Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.55K photos
134 videos
2 files
398 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በላቲቪያ ሪጋ የዓለም የጎዳና ሩጫ ላይ በመሳተፍ ድል ላስመዘገበው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ትናንት ምሽት ከፍራንክፈርት ሲነሳ ደማቅ አሸኛኘት አድርጎለታል።
አስደሳች የበረራ ግዜ በኢትዮጵያ አየር መንገድ!
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበሩ በምስል ያስቀሩትን ማራኪ ዕይታ ያጋሩን፤ Yalemsew Birehanu ናቸው እናመሰግናለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በምናብ ወደኋላ ተጉዘን የቀደሙትን ስናስታውስ።

#ትውስታ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኬንያ ሞምባሳ የ50% የደርሶ መልስ ትኬት ልዩ ቅናሽ አድርጎ ይጠብቅዎታል። ትኬትዎን እስከ ጥቅምት 4 ፣2016 ዓ.ም ይግዙ ፤ በረራዎን እስከ ሕዳር 20፣ 2016 ዓ.ም ያድርጉ።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዚሁ አጋጣሚ በረራ ያላችሁ ውድ ደንበኞቻችን ዛሬ ከሰዓት እና ነገ ጠዋት የመንገድ መጨናነቅ ሊኖር ስለሚችል የበረራ መስተጓጎል እንዳያጋጥማችሁ ከተለመደው ሰዓት ቀድማችሁ ወደ ኤርፖርት እንድታመሩ በትህትና እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ወደሚያስደስትዎ መዳረሻ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ይብረሩ!

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከጥቅምት 18, 2016 ዓ .ም ጀምሮ ወደ ጋና አክራ ከተማ የሚያደርገውን በረራ ያሳድጋል። በዚህም መሰረት በቀን ሁለት ጊዜ በመብረር ሳምንታዊ ምልልሱን ወደ 14 የሚያሳድግ ይሆናል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ከ 130 በላይ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች! ምርጫዎን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያድርጉ።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመብረር እንኳን በደህና መጡ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የእንግሊዝ ንጉሳውያን ቤተሰብ አባል ክብርት ሶፊ ሄሌን ራይስ ጆንስ ፣ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደርና በአፍሪካ ሕብረት ቋሚ መልእክተኛ ዳረን ዌልች እና የልዑካን ቡድናቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተገኝተው ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝታቸው ወቅት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የአየር መንገዱ አመራር አባላት ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጉብኝታቸው ማጠቃለያም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እንግሊዝ በረራ ማድረግ የጀመረበት 50ኛ ዓመት በኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርስቲ ተከብሯል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ