የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ኤሮ ክለብ በአቪዬሽን መስክ በጋራ ብቁ እና የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ።
👏76❤41👍34😍5🎉3
ማሳሰቢያ
ከዚህ በፊት አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ እንዲሁም ስራ ፈላጊዎችን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ መሰማራታቸውንና ማሕበረሰቡ ይህንን አውቆ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ማሳሰባችን ይታወቃል፡፡
በቅርቡም የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና ተቋማችን ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች መሰማራታቸውን ደርሰንበታል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ የማይጠይቅ መሆኑን፣ ለስራ ቅጥር ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ የማይጠይቅ እና ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ የማይሰራ መሆኑን እና ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ እንዳልተሰማራ ለማሳወቅ ይወዳል፡፡
ስለሆነም ማሕበረሰቡ ይህንን ተገንዝቦ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ለማሳሰብ እንወዳለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከዚህ በፊት አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ እንዲሁም ስራ ፈላጊዎችን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ መሰማራታቸውንና ማሕበረሰቡ ይህንን አውቆ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ማሳሰባችን ይታወቃል፡፡
በቅርቡም የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና ተቋማችን ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች መሰማራታቸውን ደርሰንበታል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ የማይጠይቅ መሆኑን፣ ለስራ ቅጥር ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ የማይጠይቅ እና ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ የማይሰራ መሆኑን እና ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ እንዳልተሰማራ ለማሳወቅ ይወዳል፡፡
ስለሆነም ማሕበረሰቡ ይህንን ተገንዝቦ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ለማሳሰብ እንወዳለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍107❤29👏12
በዛሬው ዕለት ጥር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አሉላ አባነጋ አየር ማረፊያ በበረራ ቁጥር ET106 የተደረገው በረራ በኤርፖርቱ ካረፈ በኋላ ከበረራ መስመር የመንሸራተት ችግር ገጥሞታል።
ሁሉም የአውሮፕላኑ ተሳፋሪዎች እንዲሁም የበረራ ባለሙያዎች ያለምንም ጉዳት ከአውሮፕላኑ ወጥተዋል።
የችግሩን መነሻ አየር መንገዳችን በማጣራት ላይ ይገኛል።
በዚሁ አጋጣሚ ክቡራን ደንበኞቻችን ላይ በደረሰው መጉላላት ይቅርታ እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ሁሉም የአውሮፕላኑ ተሳፋሪዎች እንዲሁም የበረራ ባለሙያዎች ያለምንም ጉዳት ከአውሮፕላኑ ወጥተዋል።
የችግሩን መነሻ አየር መንገዳችን በማጣራት ላይ ይገኛል።
በዚሁ አጋጣሚ ክቡራን ደንበኞቻችን ላይ በደረሰው መጉላላት ይቅርታ እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍212❤65👏26🎉12🥰6
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፍቅረኞች ቀንን በማስመልከት ከአዲስ አበባ ሞምባሳ፣ ኖሲ ቤ፣ ሴሸልስ እና ባንኮክ ከተሞች የጉዞ ጥቅል አዘጋጅቶ እንደሚጠብቅዎ ሲገልፅ ደስታ ይሰማዋል።ትኬትዎን ከጥር 6 ቀን እስከ ጥር 16 ቀን 2016 ዓ. ም ይግዙ፤ጉዞዎን ከየካቲት 3 ቀን እስከ የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ. ም ያድርጉ። አንድ ትኬት ሲገዙ አንድ ትኬት በነፃ ይሸለማሉ። ለተጨማሪ መረጃ በአቅራቢያዎ የሚገኘውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽያጭ ቢሮ አሊያም የጉዞ ወኪልዎን እንዲሁም ድረ ገፃችንን www.ethiopianairlines.com ይጎብኙ። ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍59❤41🥰13
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዓመቱ በሚከናወነው የብሪክስ አባል ሀገራት የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የ2024 ሽልማት ላይ “Corporate Sustainability Achievement Award” አሸናፊ ሆነ። ሽልማቱ በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ለሚኖረው የንግድ ትስስር፣ የአፈፃፀም ልህቀት እና ፈጠራ ዕውቅና የሚሰጥ ነው። የብሪክስ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት በአባል ሀገራት ውስጥ የሚገኙ የንግድና የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴዎችን ለማበረታታት እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም የተቋቋመ ምክር ቤት ነው።
https://www.youtube.com/watch?v=9DeediZvvoY
https://rb.gy/o2v7ym
https://www.youtube.com/watch?v=9DeediZvvoY
https://rb.gy/o2v7ym
👍94❤40👏14🎉6