africa to step into its full power—AFLEX will lead the way, ensuring our continent’s political, economic, cultural, and intellectual assets are unlocked for a stronger, more united Africa. 🌍

#AFLEX #UnlockingPotential #AfricanExcellence #ResearchAndDevelopment #LeadershipForAfrica #Ethiopia #ContinentalCollaboration
👍16
"ኢትዮጵያን ለማበልፀግ ጠንካራ የተቋማት ግንባታ ወሳኝ ነው"

------ ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ -----

(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 09 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ ኢትዮጵያን ለማበልፀግ ጠንካራ የተቋማት ግንባታ ወሳኝ መሆኑን የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ አስገንዝበዋል።

ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ለኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመሮችና አባላት ዛሬ ለሶስተኛ ቀን በቀጠለው ስልጠና "ተቋማዊ ግንባታ፤ ለሀገር እመርታ" በሚል ርዕስ ገለፃ እያደረጉ ነው።

ክቡር አቶ ዛዲግ በገለፃቸው ሀገራችን ከብዙ አመታት በፊት የዲሞክራሲ መገለጫ የሆነውን የገዳ ስርዓትን እና ወታደራዊ መዋቅሮችን ጨምሮ ሌሎች ተቋማትን የመገንባት ጅምሮ ቢኖራትም እስከመጨረሻው ድረስ ባለመዝለቁ ሀገራችንን ማሳደግ አልቻልንም ብለዋል።

ስለሆነም ይህ ትውልድ ኢትዮጵያን ለማሳደግ ጠንካራ ተቋማትን በመገንባት ረገድ ጀምሮ እስከ ማጠናቀቅ ድረስ ረጅም ርቀትን በቁርጠኝነት ሊሄድ እንደሚገባ አሳስበዋል።
👍15
ስለሆነም በቀጣይ ምክር ቤቱም ሆነ የምክር ቤት አባላት ከስልጠናው የሚገኘውን ዕውቀት፣ ልምድና ተሞክሮ በመቅሰም፣ ከተቋማት ጋር በመቀናጀትና ተናቦ በመስራት፣ እንዲሁም የሚሰጡ ቀጣይ ሀገራዊ አቅጣጫዎችን በአግባቡ በመያዝ ሀገራችንን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ዘርፎች በማጠናከር ወደተሻለ ከፍታና ብልጽግና የማሸጋገር ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት መወጣት ይጠበቅብናል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ‹‹የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት›› የሚለው አለማቀፋዊ፣ አህጉራዊና ሀገራዊ ጥቅል የሆነ ሀሳብን የያዘ በመሆኑ የነበራቸውን ግንዛቤ ይበልጥ እንዳሳደገላቸው ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም ዛሬ ላይ አደጉ የሚባሉት ሀገሮች የራሳቸውን ህልም አስቀምጠው እንዳሳኩ ሁሉ ሀገራችንም ወደ ብልፅግና የሚሻግራት ህልም ማስቀመጥ በመቻሏ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ያገኙት ይህ ህልም ዕውን እንዲሆንም ለመራጭ ህዝባቸው በአግባቡ በማስገንዘብ ሀሳቡ እንዲሰርጽ ማድረግ እና በክትትልና ቁጥጥር ስራቸው ውስጥ በማካተት እንዲሰሩም ሰልጣኝ የምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል፡፡

የተሰጡንን ሀገራዊ ተልዕኮዎችን በአግባቡ በመወጣት፣ ከግጭት እና ከፅንፈኝነት አመላከት በመውጣት፣ ችግሮቻችንን በጋራ በመፍታት እንዲሁም ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር ሀገራችንን ወደተሻለ ከፍታ ማሻገር ይጠበቅብናልም ነው ያሉት፡፡

በመጨረሻም ሰልጣኝ የምክር ቤት አባላት #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ በቀጣይም በሚሰጡ የስልጠና ርዕሶች ላይም በአግባቡ እንዲሳተፉና የተሻለ ዕውቀትና ግንዛቤ እንይዛለን ብለው እንደሚጠብቁም ገልጸዋል፡፡

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
👍11
#በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ የሚሰጠው
ስልጠናው ምክር ቤቱ እና የምክር ቤት አባላት የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን እንደሚፈጥር ተመላከተ
--------------------
(ዜና ፓርላማ)ጥቅምት 09 ቀን ፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ለምክር ቤቱ አመራሮችና አባላት እየተሰጠ የሚገኘው ስልጠና ምክር ቤቱ እና የምክር ቤት አባላት የተጣለባቸውን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችል ትልቅ አቅምን እንደሚፈጥር የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አመላክተዋል፡፡

ስልጠናው ምክር ቤቱና የምክር ቤት አባላት ሀገራችንን ከወቅታዊ አለምዓቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር በማገናዘብ በህገ-መንግስቱ የተሰጠንን የህግ አወጣጥ፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የህዝብ ውክልና ስራችንን በሙሉ አቅምና ብቃት ለመወጣት ያስችላል ብለዋል፡፡

የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አክለውም ስልጠናው ሀገራችን በተጨባጭ እያስመዘገበች ያለውን እመርታ፣ ያጋጠሟትን ተግዳሮቶችን እና እነዚህን ተግዳሮቶች በአንድነት በመቆምና በትብብር መንፈስ በጋራ በመስራት መወጣት እንደሚቻል ያሳየም ነው ብለዋል፡፡

ከለውጡ ወዲህ በሀገራችን ብዙ ማሻሻያዎች ተደርገዋል፤ ሰፋፊ ስራዎች ተሰርተዋል ያሉት የምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እኛም እንደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና እንደ ምክር ቤት አባል ተሳትፏችን የጎላ ነበር ሲሉ አብራርተዋል፡፡
👍15
የጋራ ትርክት ሀገራዊ ህልምን ዕውን ለማድረግ አጋዥ መሆኑን አቶ #ዛዲግ_አብርሐ ገለፁ
--------------------------
(ዜና ፓርላማ) ጥቅምት 08 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ሱሉልታ፤ የኢትዮጵያን ህልም ዕውን ለማድረግ የጋራ ትርክት መፍጠር አስፈላጊና አጋዥ ነው ሲሉ #የአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ_ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሐ ገለፁ።

ክቡር አቶ ዛዲግ ይህን የገለፁት #"የትርክት_እመርታ_ከታሪካዊ_ስብራት_ወደ_ሀገራዊ_ምልአት" በሚል ርዕስ በሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በተሰጠው የሥልጠና ርዕስ ጉዳይ ላይ ለኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና ከፍተኛ አመራሮች ማጠቃለያ በሰጡበት ወቅት ነው።

ክቡር አቶ ዛዲግ ከተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት #የኢትዮጵያ ታሪክ አጻጻፍ ላይ በሚነሱ አንዳንድ ክፍተቶች ምክንያት የጋራ ታሪክና የወል ትርክቶች መፍጠር አለመቻሉን ገልፀዋል ።

በመሆኑም እነዚህ አሉ የሚባሉ የታሪክ አተራረክ ክፍተቶችን በማረቅ ከነጠላ ትርክት ይልቅ አሰባሳቢና የጋራ የሆነ ትርክት መፍጠር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
👍16
የታሪክ አለመግባባቶች አሉ ማለት ግን ሁሉንም ታሪኮች አሽቀንጥሮ መጣልና ትክክለኛ ያልሆኑ ታሪኮች መነሻ በማድረግ ወደ ግጭት መግባት ማለት አለመሆኑን የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ ጥሩ ጥሩ ታሪኮችን መቀበልና ከተዛቡ ታሪኮች ደግሞ ትምህርት መውሰድ ያስፈልጋልም ነው ያሉት።

የታሪክ አለመግባባት በሚኖርበት ሁኔታ #የጋራ_ትርክትን ለመፍጠር እንደችግር የሚታይ እንደሆነ የገለፁት ክቡር አቶ ዛዲግ፤ ዋናው ጉዳይ ግን በእውነት ላይ ያልተመረኮዙና በምናብ በተፈጠሩ ታሪኮች ሳቢያ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች ለመከላከል የጋራ እውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት መገንባት ይገባል ብለዋል። በታሪክ የተነሳ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችንም በቀጣይ ለመቅረፍ እንደ ሀገራዊ የምክክር መድረኮች የመሳሰሉ ዕድሎች መፍትሔ እንደሚሆኑም አመላክተዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ህልም ዕውን ይሆን ዘንድም የጋራ እና አሰባሳቢ የሆነ ትርክትን መፍጠርና በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ሁሉም አካል የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንዳለበት እና የምክር ቤት አባላት በዚህ ረገድ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

(በኃይለሚካኤል አረጋኸኝ)
👍15