የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጥቅምት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በህንድ አራተኛ መዳረሻ ወደሆነችው ቸናይ ከተማ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ በማሳደግ በሳምንት አራት ቀን በረራ ማድረግ የሚጀምር መሆኑን ሲገልፅ በደስታ ነው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ውድ ደንበኞቻችን
ዛሬ ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከለሊቱ 09፡00 ሰአት ጀምሮ በነበረው ከፍተኛ ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት አብዛኞቹ ወደ አዲስ አበባ ሲያቀኑ የነበሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሊያርፉ ባለመቻላቸው በአቅራቢያ ወደሚገኙ አማራጭ ኤርፖርቶች ተመልሰው እንዲያርፉ ተገደዋል።
ይህ የአየር ሁኔታ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም-አቀፍ የጠዋት በረራዎቻችን ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል። እንደተለመደው የመንገደኞቻችን ደህንነት ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በተሳፋሪዎቻችን የጉዞ ዕቅዶች ላይ ሊፈጠሩ የሚችሉ መስተጓጉሎችን ለመቅረፍ አስፈላጊውን ሁሉ እያደረግን እንገኛለን።
በዚህ አጋጣሚ መንገደኞቻችን ላጋጠማቸው መጉላላት ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
ዛሬ ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከለሊቱ 09፡00 ሰአት ጀምሮ በነበረው ከፍተኛ ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ምክንያት አብዛኞቹ ወደ አዲስ አበባ ሲያቀኑ የነበሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሊያርፉ ባለመቻላቸው በአቅራቢያ ወደሚገኙ አማራጭ ኤርፖርቶች ተመልሰው እንዲያርፉ ተገደዋል።
ይህ የአየር ሁኔታ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም-አቀፍ የጠዋት በረራዎቻችን ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል። እንደተለመደው የመንገደኞቻችን ደህንነት ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በተሳፋሪዎቻችን የጉዞ ዕቅዶች ላይ ሊፈጠሩ የሚችሉ መስተጓጉሎችን ለመቅረፍ አስፈላጊውን ሁሉ እያደረግን እንገኛለን።
በዚህ አጋጣሚ መንገደኞቻችን ላጋጠማቸው መጉላላት ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አሊያንስ አባል
መሃላ በተግባር!
አቶ ለማ በቀለ አለሙ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በሴኪዩሪቲ ክፍል ውስጥ የሚሰሩ የሥራ ባልደረባችን ሲሆኑ በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና ሲቀጠሩ በገቡት ቃል መሰረት አየር መንገዱ የሚመራበትን መርህና ሥነ ምገባር እንዲሁም ሙያዊ ታማኝነታቸውን በብቃት በመወጣት አስመስክረዋል። አቶ ለማ በሥራ ገበታቸው ላይ በነበሩበት ወቅት አንድ መንገደኛ ረስተዉ የሄዱትን የእጅ ቦርሳ ውስጡ ከነበረው 71 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ጋር ምንም ሳያጎድሉ በሙሉ ለሚመለከተው የአየር መንገድ ቢሮ ያስረከቡ ሲሆን፤ አየር መንገዱም አስፈላጊውን ማጣራት ካደረገ በኋላ ንብረቱ ለውድ ደንበኛችን እንዲመለስ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም-አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና ስነ-ምግባር የተላበሰ የደንበኞች አገልግሎትን የዕድገቱ መርሕ አድርጎ በስኬት ጎዳና ላይ የሚገኝ ብሔራዊ ኩራት ነው። በዚህ አጋጣሚ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማኔጀመንት አባላት እና ሠራተኞች ለዚህ መልካምና አርዓያነት ላለው ተግባር የከበረ ምስጋና ያቀርባሉ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አቶ ለማ በቀለ አለሙ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በሴኪዩሪቲ ክፍል ውስጥ የሚሰሩ የሥራ ባልደረባችን ሲሆኑ በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና ሲቀጠሩ በገቡት ቃል መሰረት አየር መንገዱ የሚመራበትን መርህና ሥነ ምገባር እንዲሁም ሙያዊ ታማኝነታቸውን በብቃት በመወጣት አስመስክረዋል። አቶ ለማ በሥራ ገበታቸው ላይ በነበሩበት ወቅት አንድ መንገደኛ ረስተዉ የሄዱትን የእጅ ቦርሳ ውስጡ ከነበረው 71 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ጋር ምንም ሳያጎድሉ በሙሉ ለሚመለከተው የአየር መንገድ ቢሮ ያስረከቡ ሲሆን፤ አየር መንገዱም አስፈላጊውን ማጣራት ካደረገ በኋላ ንብረቱ ለውድ ደንበኛችን እንዲመለስ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም-አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና ስነ-ምግባር የተላበሰ የደንበኞች አገልግሎትን የዕድገቱ መርሕ አድርጎ በስኬት ጎዳና ላይ የሚገኝ ብሔራዊ ኩራት ነው። በዚህ አጋጣሚ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማኔጀመንት አባላት እና ሠራተኞች ለዚህ መልካምና አርዓያነት ላለው ተግባር የከበረ ምስጋና ያቀርባሉ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ክቡራን መንገደኞቹ አዝናኝ የበረራ ቆይታ ይኖራቸው ዘንድ የተለያዩ የመዝናኛ አማራጮችን የሚያቀርበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የሙዚቃ ስራዎች 140 ወደሚጠጉ ዓለም-አቀፍ መዳረሻዎቹ ለሚጓዙ መንገደኞቹ ተደራሽ የሚሆኑበትን አማራጭ ይዞ ብቅ ብሏል። በመሆኑም የሙዚቃ ስራዎቻችሁ አየር መንገዱ በሚያቀርበው የአውሮፕላን ውስጥ የመዝናኛ ቻናሎች ምርጫ ውስጥ እንዲካተትላችሁ የምትፈልጉ የጥበብ ባለሙያዎች በሙሉ ደረጃቸውን እና ጥራታቸውን የጠበቁ ሙዚቃዎቻችሁን ይዛችሁ በመቅረብ የዕድሉ ተሳታፊ እንድትሆኑ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ለተጨማሪ መረጃ እና ቀጠሮ ለማስያዝ በስልክ ቁጥሮቻችን 0115178079/4079/8197 ይደውሉ። አሊያም በኢሜል አድራሻዎቻችን HiwotGe@ethiopianairlines.com ወይም
HilinaBel@ethiopianairlines.com ይፃፉልን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አላያንስ አባል
ለተጨማሪ መረጃ እና ቀጠሮ ለማስያዝ በስልክ ቁጥሮቻችን 0115178079/4079/8197 ይደውሉ። አሊያም በኢሜል አድራሻዎቻችን HiwotGe@ethiopianairlines.com ወይም
HilinaBel@ethiopianairlines.com ይፃፉልን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አላያንስ አባል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው “World Travel Awards” ሽልማት በስድስት ዘርፎች ዕጩ ሆኖ ቀርቧል። ዘርፎቹም ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ፣ ምርጥ የአፍሪካ ቢዝነስ ክላስ አየር መንገድ፣ ምርጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ክላስ አየር መንገድ፣ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ብራንድ፣ ምርጥ የአፍሪካ የበረራ ላይ መዝናኛ መፅሔት ሰላምታ እና ምርጥ የአፍሪካ ኮንፈረንስ ሆቴል (የኢትዮጵያ ስካይ ላይት) ዘርፎች ናቸው። እርስዎም ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመጠቀም ድምፅዎን የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ኩራት ለሆነው አየር መንገድዎ እንዲሰጡ ተጋብዘዋል።
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በደማቅ ፈገግታ ተቀብለን በልዩ ኢትዮጵያዊ መስተንግዷችን የበረራ ቆይታዎን ምቹ ለማድረግ ዝግጁ ነን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው “World Travel Awards” ሽልማት ላይ በምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ብራንድ ዘርፍ ዕጩ ሆኖ ቀርቧል። እርስዎም ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመጠቀም ድምፅዎን የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ኩራት ለሆነው አየር መንገድዎ እንዲሰጡ ተጋብዘዋል።
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርስቲ አለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና በአፍሪካ በቀዳሚነቱ የሚጠቀስ የአቪዬሽን ትምህርት እና ስልጠናዎችን ከአፍሪካ እና ከተቀረው ዓለም ለሚቀበላቸው ተማሪዎች በተለያየ ፕሮግራም በማስተማር ለአመታት ዘልቋል።
ዘመናዊና ምቹ የሆኑ የማስተማሪያ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ብቁ እና የሰለጠነ የሰው ሀብት ለአፍሪካ ብሎም ለአለም አቪዬሽን ኢንደስትሪ እያበረከተ የዘርፉ የልህቀት ማዕከል ሆኖ ቀጥሏል።
#የኢትዮጵያአቪዬሽንዩኒቨርስቲ
ዘመናዊና ምቹ የሆኑ የማስተማሪያ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ብቁ እና የሰለጠነ የሰው ሀብት ለአፍሪካ ብሎም ለአለም አቪዬሽን ኢንደስትሪ እያበረከተ የዘርፉ የልህቀት ማዕከል ሆኖ ቀጥሏል።
#የኢትዮጵያአቪዬሽንዩኒቨርስቲ
በ World Travel Awards ሽልማት አምና የተቀዳጀነውን የአመቱ የአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ክላስ አየር መንገድ ሽልማት ዘንድሮም ለመድገም አንድ ርምጃ ብቻ ቀርቶናል። ከታች በተቀመጠው ሊንክ ለዚህ ዘርፍ የታጨውን አየር መንገድዎን ይምረጡ!
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዲጂታል አማራጮቹ በተጨማሪ በአዳዲስ የሽያጭ ቢሮዎች ይበልጥ ወደ እርስዎ ቀርቧል። በሜክሲኮ ከንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ወደ አፍሪካ ህብረት በሚወስደው መንገድ ላይ እንዲሁም ከሲ.ኤም.ሲ ወደ አያት በሚወስደው መንገድ ፀሀይ ሪል ስቴት ፊት ለፊት በሚገኘው አዲስ-አፍሪካ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽንና ኤግዚቢሽን ማዕከል በከፈትናቸው አዳዲስ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎቻችን አገልግሎት መስጠት ጀምረናል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ቦይንግ እና ቲንክ ያንግ በቅንጅት ከሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ለተውጣጡ ተማሪዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ ትምህርቶች (STEM) ልዩ ስልጠና በመስጠት ተማሪዎችን አስመርቀዋል። ሰልጣኞቹ ከ28 የተለያዩ የሁለተኛ ደረጃ ትቤቶች የተውጣጡ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ ስልጠናውም በኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩነቪርሲቲ በኩል ተሰጥቷል። ይህ STEM የተሰኘ ፕሮግራም አሁን ላይ ለሁለተኛ ጊዜ የተሰጠ ሲሆን የትምህርት ተደራሽነት በበቂ ሁኔታ ባልተሟላባቸው አካባቢዎች ላሉ ወጣቶች ልዩ ትኩረት ያደርጋል። በዚህ በ2ኛው ዙር ከተመረቁ ተማሪዎች ውስጥ 50% ሴቶች ናቸው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በዘንድሮው የ “World Travelers Award” ሽልማት ከታጨንባቸው ስድስት ዘርፎች አንዱ በአፍሪካ ምርጡ የኢኮኖሚ ክላስ አየር መንገድ ዘርፍ ነው። ከታች በተቀመጠው ሊንክ ለዚህ ዘርፍ የታጨውን አየር መንገድዎን ይምረጡ!
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
https://www.worldtravelawards.com/vote-r3#votenow
#የኢትዮጵያአየርመንገድ