#የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የጠቅላላ ጉባዔ እና የስራ አስፈጻሚ አባላትን መረጠ፣፣
ሰመራ፣ ሐምሌ11፣ 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የጠቅላላ ጉባዔ እና የስራ አስፈጻሚ አባላትን መረጠ።
ጠቅላላ ጉባዔው ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋን በፕሬዚዳንትነት፣ ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲሁም ሸኽ ሀሚድ ሙሳን በዋና ፀሐፊነት መርጧል።
በጉባኤው እንደተገለፀው፥ ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቋማዊ ለውጥና አንድነት አገር አቀፍ ጉባዔ የተመረጠው ኮሚቴ በስድስት ወራት ውስጥ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ አመራሮችን እንዲያስመርጥ ኅላፊነት ቢሰጠውም ኅላፊነቱን ሳይወጣ ለሶስት ዓመት ከስድስት ወር ቆይቷል።
በወቅቱ የተመረጠው ኮሚቴ ኅላፊነቱን ባለመወጣቱ ጉዳዩ ወደ መደበኛው ጉባዔ እንዲመጣ በተወሰነው መሰረት ዛሬ ለሁለተኛ ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ተወካዮች በተገኙበት መካሄዱ ነው የተገለፀው።
በጉባኤው ላይ በድምፅ ይሳተፋሉ ተብለው ከሚጠበቁት 300 ተሳታፊዎች መካከል 261ዱ ተገኝተዋል።
ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በተካሄደው ጉባኤ ከተሳተፉት መካከል 39ኙ በሞት፣ በህመም፣ ከሀጂ ጉዞ ባለመመለስና በልዩ ልዩ ምክንያቶች በዛሬው ጉባኤ አለመገኘታቸውም ታውቋል።
ጉባዔውን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የኅይማኖት አባቶች ስለምርጫው ሂደቱ ማብራሪያና የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በጉባዔው ምርጫ ከመካሄዱ ቀደም ብሎ የምርጫ መስፈርቶች ለጉባዔው በንባብ ቀርበዋል።
በዛሬው ጉባዔ መጂሊሱን ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የሚመሩ አመራሮች ምርጫ ተካሂዶ የሚከተሉት 14 ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ተመርጠዋል።
1. ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ
2. ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን
3. ሸኽ አልመርዲ ዐብዱላሂ
4. ሸኽ ሀሚድ ሙሳን
5. ሸኽ እድሪስ ዓሊይ ሁሴን
6. ሸኽ አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌ
7. ሸኽ መሀመድ አህመድ ያሲን
8. ሸኽ አሚን ኢብሮ
9. ኢንጂኔር አንዋር ሙስጠፋ
10. ሸኽ አብዱልሃሚድ አህመድ
11. ሀጂ ሙስጠፋ ናስር
12. ሸኽ ዛኪር ኢብራሂም
13. ሸኽ ሁሴን ሀሰን
14. ሸኽ መሀመድ አሚን ሰይድ
ከስራ አስፈጻሚ አባላቱ መካከልም ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋን በፕሬዚዳንትነት፣ ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲሁም ሸኽ ሀሚድ ሙሳን በዋና ፀሐፊነት መምረጡን ነው የኢዜአ ዘገባ የሚያመለክተው።
ተመራጩ ፕሬዚዳንት ሸኽ ኢብራሂም ቱፋ ባስተላለፉት መልዕክት ምርጫው ከየትኛውም አካል ጣልቃገብነት በጸዳ አግባብ በነጻነት ታሪካዊ ምርጫ እንደሆነ ተናግረዋል።
ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ታላቅ ኅላፊነት የተሰጣቸው መሆኑን የገለጹት ሸኽ ኢብራሂም ቱፋ፥ በተለይም የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት በማስጠበቅ ረገድ በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋገጠዋል።
ህዝበ ሙስሊሙም ከጎናቸው እንዲቆም እና በጸሎት እንዲያግዛቸውም ነው ጥሪ ያቀረቡት።
የምርጫው ታዛቢዎች በበኩላችው ምርጫው ገለልተኛ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ ታሪካዊና ትክክለኛ ምርጫ ሂደት እንደነበር ገልጸዋል።
#FBC
ሰመራ፣ ሐምሌ11፣ 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የጠቅላላ ጉባዔ እና የስራ አስፈጻሚ አባላትን መረጠ።
ጠቅላላ ጉባዔው ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋን በፕሬዚዳንትነት፣ ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲሁም ሸኽ ሀሚድ ሙሳን በዋና ፀሐፊነት መርጧል።
በጉባኤው እንደተገለፀው፥ ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቋማዊ ለውጥና አንድነት አገር አቀፍ ጉባዔ የተመረጠው ኮሚቴ በስድስት ወራት ውስጥ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ አመራሮችን እንዲያስመርጥ ኅላፊነት ቢሰጠውም ኅላፊነቱን ሳይወጣ ለሶስት ዓመት ከስድስት ወር ቆይቷል።
በወቅቱ የተመረጠው ኮሚቴ ኅላፊነቱን ባለመወጣቱ ጉዳዩ ወደ መደበኛው ጉባዔ እንዲመጣ በተወሰነው መሰረት ዛሬ ለሁለተኛ ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ተወካዮች በተገኙበት መካሄዱ ነው የተገለፀው።
በጉባኤው ላይ በድምፅ ይሳተፋሉ ተብለው ከሚጠበቁት 300 ተሳታፊዎች መካከል 261ዱ ተገኝተዋል።
ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በተካሄደው ጉባኤ ከተሳተፉት መካከል 39ኙ በሞት፣ በህመም፣ ከሀጂ ጉዞ ባለመመለስና በልዩ ልዩ ምክንያቶች በዛሬው ጉባኤ አለመገኘታቸውም ታውቋል።
ጉባዔውን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የኅይማኖት አባቶች ስለምርጫው ሂደቱ ማብራሪያና የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በጉባዔው ምርጫ ከመካሄዱ ቀደም ብሎ የምርጫ መስፈርቶች ለጉባዔው በንባብ ቀርበዋል።
በዛሬው ጉባዔ መጂሊሱን ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የሚመሩ አመራሮች ምርጫ ተካሂዶ የሚከተሉት 14 ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ተመርጠዋል።
1. ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ
2. ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን
3. ሸኽ አልመርዲ ዐብዱላሂ
4. ሸኽ ሀሚድ ሙሳን
5. ሸኽ እድሪስ ዓሊይ ሁሴን
6. ሸኽ አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌ
7. ሸኽ መሀመድ አህመድ ያሲን
8. ሸኽ አሚን ኢብሮ
9. ኢንጂኔር አንዋር ሙስጠፋ
10. ሸኽ አብዱልሃሚድ አህመድ
11. ሀጂ ሙስጠፋ ናስር
12. ሸኽ ዛኪር ኢብራሂም
13. ሸኽ ሁሴን ሀሰን
14. ሸኽ መሀመድ አሚን ሰይድ
ከስራ አስፈጻሚ አባላቱ መካከልም ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋን በፕሬዚዳንትነት፣ ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲሁም ሸኽ ሀሚድ ሙሳን በዋና ፀሐፊነት መምረጡን ነው የኢዜአ ዘገባ የሚያመለክተው።
ተመራጩ ፕሬዚዳንት ሸኽ ኢብራሂም ቱፋ ባስተላለፉት መልዕክት ምርጫው ከየትኛውም አካል ጣልቃገብነት በጸዳ አግባብ በነጻነት ታሪካዊ ምርጫ እንደሆነ ተናግረዋል።
ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ታላቅ ኅላፊነት የተሰጣቸው መሆኑን የገለጹት ሸኽ ኢብራሂም ቱፋ፥ በተለይም የህዝበ ሙስሊሙን አንድነት በማስጠበቅ ረገድ በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋገጠዋል።
ህዝበ ሙስሊሙም ከጎናቸው እንዲቆም እና በጸሎት እንዲያግዛቸውም ነው ጥሪ ያቀረቡት።
የምርጫው ታዛቢዎች በበኩላችው ምርጫው ገለልተኛ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሂደትን የተከተለ ታሪካዊና ትክክለኛ ምርጫ ሂደት እንደነበር ገልጸዋል።
#FBC
#Gabbí Rasih Caddol Parti Kee Doolat Ekraaroh Kusaqay Awaash Subac Kiiloh Magaalal Gexsitak Suge Yumurruqe
Samara-Ditelik 12, 2014 (AFMMA)
Gabbí Rasih Caddol Parti Kee Doolat Ekraaroh Kusaqay Awaash Subac Kiiloh Magaalal Gexsitak Suge Yumuruqe
Sanat 2014 Ligidak Parti Kee Doolat Abnissoh Ekraaroh Kusaaqay Gabbí Rasih Caddol Rasu Kee Daqoorit Miraaciini Edde Yengele Qidi Kee amô qidi fanteena abeh yan baar le kusaqay Gexsitak Suge Yumurruqe.
Tá Kusaaqih Ellacabol "Qabala Yaceenim Rooci Wadu" itta itrol Miraaciini Qabala Yeceenimih taama Kee Agat Caddol Qimbinteh Tan Anxaxin Ratih Tadeera Arac Xagutuh Awash Subac Kiilok, Naama Lee-fanak Fayya Le Caddoh Barittoh Buxaal Coox Dabisen.
#QafárTV
Samara-Ditelik 12, 2014 (AFMMA)
Gabbí Rasih Caddol Parti Kee Doolat Ekraaroh Kusaqay Awaash Subac Kiiloh Magaalal Gexsitak Suge Yumuruqe
Sanat 2014 Ligidak Parti Kee Doolat Abnissoh Ekraaroh Kusaaqay Gabbí Rasih Caddol Rasu Kee Daqoorit Miraaciini Edde Yengele Qidi Kee amô qidi fanteena abeh yan baar le kusaqay Gexsitak Suge Yumurruqe.
Tá Kusaaqih Ellacabol "Qabala Yaceenim Rooci Wadu" itta itrol Miraaciini Qabala Yeceenimih taama Kee Agat Caddol Qimbinteh Tan Anxaxin Ratih Tadeera Arac Xagutuh Awash Subac Kiilok, Naama Lee-fanak Fayya Le Caddoh Barittoh Buxaal Coox Dabisen.
#QafárTV
#የሚዲያና ኮሙኒኬሽን የቀውስ ጊዜ ዘገባና የመረጃ ስርአት በጥንቃቄ መመራት ይኖርበታል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ሰመራ-ነሃሴ 22/2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ተቋማት የቀውስ ጊዜ ዘገባና የመረጃ ተደራሽነት ብሄራዊ ጥቅምን ታሳቢ ያደረገና በጥንቃቄ የሚመራ ሊሆን እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አሳሰበ።
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የፌዴራልና የክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቋል።
ጉባዔው የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፣ የፌዴራልና የክልል የኮሙኒኬሽን ዘርፎች የ2014 በጀት ዓመት የስራ አፈጸጻምና የ2015 ዕቅድ ላይ ተወያይቷል።
የመንግስት ኮሙኒኬሸን የቀጣይ 5 ዓመታት ረቂቅ ስትራቴጂ ሰነድ እንደሁም በመንግስት ኮሙኒኬሸንና የክልል የዘርፉ መዋቅሮች የስራ ግንኙንት ላይ በተዘጋጀ የመግባቢያ ሰነድ ላይም መክሯል።
የክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት በፌዴራል መንግስት የሚገለጹ መረጃዎችን የሚለቁበት አግባብ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋለት እንደሚገባም በጉባኤው ተመልክቷል።
የክልል የኮሙኒኬሸን መዋቅሮች ያልተናበቡ መረጃዎችን ከመስጠት እንዲቆጠቡና ፈቃድ ያልተሰጣቸው ሚዲያዎች በመንግስት ሁነቶች ላይ የሚሳተፉበት ዕድልም ሊስተካከል ይገባል ነው ያሉት።
በተለይ አገር ቀውስ ሲገጥማት የሚዲያና ኮሙኒኬሸን ዘርፉ ላይ ያለው የመረጃ ፍሰት ጥንቃቄ ይሻል ብለዋል።
የክልል ሚዲያዎች ከክልላቸው ባሻገር ወደ ሌሎችም ክልሎች ተደራሽነታቸውን በማስፋት በአገራዊ መግባባትና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ጠቅሰዋል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ፤ ለአገርና ህዝብ ጥቅም ሲባል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ እንዲጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።
የአዘጋገብና መረጃ አሰጣጥ ሂደት ፈጣንና በዘመነ መልኩ ከወቅቱ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች እንደየ ዐውዱ እየተቃኘ መራመድ ይኖርበታልም ነው ያሉት።
ጠንካራ ኮሙኒኬሽን ስርዓት ለመገንባት የሚያስችል የኮሙኒኬሽን ፖሊሲና ስትራቴጂ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
የክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት በተቀናጀ አገራዊ አጀንዳ እየተናበቡ መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው በተናጠል አጀንዳ ቀርጾ ማስተጋባት የለባቸውም ብለዋል።
በመሆኑም በፌዴራል መንግስት በኩል ሊሰራጩ የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ መረጃ ከመስጠት ሊቆጠቡ ይገባል ነው ያሉት።
በተለይም የቀውስ ጊዜ የኮሙኒኬሽን ስራ ልዩ ትኩረት ይሻል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ጉዳዩ ከሚመለከተው አገራዊ ተቋምና ኮሚቴ በስተቀር ከጦርነት ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ማሰራጨት አይችሉም ነው ያሉት።
በእንዲህ አይነት ወቅት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች የአገርን ብሔራዊ ጥቅም ታሳቢ ባደረገ መልኩ መመራት አለባቸው ብለዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለፃ የቀውስ ጊዜ አዘጋገብ መመሪያዎች የተዘጋጁ በመሆኑ በቀጣይ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል።
የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ደሲሳ፤ የህዝብ መረጃ የማግኘት መብት መገደብ ስለሌበት ተቋማት በየወቅቱ ለሚዲያዎች መረጃ መስጠት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
በተቋማት ላይ ጠንካራ የምርመራ ጋዜጠኝነት እንዲሰራ የመንግስት ጽኑ ፍላጎት መሆኑን ጠቅሰው ከወዲሁ ግልጽ መረጃ ለመስጠት መዘጋጀት አለባቸው ነው ያሉት።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትም ከክልሎች ጋር ደረጃውን በጠበቀና ወጥነት ባለው አግባብ ተናቦ እንደሚሰራ ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ሰመራ-ነሃሴ 22/2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ተቋማት የቀውስ ጊዜ ዘገባና የመረጃ ተደራሽነት ብሄራዊ ጥቅምን ታሳቢ ያደረገና በጥንቃቄ የሚመራ ሊሆን እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አሳሰበ።
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የፌዴራልና የክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቋል።
ጉባዔው የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፣ የፌዴራልና የክልል የኮሙኒኬሽን ዘርፎች የ2014 በጀት ዓመት የስራ አፈጸጻምና የ2015 ዕቅድ ላይ ተወያይቷል።
የመንግስት ኮሙኒኬሸን የቀጣይ 5 ዓመታት ረቂቅ ስትራቴጂ ሰነድ እንደሁም በመንግስት ኮሙኒኬሸንና የክልል የዘርፉ መዋቅሮች የስራ ግንኙንት ላይ በተዘጋጀ የመግባቢያ ሰነድ ላይም መክሯል።
የክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት በፌዴራል መንግስት የሚገለጹ መረጃዎችን የሚለቁበት አግባብ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋለት እንደሚገባም በጉባኤው ተመልክቷል።
የክልል የኮሙኒኬሸን መዋቅሮች ያልተናበቡ መረጃዎችን ከመስጠት እንዲቆጠቡና ፈቃድ ያልተሰጣቸው ሚዲያዎች በመንግስት ሁነቶች ላይ የሚሳተፉበት ዕድልም ሊስተካከል ይገባል ነው ያሉት።
በተለይ አገር ቀውስ ሲገጥማት የሚዲያና ኮሙኒኬሸን ዘርፉ ላይ ያለው የመረጃ ፍሰት ጥንቃቄ ይሻል ብለዋል።
የክልል ሚዲያዎች ከክልላቸው ባሻገር ወደ ሌሎችም ክልሎች ተደራሽነታቸውን በማስፋት በአገራዊ መግባባትና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ጠቅሰዋል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ፤ ለአገርና ህዝብ ጥቅም ሲባል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ እንዲጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።
የአዘጋገብና መረጃ አሰጣጥ ሂደት ፈጣንና በዘመነ መልኩ ከወቅቱ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች እንደየ ዐውዱ እየተቃኘ መራመድ ይኖርበታልም ነው ያሉት።
ጠንካራ ኮሙኒኬሽን ስርዓት ለመገንባት የሚያስችል የኮሙኒኬሽን ፖሊሲና ስትራቴጂ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።
የክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት በተቀናጀ አገራዊ አጀንዳ እየተናበቡ መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው በተናጠል አጀንዳ ቀርጾ ማስተጋባት የለባቸውም ብለዋል።
በመሆኑም በፌዴራል መንግስት በኩል ሊሰራጩ የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ መረጃ ከመስጠት ሊቆጠቡ ይገባል ነው ያሉት።
በተለይም የቀውስ ጊዜ የኮሙኒኬሽን ስራ ልዩ ትኩረት ይሻል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ጉዳዩ ከሚመለከተው አገራዊ ተቋምና ኮሚቴ በስተቀር ከጦርነት ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ማሰራጨት አይችሉም ነው ያሉት።
በእንዲህ አይነት ወቅት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች የአገርን ብሔራዊ ጥቅም ታሳቢ ባደረገ መልኩ መመራት አለባቸው ብለዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለፃ የቀውስ ጊዜ አዘጋገብ መመሪያዎች የተዘጋጁ በመሆኑ በቀጣይ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል።
የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ደሲሳ፤ የህዝብ መረጃ የማግኘት መብት መገደብ ስለሌበት ተቋማት በየወቅቱ ለሚዲያዎች መረጃ መስጠት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
በተቋማት ላይ ጠንካራ የምርመራ ጋዜጠኝነት እንዲሰራ የመንግስት ጽኑ ፍላጎት መሆኑን ጠቅሰው ከወዲሁ ግልጽ መረጃ ለመስጠት መዘጋጀት አለባቸው ነው ያሉት።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትም ከክልሎች ጋር ደረጃውን በጠበቀና ወጥነት ባለው አግባብ ተናቦ እንደሚሰራ ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
#መከላከያ ሠራዊት ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ መሆኑን አስታወቀ፣፣
ሰመራ፣ ነሐሴ 22፣ 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠባቂ በመሆኑ ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
መከላከያ ሠራዊት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ÷ አሸባሪው ህወሓት የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱ፣ “እኔ እየመራሁ የማልዘርፋት ሀገር ትፍረስ” ከሚል እኩይ ተግባሩና ፀረ-ሕዝብ ባህሪው አንፃር የሚጠበቅ ነው ብሏል።
በተቃራኒው እኛ ግን የመላው ከ120 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵውያንን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ተቀብለን የምንፈፅም ሕዝባዊና ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ስለሆንን፥ መላውን ሕዝባችንና የትግራይን ጨቅላ ሕፃናት ከከንቱ እልቂት የመታደግ ሞራላዊና ሕጋዊ ግዴታ አለብን ነው ያለው መከላከያ በመግለጫው፡፡
ህወሓት ያኔ ጥንት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ስልጣኔና የዘመነ ጦር መሳሪያ ባልነበረበት ጊዜ ጦርነትን በሰው ማዕበል ገጥመህ ማሸነፍ ወረት በነረበት ወቅት እንደሚደረገው፥ ከግብረ-ገብ፣ ከሞራልና ሕጋዊነት በእጅጉ በተጣረሰ አኳኋን ገና በሰውነታቸው ያልጠነከሩ ጨቅላና ለጋ ሕፃናትን ከኋላ በኃይል እየገፋ፥ በሚገባ ሰልጥኖ እስከ አፍንጫው ከታጠቀ የመከላከያና ጥምር ኃይል ፊት እያሰለፈ የእሳት እራት አድርጎ በማስፈጀት የሞት ቀኑን ለማዘግየት ታሪክ ይቅር የማይለውን ጭካኔ በገዛ ወገኑ፣ ወገናችን የትግራይ ሕዝብ ላይ እየፈፀመ መሆኑንም ነው የገለጸው፡፡
መከላከያ ሠራዊት በሕግ የተቋቋመ፣ በሕግ የሚመራና በሕዝብ በተመረጠ መንግስት የሚታዘዝ፣ ሲያለማ እደሚሞገስና እንደሚሸለም ሁሉ የተሰጠውን ሕገ መንግስታዊ ተልዕኮ በሚገባ ሳይፈፅም ሲቀርና ሲያበላሽ በሀገሪቱና ዓለም አቀፍ ሕጎች የሚጠየቅና የሚዳኝ ሀገራዊ ኃይል እንደሆነም በመግለጫው አስረድቷል፡፡
ስለሆነም መከላከያ ሠራዊት ሕግን ተከትሎ ወገኑን ከሰቆቃና እልቂት ለመታደግ አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት በጀግንነት በመክፈል፥ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ያስከብራል ነው ያለው መከላከያ ሠራዊት፡፡
የሽብር ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተከፋይ፣ ጉዳይ አስፈፃሚና በወንጀል የሚፈለግ ሕገ-ወጥ ሽፍታ መሆኑን ያመላከተው መከላከያ÷ ቡድኑ የኃላፊነትና የተጠያቂነት መንፈስ የማይሰማው መሆኑን ገልጾ፥ በባህሪው ምክንያት ሊሰማውም እንደማይችል አስረድቷል፡፡
በዚህ ሳቢያም የሽብር ቡድኑ እንደፈለገው የሚዋሽ እና የግፎች ሁሉ ጥግ የሆነ ተግባር በገዛ ወገኑ ላይ የሚፈጽም መሆኑንም ነው ያብራራው፡፡
ስለሆነም መከላከያ ሠራዊት ሕዝባችንን ከዚህ አረመኔ ቡድን ቀንበር ለማላቀቅና ከከንቱ ጭፍጨፋ ለማዳን ለሕዝባችንና ለሀገራችን ይጠቅማል የተባለውን ሁሉ በመስዋዕትነታችን እውን ለማድረግ በከፍተኛ ብቃትና የላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
ሕዝባችንን ከፍጅት ለመታደግ ሲባል፥ መሆን የሚገባውን ሁሉ አጠቃላይ ሁኔታን በማያበላሽ አግባብ ቀጣይም ሊኖር እንደሚችል መታወቅ ይኖርበታል ነው ያለው፡፡
እኛ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት ካለበት የመከላከያ ኃይል በሚጠበቅ አግባብ፣ ሁለንተናዊ በሆነና ነገን አሻግሮ በሚመለከት እሳቤ እንዲሁም በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የምናደርገው እና እናንተ በጋለ ጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት ዛሬ፣ አሁን፣ እዚችው እዲሆን የምትፈልጉትን ሁሉ "አፍ በእጅ በሚያሲዝ" አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ ድል ይታረቃል ሲልም አረጋግጧል፡፡
“ዛሬም ሆነ እስከ ወዲያኛው የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም ለመጉዳት የሚደረግ ከሰማይ በታች ባለ ፈተና ሁሉ እንደማንፈተን ታውቃላችሁ! ታምኑናላችሁም!” ሲል የገለጸው መከላከያ ሠራዊት፥ ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ደህንነት፣ የግዛት አንድነትና ለሀገረ መንግሥቱ ቀጣይነት በመቆም የምንከፍለው መስዋዕትነት ክብርና ኩራታችን ነው ብሏል በመግለጫው፡፡
ሰመራ፣ ነሐሴ 22፣ 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠባቂ በመሆኑ ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
መከላከያ ሠራዊት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ÷ አሸባሪው ህወሓት የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱ፣ “እኔ እየመራሁ የማልዘርፋት ሀገር ትፍረስ” ከሚል እኩይ ተግባሩና ፀረ-ሕዝብ ባህሪው አንፃር የሚጠበቅ ነው ብሏል።
በተቃራኒው እኛ ግን የመላው ከ120 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵውያንን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ተቀብለን የምንፈፅም ሕዝባዊና ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ስለሆንን፥ መላውን ሕዝባችንና የትግራይን ጨቅላ ሕፃናት ከከንቱ እልቂት የመታደግ ሞራላዊና ሕጋዊ ግዴታ አለብን ነው ያለው መከላከያ በመግለጫው፡፡
ህወሓት ያኔ ጥንት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ስልጣኔና የዘመነ ጦር መሳሪያ ባልነበረበት ጊዜ ጦርነትን በሰው ማዕበል ገጥመህ ማሸነፍ ወረት በነረበት ወቅት እንደሚደረገው፥ ከግብረ-ገብ፣ ከሞራልና ሕጋዊነት በእጅጉ በተጣረሰ አኳኋን ገና በሰውነታቸው ያልጠነከሩ ጨቅላና ለጋ ሕፃናትን ከኋላ በኃይል እየገፋ፥ በሚገባ ሰልጥኖ እስከ አፍንጫው ከታጠቀ የመከላከያና ጥምር ኃይል ፊት እያሰለፈ የእሳት እራት አድርጎ በማስፈጀት የሞት ቀኑን ለማዘግየት ታሪክ ይቅር የማይለውን ጭካኔ በገዛ ወገኑ፣ ወገናችን የትግራይ ሕዝብ ላይ እየፈፀመ መሆኑንም ነው የገለጸው፡፡
መከላከያ ሠራዊት በሕግ የተቋቋመ፣ በሕግ የሚመራና በሕዝብ በተመረጠ መንግስት የሚታዘዝ፣ ሲያለማ እደሚሞገስና እንደሚሸለም ሁሉ የተሰጠውን ሕገ መንግስታዊ ተልዕኮ በሚገባ ሳይፈፅም ሲቀርና ሲያበላሽ በሀገሪቱና ዓለም አቀፍ ሕጎች የሚጠየቅና የሚዳኝ ሀገራዊ ኃይል እንደሆነም በመግለጫው አስረድቷል፡፡
ስለሆነም መከላከያ ሠራዊት ሕግን ተከትሎ ወገኑን ከሰቆቃና እልቂት ለመታደግ አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት በጀግንነት በመክፈል፥ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ያስከብራል ነው ያለው መከላከያ ሠራዊት፡፡
የሽብር ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተከፋይ፣ ጉዳይ አስፈፃሚና በወንጀል የሚፈለግ ሕገ-ወጥ ሽፍታ መሆኑን ያመላከተው መከላከያ÷ ቡድኑ የኃላፊነትና የተጠያቂነት መንፈስ የማይሰማው መሆኑን ገልጾ፥ በባህሪው ምክንያት ሊሰማውም እንደማይችል አስረድቷል፡፡
በዚህ ሳቢያም የሽብር ቡድኑ እንደፈለገው የሚዋሽ እና የግፎች ሁሉ ጥግ የሆነ ተግባር በገዛ ወገኑ ላይ የሚፈጽም መሆኑንም ነው ያብራራው፡፡
ስለሆነም መከላከያ ሠራዊት ሕዝባችንን ከዚህ አረመኔ ቡድን ቀንበር ለማላቀቅና ከከንቱ ጭፍጨፋ ለማዳን ለሕዝባችንና ለሀገራችን ይጠቅማል የተባለውን ሁሉ በመስዋዕትነታችን እውን ለማድረግ በከፍተኛ ብቃትና የላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
ሕዝባችንን ከፍጅት ለመታደግ ሲባል፥ መሆን የሚገባውን ሁሉ አጠቃላይ ሁኔታን በማያበላሽ አግባብ ቀጣይም ሊኖር እንደሚችል መታወቅ ይኖርበታል ነው ያለው፡፡
እኛ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት ካለበት የመከላከያ ኃይል በሚጠበቅ አግባብ፣ ሁለንተናዊ በሆነና ነገን አሻግሮ በሚመለከት እሳቤ እንዲሁም በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የምናደርገው እና እናንተ በጋለ ጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት ዛሬ፣ አሁን፣ እዚችው እዲሆን የምትፈልጉትን ሁሉ "አፍ በእጅ በሚያሲዝ" አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ ድል ይታረቃል ሲልም አረጋግጧል፡፡
“ዛሬም ሆነ እስከ ወዲያኛው የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም ለመጉዳት የሚደረግ ከሰማይ በታች ባለ ፈተና ሁሉ እንደማንፈተን ታውቃላችሁ! ታምኑናላችሁም!” ሲል የገለጸው መከላከያ ሠራዊት፥ ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ደህንነት፣ የግዛት አንድነትና ለሀገረ መንግሥቱ ቀጣይነት በመቆም የምንከፍለው መስዋዕትነት ክብርና ኩራታችን ነው ብሏል በመግለጫው፡፡