አርብ፡- ጳጉሜ 1 ቀን 2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን ሠራተኞች በሙሉ
ነገ ቅዳሜ ማለትም ጳጉሜ 2 ቀን 2016 ዓ.ም የሪፎርም ቀን ሲሆን ዕለቱ ''ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት'' በሚል መሪ ቃል ሁሉም የአዲስ አበባ አስተዳደር መሥሪያ ቤቶች ለተገልጋዮች መደበኛ አገልግሎት ይሰጣሉ።
ስለሆነም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ሁላችሁም የኮሌጃችን ሠራተኞች በነገው ዕለት በመደበኛ ስራችሁ ተገኝታችሁ ስራችሁን እንዲትሰሩ እያሳወቅን የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎትም መኖሩን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ፦ አገልግሎቱ እንደመደበኛው ሰዓት ሲሆን የሰዓት ፊርማውም በጣት አሻራ መሆኑን እንጠቁማለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን ሠራተኞች በሙሉ
ነገ ቅዳሜ ማለትም ጳጉሜ 2 ቀን 2016 ዓ.ም የሪፎርም ቀን ሲሆን ዕለቱ ''ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት'' በሚል መሪ ቃል ሁሉም የአዲስ አበባ አስተዳደር መሥሪያ ቤቶች ለተገልጋዮች መደበኛ አገልግሎት ይሰጣሉ።
ስለሆነም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ሁላችሁም የኮሌጃችን ሠራተኞች በነገው ዕለት በመደበኛ ስራችሁ ተገኝታችሁ ስራችሁን እንዲትሰሩ እያሳወቅን የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎትም መኖሩን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ፦ አገልግሎቱ እንደመደበኛው ሰዓት ሲሆን የሰዓት ፊርማውም በጣት አሻራ መሆኑን እንጠቁማለን።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
አርብ:- ጳጉሜ 1 ቀን 2016 ዓ.ም
የመሻገር ቀን
ዛሬ የመሻገር ቀንን ምክኒያት በማድረግ ‹‹የመሻገር ጥረቶች፤ የአዲስ ብርሃን ወረቶች›› በሚል መሪ ሐሳብ ጳጉሜ 1 ቀንን በትጋት እየሰራን እናስባለን፡፡
መሻገር ከትናንት ወደ ነገ፣ ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከወንዙ ባሻገር ወደ ሌላኛው መንደር፣ ከአንድ ዘመን ወደ ሌላ፣ ከመጥፎ ወደ ጥሩ፣ ከድካም ወደ እረፍት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ወዘተ ነው፡፡
እኛ እንደ ተቋም ባሳለፍነው ጊዜ በርካታ ድንቅና ብርቅ የሆኖ እምርታዊና መሰረታዊ ለውጦችን በማምጣት የላቀ ስኬት አስመዝግበናል፡፡ እነዚህ ተግባራት ደግሞ እንደ ኮሌጅ ለመሻገር ጓጉተን ለመድረስ ቸኩለን ያስመዘገብናቸው አስደናቂ ውጤቶች ናቸው፡፡
ሁላችንም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ለመሻገር በሩቅ ያቀድናቸውን ጭምር በቅርብ ማጠናቀቅ ችለናል፡፡ ለዚህ ስኬት ደግሞ የሁሉም አካል ርብርብ እና ቀና አመለካከት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይህም ይቻላል የሚለውን አቅም አሳይቶናል፡፡
ያለፈው ጊዜ ውጤታማነታችን ለቀጣይ እቅዳችን ስንቅ ለጉዟችን ደግሞ ትጥቅ ስለሆነ መጪው ጊዜ እንደ ግልም ሆነ እንደተቋም የመሻገር ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞታችንን እንገልፃን፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
የመሻገር ቀን
ዛሬ የመሻገር ቀንን ምክኒያት በማድረግ ‹‹የመሻገር ጥረቶች፤ የአዲስ ብርሃን ወረቶች›› በሚል መሪ ሐሳብ ጳጉሜ 1 ቀንን በትጋት እየሰራን እናስባለን፡፡
መሻገር ከትናንት ወደ ነገ፣ ከአሮጌ ወደ አዲስ፣ ከወንዙ ባሻገር ወደ ሌላኛው መንደር፣ ከአንድ ዘመን ወደ ሌላ፣ ከመጥፎ ወደ ጥሩ፣ ከድካም ወደ እረፍት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ወዘተ ነው፡፡
እኛ እንደ ተቋም ባሳለፍነው ጊዜ በርካታ ድንቅና ብርቅ የሆኖ እምርታዊና መሰረታዊ ለውጦችን በማምጣት የላቀ ስኬት አስመዝግበናል፡፡ እነዚህ ተግባራት ደግሞ እንደ ኮሌጅ ለመሻገር ጓጉተን ለመድረስ ቸኩለን ያስመዘገብናቸው አስደናቂ ውጤቶች ናቸው፡፡
ሁላችንም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ለመሻገር በሩቅ ያቀድናቸውን ጭምር በቅርብ ማጠናቀቅ ችለናል፡፡ ለዚህ ስኬት ደግሞ የሁሉም አካል ርብርብ እና ቀና አመለካከት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ይህም ይቻላል የሚለውን አቅም አሳይቶናል፡፡
ያለፈው ጊዜ ውጤታማነታችን ለቀጣይ እቅዳችን ስንቅ ለጉዟችን ደግሞ ትጥቅ ስለሆነ መጪው ጊዜ እንደ ግልም ሆነ እንደተቋም የመሻገር ይሆንልን ዘንድ መልካም ምኞታችንን እንገልፃን፡፡
‹‹በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት››
ዕሁድ፦ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም
ለኮሌጃችን የእስልምና እምነት ተከታይ ሠራተኞች፣ ሠልጣኞች እና አጋሮቻችን በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የነብዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የዕድገት እና የበጎነት ይሆንላችሁ ዘንድ እንመኛለን።
የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ለኮሌጃችን የእስልምና እምነት ተከታይ ሠራተኞች፣ ሠልጣኞች እና አጋሮቻችን በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የነብዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የዕድገት እና የበጎነት ይሆንላችሁ ዘንድ እንመኛለን።
የጀነራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ሐሙስ፡- መስከረም 9 ቀን 2016 ዓ.ም
#ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና ለውጪ የተቋማችን አጋር ማኅበረሰብ በሙሉ
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ያደለባቸውን 9 #በሬዎች በከፍተኛ ጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ አቅዷል፡፡
ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በበሬዎቹ ፎቶ ላይ በተለጠፈው የዋጋ ዝርዝር መሰረት ከፍለው መውሰድ የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡
ለመስቀል በዓል፣ ለተለያዩ ዝግጅቶች ወይም የስጋ አምርዎቶን ቁርጥ ለማድረግ ካሰቡ ወደየትም አይሂዱ፤ የስጋ ፍላግዎቶን ለማርካት እኛ ጋር ኑ አስር ጊዜ ለክተው አንድ ጊዜ ይመርጡናል እንጂ አያወዳድሩንም ይላል የኮሌጁ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ፡፡
ቀንበር ያልተጫነባቸውና ጅራፍ ያላረፈባቸው የእርድ ቅልብ ሰንጋዎቻችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ
#አድራሻ፡- ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
ስልክ - 0991824160
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
#ማስታወቂያ
ለኮሌጃችን የውስጥ ሰራተኞች እና ለውጪ የተቋማችን አጋር ማኅበረሰብ በሙሉ
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ ያደለባቸውን 9 #በሬዎች በከፍተኛ ጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማህበረሰብ ለመሸጥ አቅዷል፡፡
ስለሆነም በተዘጋጀው ጥቂት የመሸጫ ቀናት ውስጥ ፈጥነው በመምጣት የመረጡትን ሰንጋ በበሬዎቹ ፎቶ ላይ በተለጠፈው የዋጋ ዝርዝር መሰረት ከፍለው መውሰድ የሚችሉ መሆኑን ስንገልጽልዎት በታላቅ ደስታ ነው፡፡
ለመስቀል በዓል፣ ለተለያዩ ዝግጅቶች ወይም የስጋ አምርዎቶን ቁርጥ ለማድረግ ካሰቡ ወደየትም አይሂዱ፤ የስጋ ፍላግዎቶን ለማርካት እኛ ጋር ኑ አስር ጊዜ ለክተው አንድ ጊዜ ይመርጡናል እንጂ አያወዳድሩንም ይላል የኮሌጁ ተቋማዊዩ የግል ኢንተርፕራይዝ፡፡
ቀንበር ያልተጫነባቸውና ጅራፍ ያላረፈባቸው የእርድ ቅልብ ሰንጋዎቻችንን መርጠው ለመግዛት ከፈለጉ
#አድራሻ፡- ቦታ - ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ
ስልክ - 0991824160
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ