Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.6K subscribers
3.74K photos
140 videos
2 files
410 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ሞምባሳ ከ1,100 ዶላር ጀምሮ የ2 ሌሊት የ3 ቀናት ሆቴል ቆይታን ያካተተ “አንድ ትኬት ይግዙ አንድ በነፃ ይሸለሙ” ልዩ የጉዞ ጥቅል አዘጋጅቷል:: ትኬትዎን ከታህሳስ 6፣2017 እስከ እስከ ጥር 23 ፣2017 ዓ.ም ድረስ ገዝተው በረራዎን ከታህሳስ 21 እስከ የካቲት 21፣ 2017 ዓ.ም ያድርጉ። ስለ ልዩ የጉዞ ጥቅሉ ተጨማሪ መረጃ በአቅራቢያዎ ከሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎቻችንን አሊያም የጉዞ ወኪልዎን ማግኘት ይችላሉ።
ደንብና እና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ይብረሩ! ምቹ እና አስደሳች የበረራ ጊዜ ያሳልፉ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን @TimothGB ናቸው፤ እናመሰግናለን! እርስዎም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበርሩ ያነሷቸውን ምስሎች ይላኩልን፤ መልሰን እናጋራዎታለን።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለተኛው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን (ET-BAX) ፣ አየር መንገዳችን ለምቹ እና ዘመናዊ የደንበኞች አገልግሎት የሚሰጠውን ትኩረት ማሳያ ከመሆኑም በላይ በአቪዬሽኑ ዘርፍ በአፍሪካ አህጉር ያለንን የመሪነት ሚና የሚያጠናክር ነው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ኤርባስA350-1000
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመርያ በረራዉን የት ነዉ ያደረገዉ?

#የኢትዮጵያአየርመንገድ #በረራ
በኢትዮጵያዊ እንክብካቤ እና መስተንግዶ ምቾትዎን ጠብቀን ለማገልገል ሁሌም እንተጋለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የበረራ ቆይታዎን አስደሳች ለማድረግ ዝግጅታችንን አጠናቅቀናል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አስደሳች የበረራ ጉዞ በኢትዮጵያ አየር መንገድ! መልካም ሳምንት ይሁንልዎ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
መግለጫ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በርካታ ተጨማሪ በረራዎችን በመመደብ ለውድ ደንበኞቹ አገልግሎት ከሚሰጥባቸው ሀይማኖታዊ በዓላት መካከል በመጪው ታህሳስ ወር የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረበዓል አንዱ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ክቡራን ደንበኞቹ ይህንን በዓል በስፍራው ተገኝተው እንዲያከብሩ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ወደ ድሬዳዋ ከሚያደርገው መደበኛ ዕለታዊ በረራዎች ባሻገር በርካታ ተጨማሪ በረራዎችን በመመደብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን እነዚህ ተጨማሪ በረራዎች ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ ያለምንም መንገደኛ መሆኑን ታሳቢ ያደረገ የዋጋ ማስተካከያ የሚደረግ መሆኑን ለክቡራን ደንበኞቻችን ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን።
ይህንን ክብረበዓል ተከትሎ ወደ ድሬዳዋ የሚጓዘውን ከፍተኛ የመንገደኛ ቁጥር በተሳለጠ መልኩ ለማስተናገድ ለድሬደዋ መንገደኞች ተለይቶ በተዘጋጀው የስልክ ቁጥር 6787 በመደወል ከመንገደኞች ምዝገባ እና ትኬት ጋር የተያያዘ ማንኛውንም መረጃ ማግኘት ይችላሉ። የዋጋ ማስተካከያው አየር መንገዱ ወደ ድሬደዋ የሚያደርጋቸውን ሰባት ዕለታዊ መደበኛ በረራዎች አያካትትም።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓሉን ለምታከብሩ ውድ ደንበኞቻችን ሁሉ ከወዲሁ መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮንጎ ዴሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ መንግስት ጋር በጋራ በመሆን “ኤር ኮንጎ” የሚል ስያሜ የተሰጠው አየር መንገድ አቋቁሞ በይፋ ስራ አስጀመረ። ኤር ኮንጎ በሁለት ቦይንግ 737 አውሮፕላኖች በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ሰባት ኤርፖርቶች በረራ በማድረግ አገልግሎት ጀምሯል። ይህ ጥምረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራዕይ 2035 አንዱ አካል ሲሆን ከዚህም በፊት በሎሜ አስካይ አየር መንገድ፣ በሊሎንግዌ የማላዊ አየር መንገድ እንዲሁም በሉሳካ የዛምቢያ አየር መንገድን በጋራ ማቋቋሙ ይታወሳል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ: https://corporate.ethiopianairlines.com/Press-release-open-page/ethiopian-airlines-partners-with-drc-government-to-launch-air-congo
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን Hilena Tafesse ናቸው፤ እናመሰግናለን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ላይ የምግብና መጠጥ ዝግጅት ክፍል (Inflight Catering) በቀን ከ100,000 ሺህ በላይ ምግቦችን ያዘጋጃል።
ሙሉ ፕሮግራሙን በዚህ ሊንክ እንዲከታተሉ ጋብዘንዎታል!
https://www.youtube.com/watch?v=6hKPZLtflD4

#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰ የተመራ ከፍተኛ የኢቢሲ የስራ ሀላፊዎች ቡድን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅጥር ግቢ በመገኘት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ ሀላፊዎች ጋር ፍሬያማ ውይይት እንዲሁም የስራ ጉብኝት አደረገ።

የኢቢሲ አመራሮች በጉብኝታቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አቪዬሽን ልህቀት ቀዳሚ እንዲሁም በዓለም ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስቻሉትን የስራ ክፍሎችና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ሁለቱ ብሔራዊና አንጋፋ ተቋማት በቅርበት በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር አድርገዋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ Ethiopian Broadcasting Corporation