የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በኬንያ ናይሮቢ በተካሄደው የ2025 ዓ.ም (STAT Times International Awards for Excellence in Air Cargo 2025) የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት ልሕቀት ሽልማት መርሀግብር “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ዕውቅና ተቀዳጀ። ከዚህ በተጨማሪም “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት ኤርፖርት” እና “ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ያለ የዓመቱ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ተደራራቢ ዕውቅና እና ሽልማት ተችሮታል።
እነዚህ ሽልማቶች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ላለው ዘርፈ ብዙ ዓለም አቀፍ አገልግሎት አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ማረጋገጫዎች ሲሆኑ፤ የበረራ አድማሳችንን እና አገልግሎታችንን በማጠናከር አህጉራዊ መሪነታችንን እና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነታችንን ለማስቀጠል በዕጅጉ የሚረዱ ናቸው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎ
እነዚህ ሽልማቶች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ላለው ዘርፈ ብዙ ዓለም አቀፍ አገልግሎት አስተማማኝነትና ቅልጥፍና ማረጋገጫዎች ሲሆኑ፤ የበረራ አድማሳችንን እና አገልግሎታችንን በማጠናከር አህጉራዊ መሪነታችንን እና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነታችንን ለማስቀጠል በዕጅጉ የሚረዱ ናቸው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎ
የኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት የህክምና ቁሳቁሶችን በማጓጓዝ እና አጠቃላይ በካርጎ አገልግሎት ዘርፎች ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን የአፍሪካ ምርጥ የፋርማ እቃ ጭነት አገልግሎት አየር መንገድ (Air Cargo Pharma Service of the Year, Africa) እና የአፍሪካ ምርጥ የዕቃ ጭነት አገልግሎት አየር መንገድ (Cargo Airline of the Year, Africa) በመባል ሁለት ሽልማቶች ከ “Aviation Achievement Awards” (AAA) የተበረከተለት መሆኑን ሲገልጽ በደስታ ነው።
እነዚህ ሽልማቶች አየር መንገዳችን ለልህቀት፣ ፈጠራ እና አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለደንበኞች ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላክቱ ሲሆን አየር መንገዳችን ዓለም አቀፍ የዕቃ ጭነት በረራ አድማሱን እያሰፋ መሄዱን ተከትሎ በዓለም ደረጃ ያለውን ተፎካካሪነት አጠናክሮ እንዲቀጥል ያስችለዋል።
አሸናፊዎች እንድንሆን ላበቁን የምንጊዜም አጋሮቻችን እና ታታሪ ሰራተኞቻችን ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። የኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት መዳረሻዎቹንና አገልግሎቶቹን በማስፋፋት የመሪነት ሚናውን ይበልጥ አጠናክሮ ይቀጥላል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎ
እነዚህ ሽልማቶች አየር መንገዳችን ለልህቀት፣ ፈጠራ እና አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለደንበኞች ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላክቱ ሲሆን አየር መንገዳችን ዓለም አቀፍ የዕቃ ጭነት በረራ አድማሱን እያሰፋ መሄዱን ተከትሎ በዓለም ደረጃ ያለውን ተፎካካሪነት አጠናክሮ እንዲቀጥል ያስችለዋል።
አሸናፊዎች እንድንሆን ላበቁን የምንጊዜም አጋሮቻችን እና ታታሪ ሰራተኞቻችን ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። የኢትዮጵያ ካርጎ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት መዳረሻዎቹንና አገልግሎቶቹን በማስፋፋት የመሪነት ሚናውን ይበልጥ አጠናክሮ ይቀጥላል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #የኢትዮጵያካርጎ