ET Securities
655 subscribers
578 photos
7 videos
28 files
290 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
በዛሬዉ ነሐሴ 1፣ 2016 የውጭ ምንዛሬ ገበያ

ለዋናዎቹ የውጭ ገንዘቦች የቀረበውን ከፍተኛ የባንኮች የመግዣ እና ዝቅተኛ የመሸጫ ዋጋ ተመልከቱ

ለአንድ የአሜሪካ ዶላር 🇺🇸 💵
ከፍተኛ የመግዣ ዋጋ 107.3307 * ገዳ ባንክ
ዝቅተኛ የመሸጫ ዋጋ 99.3676 * ግሎባል ባንክ

ለአንድ ፓውንድ 🇬🇧 💷
ከፍተኛ የመግዣ ዋጋ ብር 100.6943 * ህብረት ባንክ
ዝቅተኛ የመሸጫ ዋጋ ብር 118.0187 *ኮፐሬቲቭ ባንክ

ለአንድ ዮሮ🇪🇺 💶
ከፍተኛ የመግዣ ዋጋ ብር 112.5636 * ፀሐይ ባንክ
ዝቅተኛ የመሸጫ ዋጋ ብር 108.1216 * ግሎባል ባንክ

~~
Today, August 07, 2024, the foreign exchange market

Look at the high bank bid and low bid rates for major foreign currencies

For one US dollar 🇺🇸 💵
Maximum purchase price ETB 107.3307 * Geda Bank
Minimum selling price ETB 99.3676 * Global Bank

For one Pound 🇬🇧 💷
Maximum purchase price ETB 100.6943 * Hibret Bank
Minimum selling price ETB 118.0187 *Cooperative Bank

For one Euro🇪🇺 💶
Maximum purchase price ETB 112.5636 * Tsehay Bank
Minimum selling price ETB 108.1216 * Global Bank


www.condoaddis.com/240807-2
#News የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የልዩ የዉጭ ምንዛሪ ጨረታን በአማካይ ዋጋ በዶላር 107.9 ብር መሆኑን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. የተካሄደውን የልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል።

27 ባንኮች ተሳትፎዉበታል በተባለዉ በዚህ ልዩ ጨረታ አሸናፊ የሆኑት ተጫራቾች አማካይ ዋጋ በአንድ ዶላር 107.9 ብር እንደሆነ ብሔራዊ ባንክ ገልጿል። ይህም ነገ ከነሐሴ 2፤2016 ዓ.ም. ጀምሮ በዉጪ ምንዛሪ ተመን ላይ ተግባራዊ ይደረጋሉ ።

የብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ ዉጤቱን ተከትሎ እንደተናገሩት "ተግባራዊ የተደረገዉን በባንክ ምንዛሪ ዋጋ እና በትይዩ የገበያ ዋጋ መካከል ያለው ልዩነት እና እንዲሁም የምንዛሪ ተመን መረጋጋት ትርጉም ያለው እድገት ሆኖ በማየታችን ደስተኞች" ነን ብለዋል።

የዉጪ ምንዛሪ ግብይት አብዛኛው እንቅስቃሴ ወደ ባንክ ሥርዓት እንዲሸጋገር የሚያደርግ ሲሆን በዚህም የውጭ ምንዛሪ የሚያመጡትን ላኪዎች እንዲሁም ብዙ ኩባንያዎችን እና የውጭ ምንዛሪ ለሚፈልጉ ሥራ ፈጣሪዎች አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተመልክቷል ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የዉጪ ምንዛሪ ጨረታዉን ከዛሬ ጀምሮ ሊያካሄድ መሆኑን መግለፁ የሚታወስ ሲሆን ቢዘህም ፍላጎቱ ያላቸዉ ባንኮች በጨረታው መሳተፍ እንደሚችሉ አስታዉቆ ነበር።


#News The National Bank of Ethiopia has announced a special foreign currency auction with an average price of 107.9 Birr per dollar.

National Bank of Ethiopia today, August 1, 2016.  He announced the results of the special foreign exchange auction.

According to the National Bank, the average price of the winning bidders in this special auction is 107.9 Birr per dollar.  This is from tomorrow, August 2, 2016.  They will be applied on the foreign exchange rate.

Following the results, National Bank Governor Mamo Mehretu said, "We are happy to see the difference between the bank exchange rate and the parallel market rate, as well as the stability of the exchange rate, as a meaningful development."

He observed that most of the foreign exchange trading activity is transferred to the banking system, thus contributing to the exporters who bring foreign currency as well as many companies and entrepreneurs who need foreign currency.

It should be remembered that the National Bank of Ethiopia announced that it will hold a special foreign exchange auction from today, and it announced that interested banks can participate in the auction.

www.condoaddis.com/240807-1
#ECMA
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያን ባለስልጣን ሃና ተኸልኩን ዋና ዳይሬክተር አድርጎ ሾመ!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያን ባለስልጣን ሃና ተኸልኩን ዋና ዳይሬክተር አድርጎ ሲሾም በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ብሩክ ታዬን (ዶ/ር) ዋና ስራ አስፈፃሚ አድርጎ ተቀብሏል

ላለፉት ሁለት ዓመታት የካፒታል ገበያ ባለስልጣንን ከማቋቋም ጀምሮ በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ በነበሩት ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) ምትክ በህግ እና በኢኮኖሚያዊ ወንጀሎች ላይ ሰፊ ልምድ ያላቸውን ሃና ተኸልኩን አዲሱ ዳይሬክተር አድርጎ መቀበሉን አስታዉቋል ።

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የመጀመሪያ እና የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ብሩክ ታዬ ( ዶ/ር) በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዉ መሾማቸው ተሰምቷል።

ብሩክ ታዬ የኢትዮጵያ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ 27 የሚደርሱ የመንግስት ኩባንያዎችን የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግን ላለፉት ሁለት ዓመታት በስራ አስፈፃሚነት በመሩት አብዱረህማን ኢድ ጣሂር ምትክ መሾማቸው ለማወቅ ተችሏል ።

Please follow and like us:
Fb.me/etstocks
X.com/etstocks1
YouTube.com/@etstocks
Website:- condoaddis.com/category/etstocks
#CBE #USD
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዶላር ዋጋ ጨመረ።

ባለፉት 5 ተከታታይ ቀናት ለውጥ የሌለበት የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ይፋ ሲያደርግ ነበር።

ዛሬ ግን በሁሉም የውጭ ምንዛሬ ዋጋዎች ላይ ጭማሪ አደርጓል።
የአሜሪካ ዶላር መግዣው 101 ብር ከ0041 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 111 ብር ከ1045 ሳንቲም ገብቷል።

#GBP
ፓውንድ ስተርሊግ መግዣው 122 ብር ከ6543 ሳንቲም ፤ መሸጫው 134 ብር ከ9197 ሳንቲም ሆኗል።

#Euro
ዩሮ መግዣው 110 ብር ከ2157 ሳንቲም ፤ መሸጫው ወደ 121 ብር ከ2372 ሳንቲም ጨምሯል።

#KWE
አንዱ የኩዌት ዲናር መግዣው 314 ብር ከ4020 ሳንቲም መሸጫው ደግሞ 345 ብር ከ8421 ሳንቲም ገብቷል።

Condoaddis.com/240809-2
#NBE #FOREX
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮ ለመከፈት የሚፈልጉ የሥራ ፈቃድ መስጠት መጀመሩን አስታዉቋል

በገበያ ላይ ተመሥርተው የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ መሸጥና መግዛት የሚፈልጉ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች እንዲቋቋሙ በተፈቀደው መሠረት ብሔራዊ ባንክ ይህኑ ፍቃድ መስጠት ጀምሬያለሁ ብሏል።

የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች መቋቋም የውጭ ምንዛሪ ገበያን መሠረት ለማስፋትና ለማጠናከር እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ ለመሸጥም ሆነ ለመግዛት የሚሹ ደንበኞችን ፍላጎት ለማሳካት እንደሚረዳ ይታመናል ብሏል ባንኩ ባወጣዉ መግለጫ ።

የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች እንዲከፈቱ የሥራ ፈቃድ መስጠት መጀመሩን የገለፀው ባንኩ ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ለመክፈትና ዘርፉን በቀጣይ ዓመታት ተወዳዳሪ ለማድረግ የተጀመርነው አዲስ ምዕራፍ መሆኑ ገልጿል።

Condoaddis.com/240809-3
#Afdp #DashenBank
የአፍሪካ ልማት ባንክ ቡድን ዳይሬክተሮች ቦርድ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ የመጀመሪያ የሆነውን ለዓለም አቀፍ ንግድ ልውውጥ ዋስትና የሚውል 40 ሚሊዮን ዶላር ለዳሸን ባንክ አፅድቋል።

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ ባንካችን የአፍሪካ ልማት ባንክ ያስቀምጣቸውን ጥብቅ ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላቱ ይህ 40 ሚሊዮን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ልውውጥ ዋስትና ማዕቀፍ በመፈቀዱ በጣም ደስተኞች ነን። ይህም ባንካችን በክፍለ አህጉሩና ከዚያም ባለፈ የንግድ አገልግሎታችንን ለማሳደግ በጣም  አስፈላጊ ድጋፍ ነው ብለዋል።

ይህን  ድጋፍ ለማግኘት ያሟላቸው ቅድመ ሁኔታዎች እና በሂደቱ የተገኙ የልምድ ልውውጦች ዳሸን ባንክ ከአፍሪካ ተመራጭ እና ቀዳሚ ባንኮች ተርታ ለመሰለፍ ያለውን ራዕይ ዕውን ለማድረግ እንደ ግብአት እንደሚጠቅም አመልክተዋል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ ዳይሬክተር ጀነራል ኔና ኑዋቡፎ በበኩላቸው የአፍሪካን ንግድ መደገፍ ባንካችን ተቀዳሚ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ይህም የአህጉሩን የኢኮኖሚ ዕድገት ለመጨመርና ድንበር ዘለል ንግድ ለማሳደግ ወሳኝ ሚና አለው ብለዋል።

ባንኩ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ያገኘው ይህ የድጋፍ ማዕቀፍ ባንኩ በዓለም አቀፍ ንግድ ልውውጥ ያለውን ተቀባይነት እና ተመራጭነት ይበልጥ እንደሚያሳድገው ተመልክቷል።

የፋይናንስ አቅርቦቱ ዳሸን ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች አገር በቀል ድርጅቶች ምርት ለመላክና ለማስመጣት የሚፈልጉትን አቅርቦትና ዋስትና እንዲያገኙ ዕድል እንደሚፈጥር ተገልጿል።

የገንዘብ አቅርቦቱ ለኢትዮጵያ በጣም አስፈላጊ የሆኑ እንደ ማዳበሪያ፣መድሃኒት፣የሶላር ሃይል ማመንጫ፣የግብርና ማሽነሪዎችና ሌሎች ምርቶችን ለማስገባት ያግዛል።

Condoaddis.com/240809-4
#Forex #NBE
የውጭ ምንዛሬ (Forex) ቢሮ ፍቃድ ለማውጣት መስፈርቶች!

ነፃ የውጭ ምንዛሪ ቢሮ (In dependent Forex Bureau) የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ ኖቶችን #በመግዛትና #በመሸጥ ላይ ብቻ የሚሰማራ እንጂ በሌላ የባንክ ሥራ ላይ መሰማራት የለበትም።

1. በማንኛውም ህጋዊ መንገድ የተቋቋመ፣ በኢትዮጵያዊ ዜጋ፣ ነዋሪ ያልሆነ ኢትዮጵያዊ እና/ወይም ትውልደ ኢትዮጵያዊ የውጭ ዜጋ የሆነ የተቋቋመ የንግድ ድርጅት፤

2. ዝቅተኛውን የብር 15 ሚሊዮን ካፒታል አሟልቷል እናም 30 ሚሊዮን ብር የደህንነት ማስያዣ በተዘጋ አካውንት (ወለድ ሊያስገኝ ይችላል) በማንኛውም ባንክ ማቅረብ የሚችል፤

3. የደህንነት ማስያዣ ተቀማጭ ገንዘብ ፊት ዋጋ በገለልተኛ Forex ቢሮ ለሁለት ዓመታት ከቀጠለ አገልግሎት ይለቀቃል፤

4. የውጭ ምንዛሬ (Forex) ቢሮን ንግድ ለመፈፀም በሁሉም ረገድ ተስማሚ የሆነ እና ብሔራዊ ባንክ እንደ ባንክ ላሉ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ያስቀመጠውን የደህንነት እና የደህንነት መስፈርቶችን የሚያሟላ፤

5. የውጭ ምንዛሬ (Forex) ቢሮ አድራሻን የሚያመለክት የስም ሰሌዳ፤

6. የውሸት ማስታወሻዎችን ለመለየት አስፈላጊ መሳሪያ መያዝ፤

7. የውጭ ምንዛሬ (Forex) ቢሮ ሰራተኞችን ስም ዝርዝር እና ስያሜ መስጠት፤

8. የውጭ ምንዛሬ (Forex) ቢሮ ሰራተኞች የማጭበርበር ፣የማታለል እና የሙስና መዝገብ የሌላቸው ታማኝ ፣ታማኝነት እና ብቃት ያላቸው ሰዎች መሆናቸውን ማረጋገጥ፤

9. በማንኛውም የውጭ ምንዛሬ (Forex) ቢሮ ሳይት የሚገኘውን ከፍተኛውን የገንዘብ መጠን ለመሸፈን በቂ ኢንሹራንስ መግዛቱን ያረጋገጡ።

Condoaddis.com/240810-1