Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ዛሬ በይፋ የተመረቀው የዋቆ ጉቱ ኤርፖርት ተርሚናል ጎብኚዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ እንዲሁም የአካባቢው ተወላጆች ከመላው ዓለም ወደ ባሌ ዞን ሲመጡ ምቾት ያለው አገልግሎት በመስጠት ቁልፍ መተላለፊያ (Gateway) ሆኖ ያገለግላል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ2017 ዓ.ም የገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል። መልካም በዓል!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በአስደናቂ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የምትታወቀውን ታሪካዊቷን የላሊበላ ከተማን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ይጎብኙ። ይህንን የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ በስፍራው ተገኝተው በመጎብኘት የማይረሳ የጉዞ ትዉስታ ያኑሩ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ላሊበላ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ላሊበላ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በኢትዮጵያ አየር መንገድ አጠቃላይ የደንበኞች አገልግሎት እንደምን ያለ ነው? በዛሬው የኢትዮጵያ ዝግጅታችን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የደንበኞች አገልግሎት የስራ ክፍል እንቅስቃሴ በተመለከተ ቆይታ አድርገናል፤ይከታተሉን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ @FanaBroadcastingCorporate
#የኢትዮጵያአየርመንገድ @FanaBroadcastingCorporate
ክቡራን ደንበኞቻችን
የደንበኞች ጥሪ መቀበያ ማዕከል ቁጥራችን 6787 በሙሉ አቅሙ የሀገር ውስጥ ጥሪዎችን እየተቀበለ እንዳልሆነ ተረድተናል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ የቴክኒክ ባለሙያዎቻችን እየሰሩ ይገኛሉ።
በ6787 መገልገል ያልቻላችሁ ክቡራን ደንበኞቻችን በድረ ገፃችን www.ethiopianairlines.com በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችን https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app እንዲሁም በሌሎች የዲጂታል አማራጮቻችን በመጠቀም አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ተጨማሪ እርዳታ የምትሹ ደንበኞቻችን በአቅራቢያችሁ ወደሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎቻችን አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን። ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
የደንበኞች ጥሪ መቀበያ ማዕከል ቁጥራችን 6787 በሙሉ አቅሙ የሀገር ውስጥ ጥሪዎችን እየተቀበለ እንዳልሆነ ተረድተናል። ይህንን ችግር ለመቅረፍ የቴክኒክ ባለሙያዎቻችን እየሰሩ ይገኛሉ።
በ6787 መገልገል ያልቻላችሁ ክቡራን ደንበኞቻችን በድረ ገፃችን www.ethiopianairlines.com በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችን https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app እንዲሁም በሌሎች የዲጂታል አማራጮቻችን በመጠቀም አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ተጨማሪ እርዳታ የምትሹ ደንበኞቻችን በአቅራቢያችሁ ወደሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎቻችን አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን። ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
ክቡራን ደንበኞቻችን
ዛሬ በደንበኞቻችን የጥሪ አገልግሎት ማዕከል ቁጥር 6787 ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ማዕከሉ የደንበኞችንን ጥሪ በሙሉ አቅሙ እየተቀበለ አለመሆኑን መግለፃችን ይታወሳል።
ችግሩን ለመቅረፍ የቴክኒክ ባለሙያዎቻችን ባደረጉት ርብርብ በአሁኑ ሰዓት አገልግሎቱን ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል። በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ወደ 6787 በመደወል የተለመደውን የደንበኞች አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እያስታወቅን ለተፈጠረው ችግር በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
ዛሬ በደንበኞቻችን የጥሪ አገልግሎት ማዕከል ቁጥር 6787 ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ማዕከሉ የደንበኞችንን ጥሪ በሙሉ አቅሙ እየተቀበለ አለመሆኑን መግለፃችን ይታወሳል።
ችግሩን ለመቅረፍ የቴክኒክ ባለሙያዎቻችን ባደረጉት ርብርብ በአሁኑ ሰዓት አገልግሎቱን ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል። በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ወደ 6787 በመደወል የተለመደውን የደንበኞች አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እያስታወቅን ለተፈጠረው ችግር በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
ጤና ይስጥልን!
ይህ የስታር አሊያንስ አባል የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለም ዓቀፍ የመንገደኞች ጥሪ ማዕከል ነው። እርስዎን ለማስተናገድ ሁሌም ዘግጁ ነን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ይህ የስታር አሊያንስ አባል የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለም ዓቀፍ የመንገደኞች ጥሪ ማዕከል ነው። እርስዎን ለማስተናገድ ሁሌም ዘግጁ ነን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አስደሳች በረራ እና ማራኪ እይታ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር! በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበርሩ ያነሷቸውን ምስሎች በመልዕክት መቀበያ ሳጥን በኩል ይላኩልን፤ መልሰን እናጋራዎታለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከኢትዮጵያ አየርመንገድ ጋር ወደ ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ይጓዙ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በአፍሪካ አቪዬሽን ታሪክ የስኬት እና ቀዳሚነት ምልክት ሆነን ዛሬ ላይ ደርሰናል። ለበለጠ ስኬት እና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎትም እየተጋን እንገኛለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከእኛ ጋር የሚኖርዎትን ቆይታ በልዩ መስተንግዷችን ምቹ እና አስደሳች ለማድረግ ሁሌም እንተጋለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በዛሬው የኢትዮጵያ የተሰኘው ፕሮግራማችን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሰራተኞቹ ተስማሚ የስራ አካባቢ ለመፍጠር ከሚያደርጋችው እንቅስቃሴዎች መካከል የሰራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ይጠቀሳል ፤ የዛሬው ፕሮግራማችን በዚህ ላይ ያተኮረ ነው ይከታተሉን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ @FanaBroadcastingCorporate
https://youtu.be/ecwFJsabUf8
#የኢትዮጵያአየርመንገድ @FanaBroadcastingCorporate
https://youtu.be/ecwFJsabUf8
YouTube
የሰራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ
በዛሬው የኢትዮጵያ የተሰኘው ፕሮግራማችን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሰራተኞቹ ተስማሚ የስራ አካባቢ ለመፍጠር ከሚያደርጋችው እንቅስቃሴዎች መካከል የሰራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ይጠቀሳል ፤ የዛሬው ፕሮግራማችን በዚህ ላይ ያተኮረ ነው ይከታተሉን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ @fanamediacorporation
#የኢትዮጵያአየርመንገድ @fanamediacorporation
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ ከዚህ አለም በሞት ለተለዩት ለቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለካፒቴን መሐመድ አህመድ ቤተሰቦቻቸው፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮች፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ፣ የማኔጅመንት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የመታሰቢያ መርሓ ግብር ያካሄደ ሲሆን በአየር መንገዱ ቅጥር ግቢም የመታሰቢያ ሀውልት ቆሞላቸዋል።
ካፒቴን መሀመድ አህመድ በአቪዬሽኑ መስክ ግንባር ቀደም ከሚባሉት አመራሮች አንዱ ሲሆኑ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለንተናዊ ዕድገት ያኖሩት የማይተካ አሻራ በመጪው ትውልድም ሁልግዜ ሲታወስ ይኖራል።
ካፒቴን መሀመድ አህመድ ከኢትዮጵያ አልፈው የአፍሪካ አየር መንገዶች ህብረት ን ለአስር አመታት በመምራት በአፍሪካ አየር መንገዶች መካከል የጠበቀ ግንኙነት እንዲፈጠርና ለአህጉሪቱ የአቪዬሽን ኢንደስትሪ ዕድገት በጋራ የመስራት መንፈስ እንዲጎለብት ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። በአለም ዓቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር በአመራር ኮሚቴዎች ውስጥ በነበራቸው ሚና የአፍሪካ አየር መንገዶች በአለም መድረክ አድገውና ጎልብተው በአለም መድረክ ላይ እንዲወጡ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርገዋል።
ካፒቴን መሀመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድን በዋና ስራ አስፈፃሚነት በመሩባቸው ዓመታት አየር መንገዱ ዛሬ ለደረሰበት እድገት እና ስኬት ባበረከቱት የላቀ አስተዋፅዖ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራር ቦርድ፣ ማኔጅመንት እና ሰራተኞች ምን ጊዜም ያስታውሷቸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ካፒቴን መሀመድ አህመድ በአቪዬሽኑ መስክ ግንባር ቀደም ከሚባሉት አመራሮች አንዱ ሲሆኑ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለንተናዊ ዕድገት ያኖሩት የማይተካ አሻራ በመጪው ትውልድም ሁልግዜ ሲታወስ ይኖራል።
ካፒቴን መሀመድ አህመድ ከኢትዮጵያ አልፈው የአፍሪካ አየር መንገዶች ህብረት ን ለአስር አመታት በመምራት በአፍሪካ አየር መንገዶች መካከል የጠበቀ ግንኙነት እንዲፈጠርና ለአህጉሪቱ የአቪዬሽን ኢንደስትሪ ዕድገት በጋራ የመስራት መንፈስ እንዲጎለብት ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። በአለም ዓቀፍ የአየር ትራንስፖርት ማህበር በአመራር ኮሚቴዎች ውስጥ በነበራቸው ሚና የአፍሪካ አየር መንገዶች በአለም መድረክ አድገውና ጎልብተው በአለም መድረክ ላይ እንዲወጡ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርገዋል።
ካፒቴን መሀመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድን በዋና ስራ አስፈፃሚነት በመሩባቸው ዓመታት አየር መንገዱ ዛሬ ለደረሰበት እድገት እና ስኬት ባበረከቱት የላቀ አስተዋፅዖ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራር ቦርድ፣ ማኔጅመንት እና ሰራተኞች ምን ጊዜም ያስታውሷቸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ