"የደጋ ሰው"
የየማ የመጀመሪያ አልበም በፈረንሳይ 🇫🇷 ሀገር በሲዲ ታተመ
#Ethiopia | "የደጋ ሰው" የተሰኘው የየማ የመጀመሪያ አልበም በተለያዩ መተግበሪያዎች ከተለቀቀ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንሳይ ሀገር በሲዲ ታተመ።
“በዲጂታል ዘመን ሙዚቃዎቼ ታትመው በእጄ ሳገኛቸው ስሜቱ የተለየ ነው። “ ስትል በማህበራዊ ገፇ የማ አስፍራለች።
በቅርቡ በዩኤስቢ እና በሽክላ የሚታተም ይሆናል።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music #yema #eyuel_mengistu #yedegasew
የየማ የመጀመሪያ አልበም በፈረንሳይ 🇫🇷 ሀገር በሲዲ ታተመ
#Ethiopia | "የደጋ ሰው" የተሰኘው የየማ የመጀመሪያ አልበም በተለያዩ መተግበሪያዎች ከተለቀቀ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በፈረንሳይ ሀገር በሲዲ ታተመ።
“በዲጂታል ዘመን ሙዚቃዎቼ ታትመው በእጄ ሳገኛቸው ስሜቱ የተለየ ነው። “ ስትል በማህበራዊ ገፇ የማ አስፍራለች።
በቅርቡ በዩኤስቢ እና በሽክላ የሚታተም ይሆናል።
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music #yema #eyuel_mengistu #yedegasew
👉« ለህክምና ወደ አሜሪካ ከመጓዙ በፊት ከተፈሪ ጋር በስልክ ተገናኝተን ነበር። አሜሪካም ሆኖ ተደዋውለናል።ለህክምና ቀጠሮ እንደያዘ ነግሮኝ ነበር።ለመጨረሻ ጊዜ ስንገናኝ ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ተለዋውጠናል፡፡»
👉 «ተፈሪን ድራመር ብቻ አድርጎ መውሰድ እሱን ማሳነስ ይሆናል።ተፈሪ እጅግ ሩህሩህ ደግ ለሰው አዛኝ ነው። ይህ በተለምዶ ሰዎች ሲያልፉ የሚባል ሳይሆን የእውነት የኖረበት ስለሆነም ነው፡፡»
👉 «ተፈሪ የሙዚቃ ተመራማሪ፤መምህር፤የሙዚቃ ደራሲ ሲሆን በምርምሩ ረገድ ኢትዮጵያን ከጫፍ ጫፍ ዞሮ ምርምር ያደረገ ሲሆን ውጤቱን ለህዝብ ለማድረስ በተዘጋጀበት ጊዜ ህይወቱ ማለፉ ያስቆጫል፡፡»
👉 «በርግጥም በተቋማት ደረጃ መሰራት የሚገባውን የባህል እሴትን ማጥናት ብሎም መሰነድን ብቻውን ሲያደርግ የነበረ ታላቅ ሰው ነበር፡፡»
👉« ባለፈው ዓመት በወጣው የየማ እና የኔ አልበም ላይ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ተሳትፎ ነበረው።አልበሙ ላይ የመጀመሪያውን ሳንፕል አሰምቼው ወዶታል።በተለይ ሀገረሰብ የሆኑ ስራዎችን መውደዱ እገዛውን ከፍ አድርጎልን ነበር።ከደጋ ሰው አልበምም ሾንቢቴ ለተሰኘው ሙዚቃ ፍቅር ነበረው። ከወጣ በኃላም ''ታዋቂ አደረጋችሁኝ አይደል? " ዕያለ ይቀልድብኝ ነበር»
👉«ተፈሪ በቅርብ ካሳተመው ኦርጂንስ አልበሙ በተጨማሪ በእጁ ብዙ አርካይቮች አሉት።
የሰበሰባቸው ያጠናቸው ብዙ ስራዎች ነበሩት።በቅጂ ደረጃም የጨረሰውን አልበም አንድ ላይ ሰምተነዋል።
ወደፊት ብዙ የሚሰጠን ስራዎች ነበሩ አንድም ህልፈቱ የሚያስቆጨው ይህ በመሆኑ ነው፡፡»
👉 «ድራም ተጫዋቹ፤መምህሩ፤ተመራማሪውን ተፈሪ በቀጥታ በስራም ይሁን በተዘዋዋሪ ስለሚገናኘው፤ ስለሚያውቀው ህልፈቱ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ እድገት ስብራት መሆኑን ተረድቶታል። ይህ በሌሎች ማህበረሰቦች ዘንድ ተመሳሳይ ነው ከተባለ አይደለም። ነገር ግን ተፈሪን ወደፊት የሚረዱ፤ስራዉ ላይ ምርምር የሚደርጉ ሰዎች በቀጣይ ይፈጠራሉ።»
ሲል የሙዚቃ ባለሙያው እዮኤል መንግስቱ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ፕሮግራም ጋር የነበረዉን ቆይታ አጠቃሏል።
ተፈሪ አሰፋ በላስታ ሳውንድ፣ ውዳሴ፣ ኢትዮ-ጃዝ እና ነጋሪት ባንድ በሠራቸው ሥራዎቹ ባህላዊ የኢትዮጵያን ሙዚቃዎች የኢትዮ-ጃዝ መንፈስን በማላበስ በሙዚቃ ዓለም ላይ የማይሻር አሻራ አሳርፏል፡፡
በስቱዲዮም ዘመን አይሽሬ የሙዚቃ ሥራዎችን የሠራ ሲሆን፣ በ2011 ዓ.ም በተካሄደው አዲስ ጃዝ ፌስቲቫል ከቃየን ጋር፣ በ2015 ዓ.ም በተካሄደው አዲስ ጃዝ ፌስቲቫል ደግሞ ከኢትዮጵያን ሪከርድስ ጋር በመሳተፍ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ከፍ አድርጓል፡፡
ሀገር በቀል ሙዚቃዎች ላይ በትኩረት በመሥራት እና የጃዝ የሙዚቃ ስልትን በመጫወት የሚታወቀው ተፈሪ በፖላንድ ሀገር በተለያዩ የሙዚቃ ስልቶች እስከ ሁለተኛ ድግሪ ተምሯል፡፡ ትምህርቱን እንዳጠናቀቀም በሩሲያ፣ በካዛኪስታን፣ በቤላሩስ እና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ሲሠራ ቆይቶ፣ ወደ አሜሪካ በማቅናት አካውንቲንግ በመማር የሙዚቃ ሥራ እስከሚያገኝ ድረስ አካውንታትን ሆኖ ሠርቷል፡፡
በአሜሪካ እያለም ላስታ ሳውንድ የተባለን ባንድ በማቋቋም የመጀመሪያ መድረኩን ከጥላሁን ገሰሰ ጋር የሠራ ሲሆን፣ አልበምም አሳትሟል፡፡
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music #teferi #eyuel_mengistu
👉 «ተፈሪን ድራመር ብቻ አድርጎ መውሰድ እሱን ማሳነስ ይሆናል።ተፈሪ እጅግ ሩህሩህ ደግ ለሰው አዛኝ ነው። ይህ በተለምዶ ሰዎች ሲያልፉ የሚባል ሳይሆን የእውነት የኖረበት ስለሆነም ነው፡፡»
👉 «ተፈሪ የሙዚቃ ተመራማሪ፤መምህር፤የሙዚቃ ደራሲ ሲሆን በምርምሩ ረገድ ኢትዮጵያን ከጫፍ ጫፍ ዞሮ ምርምር ያደረገ ሲሆን ውጤቱን ለህዝብ ለማድረስ በተዘጋጀበት ጊዜ ህይወቱ ማለፉ ያስቆጫል፡፡»
👉 «በርግጥም በተቋማት ደረጃ መሰራት የሚገባውን የባህል እሴትን ማጥናት ብሎም መሰነድን ብቻውን ሲያደርግ የነበረ ታላቅ ሰው ነበር፡፡»
👉« ባለፈው ዓመት በወጣው የየማ እና የኔ አልበም ላይ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ተሳትፎ ነበረው።አልበሙ ላይ የመጀመሪያውን ሳንፕል አሰምቼው ወዶታል።በተለይ ሀገረሰብ የሆኑ ስራዎችን መውደዱ እገዛውን ከፍ አድርጎልን ነበር።ከደጋ ሰው አልበምም ሾንቢቴ ለተሰኘው ሙዚቃ ፍቅር ነበረው። ከወጣ በኃላም ''ታዋቂ አደረጋችሁኝ አይደል? " ዕያለ ይቀልድብኝ ነበር»
👉«ተፈሪ በቅርብ ካሳተመው ኦርጂንስ አልበሙ በተጨማሪ በእጁ ብዙ አርካይቮች አሉት።
የሰበሰባቸው ያጠናቸው ብዙ ስራዎች ነበሩት።በቅጂ ደረጃም የጨረሰውን አልበም አንድ ላይ ሰምተነዋል።
ወደፊት ብዙ የሚሰጠን ስራዎች ነበሩ አንድም ህልፈቱ የሚያስቆጨው ይህ በመሆኑ ነው፡፡»
👉 «ድራም ተጫዋቹ፤መምህሩ፤ተመራማሪውን ተፈሪ በቀጥታ በስራም ይሁን በተዘዋዋሪ ስለሚገናኘው፤ ስለሚያውቀው ህልፈቱ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ እድገት ስብራት መሆኑን ተረድቶታል። ይህ በሌሎች ማህበረሰቦች ዘንድ ተመሳሳይ ነው ከተባለ አይደለም። ነገር ግን ተፈሪን ወደፊት የሚረዱ፤ስራዉ ላይ ምርምር የሚደርጉ ሰዎች በቀጣይ ይፈጠራሉ።»
ሲል የሙዚቃ ባለሙያው እዮኤል መንግስቱ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ፕሮግራም ጋር የነበረዉን ቆይታ አጠቃሏል።
ተፈሪ አሰፋ በላስታ ሳውንድ፣ ውዳሴ፣ ኢትዮ-ጃዝ እና ነጋሪት ባንድ በሠራቸው ሥራዎቹ ባህላዊ የኢትዮጵያን ሙዚቃዎች የኢትዮ-ጃዝ መንፈስን በማላበስ በሙዚቃ ዓለም ላይ የማይሻር አሻራ አሳርፏል፡፡
በስቱዲዮም ዘመን አይሽሬ የሙዚቃ ሥራዎችን የሠራ ሲሆን፣ በ2011 ዓ.ም በተካሄደው አዲስ ጃዝ ፌስቲቫል ከቃየን ጋር፣ በ2015 ዓ.ም በተካሄደው አዲስ ጃዝ ፌስቲቫል ደግሞ ከኢትዮጵያን ሪከርድስ ጋር በመሳተፍ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ከፍ አድርጓል፡፡
ሀገር በቀል ሙዚቃዎች ላይ በትኩረት በመሥራት እና የጃዝ የሙዚቃ ስልትን በመጫወት የሚታወቀው ተፈሪ በፖላንድ ሀገር በተለያዩ የሙዚቃ ስልቶች እስከ ሁለተኛ ድግሪ ተምሯል፡፡ ትምህርቱን እንዳጠናቀቀም በሩሲያ፣ በካዛኪስታን፣ በቤላሩስ እና በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ሲሠራ ቆይቶ፣ ወደ አሜሪካ በማቅናት አካውንቲንግ በመማር የሙዚቃ ሥራ እስከሚያገኝ ድረስ አካውንታትን ሆኖ ሠርቷል፡፡
በአሜሪካ እያለም ላስታ ሳውንድ የተባለን ባንድ በማቋቋም የመጀመሪያ መድረኩን ከጥላሁን ገሰሰ ጋር የሠራ ሲሆን፣ አልበምም አሳትሟል፡፡
Follow us on Social Medias
Youtube - https://www.youtube.com/@waliyaentmt
Facebook - https://www.facebook.com/Waliyaentmt
Tiktok - https://www.tiktok.com/@Waliyaentmt
Telegram - https://t.me/waliyaentmt
#Waliya_Entertainemnt #Music #teferi #eyuel_mengistu