የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓመታዊው የሰራተኞች ቀን ክብረ በዓል አካል የሆነው የመድረክ ውይይት በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል ተከናውኗል። በመድረኩም የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ፣ አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ፣ የዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞች እንዲሁም የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ተገኝተዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ዒድ ሙባረክ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ሳምንቱን ሙሉ እየተከበረ የሚገኘው ዓመታዊው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሰራተኞች ቀን ዓለም-አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ በተሠራው የአየር መንገዱ የእግር ኳስ ሜዳ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች፤ እንዲሁም በሁለቱ ተቋማት የወንድ የእግር ኳስ ቡድኖች መካከል በተደረጉ ማራኪ የእግር ኳስ ጨዋታዎች፣ በሰራተኞች መካከል በተደረጉ የአትሌቲክስ ውድድሮች ደምቆ ቀጥሏል። ክብረ በዓሉ በነገው ዕለት በሚደረግ እና 18 ሺ የአየር መንገዱ ሠራተኞች በተጋበዙበት ታላቅ በዓል የሚፈጸም ይሆናል። #የኢትዮጵያአየርመንገድ
በተለያዩ ክብረ በዓላት ሳምንቱን ሙሉ የተከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሰራተኞች ቀን በዛሬው ዕለት 18 ሺ የአየር መንገዱ ሠራተኞች በተጋበዙበት እንዲሁም የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ ሌ/ጄነራል ይልማ መርዳሳ እንዲሁም የቦርድ አባላት፣ የአየርመንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ እንዲሁም ሌሎች የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ አመራሮች በታደሙበት ታላቅ ስነ ስርአት ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ በተሠራው የአየር መንገዱ የእግር ኳስ ሜዳ ተከብሮ ውሏል።
በዝግጅቱ ላይ ከአየር መንገዱ የተለያዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞች ከዋና ስራ አስፈፃሚው እና ከየክፍሎቻቸው ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እጅ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል። በዛሬው
ዕለት የተከናወነው ክብረ በዓል ለአንድ ሳምንት የቆየው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰራተኞች ቀን ክብረ በዓል የመዝጊያ ዝግጅት ሲሆን በሰራተኞች ዘንድ ያለውን ቅርርብ የሚያሳድግ ነው። #የኢትዮጵያአየርመንገድ #የሰራተኞችቀን2017
በዝግጅቱ ላይ ከአየር መንገዱ የተለያዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞች ከዋና ስራ አስፈፃሚው እና ከየክፍሎቻቸው ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እጅ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል። በዛሬው
ዕለት የተከናወነው ክብረ በዓል ለአንድ ሳምንት የቆየው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰራተኞች ቀን ክብረ በዓል የመዝጊያ ዝግጅት ሲሆን በሰራተኞች ዘንድ ያለውን ቅርርብ የሚያሳድግ ነው። #የኢትዮጵያአየርመንገድ #የሰራተኞችቀን2017