General Wingate Polytechnic college-Official channel
9.95K subscribers
3.35K photos
43 videos
204 files
196 links
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።

የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Download Telegram
የስልጠና ማስታወቂያ
          
  ለ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን የቀረበ የስልጠና ገጸ በረከት 

አጠቃላይ ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ለማህበራዊ ሚዲያችን ተከታታዮች በሙሉ ይህን የኮደርስ ስልጠና መሳተፍ እንደምትችሉ እያሳወቅን የኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠናን ሲያጠናቅቁ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ባለቤት እንደሚሆኑም ስንነግሮት በሙሉ እምነት ነው::

ስልጠናው የሚሰጠው በኦን ላይን /online/ ሲሆን ስልጠናውን ለመከታተል ኢተርኔት ባለበት ቦታ በላፕቶብ ወይም በእጅ ስልክ /ሞባይል/ በመጠቀም መውሰድ እንደምትችሉ ስናበስር ለእናንተ ቅርብ ሆነን ነው፡፡

የሚሰጡ የስልጠና ዓይነቶች:-
1.ዌብ ፕሮግራሚንግ /web programming/
2.ሞባይል ፕሮግራሚንግ /Mobile programming/
3.ዳታ ሳይንስ /Data science/
4. ሰው ሰራሽ አስተውሎት / Artificial Intelligence/ or AI

ማሳሰቢያ:-  ኦንላይን ስትሞሉ #Institution የሚለው ላይ #General_Wingate_Polytechnic_College ብላችሁ መሙላት ይጠበቅባችኋል።
ለስልጠናው የተመዘገባችሁ ሙሉ ስማችሁንና የተመዘገባችሁበትን ሙያ ለአይሲቲ ዲፓርትመንት ኃላፊ ቢሮ እንድታሳውቁ
ትምህርቱ እድሜ፣ ፆታ እና ቦታ አይገድበውም:: 

    📍 በዚህ ሊንክ   https://ethiocoders.et/

መረጃው የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሲሆን ለተጨማሪ ማብራሪያ የኮሌጁን አይሲቲ /ICT/ ዲፓርትመንት ኃላፊ ቢሮ መጠየቅ ትችላላችሁ ተብላችኋል፡፡
አርብ:- ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ∙ም

#የሺያጭ #ማስታወቂያ

ሀ-ብዬ የቆዳ ምርት ውጤቶች ማምረቻ እና ማከፋፈያ ድርጅት ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ ከወዲሁ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ ድርጅቱ በዓሉን ምክኒያት በማድረግ በጥራትና በውበት የሚያመርታቸውን ፋሽን ጫማዎችና ሌዘር ጃኬቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና በ3 ወር የክፍያ ጊዜ ወስዳችሁ ሽር ብትን በሉ ብሏችኋል፡፡

የሺያጭ ጊዜ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚቆ ሲሆን ቦታውም በሰራተኞች ካፍተሪያ አገልግሎት መግቢያ በር አካባቢ ታገኙናለችሁ ኑና መርጣችሁ ሸምቱ ተብላችኋል፡፡

ሀ-ብዬ የቆዳ ምርት ውጤቶች ማምረቻ እና ማከፋፈያ ድርጅት
ቅዳሜ፡- ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም

               #ማስታወቂያ

  ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና  ለውጪ የተቋማችን አጋር  ማኅበረሰብ በሙሉ

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ እያለ ለበዓል ያደለባቸውን ምርጥ #በሬዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ እንሆ ይላል፡፡

ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመት የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡

ዝም ብሎ በሬ አለ በሬ ብሎ ዝምም አለ። የእኛዎቹ በሬ ብሎ ዝም ናቸው ይላል ጀነራል ዊንጌት የግል ኢንተርፕራይዝ።

እንደ ስማችን ዊን_ጌት የሆኑ ሰንጋዎችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ ይምጡ ለበዓል ይሸምቱ ተብላችኋል።

#አድራሻ፡-   ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
             ስልክ - 0991824160

የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ሰኞ፡- ታህሳስ 28 ቀን 2017 ዓ/ም                                                                                            
‹አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡›› ሉቃ 2፡11

ለኮሌጃችን የክርስትና እምነት ተከታይ ሰራተኞች፣ ሰልጣኞች እና አጋሮቻችን በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ!!

በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የዕድገት እና የበጎነት ይሆን ዘንድ እንመኛለን። መልካም በዓል ይሁንላችሁ፡፡

                   የጀነራል  ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ