አስደሳች በረራ እና ማራኪ እይታ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በሳምንታዊው "የኢትዮጵያ" መርሐግብራችን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዴሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ እየሰጠ የሚገኘውን የበረራ አገልግሎት አስመልክቶ ቆይታ አድርገናል፤ ይከታተሉን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቀድሞ የአየር መንገዱ ቦርድ አባል ለነበሩት ክቡር የኢ.ፌ.ዲ. ሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሽኝት መርሐ ግብር አካሄደ።
በዚህ የሽኝት መርሀግብር ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።
በመርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባስተላፉት መልዕክት አየር መንገዱ አህጉራዊ መሪነቱን እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም እንደወትሮው ሁሉ የጥንካሬ የእድገት እና የአዳዲስ ዕመርታዎች ተምሳሌት ሆኖ እንዲዘልቅ ክቡር ፕሬዝደንት በቦርድ አባልነታቸው ላበረከቱት አስተዋፅዖ ምስጋና አቅርበዋል።
በተመሳሳይም አየር መንገዱን በቦርድ አባልነት ያገለገሉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብርት ወሮ ያስሚን ወሀብረቢ ሽኝት ተደርጎላቸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በዚህ የሽኝት መርሀግብር ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።
በመርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባስተላፉት መልዕክት አየር መንገዱ አህጉራዊ መሪነቱን እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም እንደወትሮው ሁሉ የጥንካሬ የእድገት እና የአዳዲስ ዕመርታዎች ተምሳሌት ሆኖ እንዲዘልቅ ክቡር ፕሬዝደንት በቦርድ አባልነታቸው ላበረከቱት አስተዋፅዖ ምስጋና አቅርበዋል።
በተመሳሳይም አየር መንገዱን በቦርድ አባልነት ያገለገሉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብርት ወሮ ያስሚን ወሀብረቢ ሽኝት ተደርጎላቸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታላቁን የረመዳን ፆም ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል የኢፍጣር መርሐግብር አካሄደ።
በኢፍጣር መርሐግብሩ ላይ የተከበሩ ሼህ አብዱልአዚዝ አብዱልወሌ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ፣ የተከበሩ ዶ/ር ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ዘርፍ ዋና ሀላፊ አቶ ለማ ያዴቻ ፣ የአየር መንገዱ አመራር አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዓመቱ የኢፍጣር መርሀግብር ከማዘጋጀት ባሻገር በርካታ በረራዎችንና ሰራተኞችን በመመደብ የሀጅ ተጓዦችን ወደ ሳዑዲ አረቢያ በማጓጓዝ፣ለሐጅ ተጓዦች ብቻ የሚውል መስገጃና ማረፊያ ያለው ተርሚናል ማዘጋጀት፣በኢትዮጵያ አየር መንገድ ፋውንዴሽን በኩል በተለያዩ ጊዜያትና ሁኔታ በመንገደኞች የተረሱ ሃይማኖታዊ መጻሕፍትን ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በክብር በማስረከብ እና በተለያዩ ተያያዥ አገልግሎቶች ሀገራዊ ሀላፊነቱን አቅም በፈቀደ መጠን ሲወጣ ቆይቷል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በኢፍጣር መርሐግብሩ ላይ የተከበሩ ሼህ አብዱልአዚዝ አብዱልወሌ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ፣ የተከበሩ ዶ/ር ሼህ ሱልጣን አማን ኤባ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ዘርፍ ዋና ሀላፊ አቶ ለማ ያዴቻ ፣ የአየር መንገዱ አመራር አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዓመቱ የኢፍጣር መርሀግብር ከማዘጋጀት ባሻገር በርካታ በረራዎችንና ሰራተኞችን በመመደብ የሀጅ ተጓዦችን ወደ ሳዑዲ አረቢያ በማጓጓዝ፣ለሐጅ ተጓዦች ብቻ የሚውል መስገጃና ማረፊያ ያለው ተርሚናል ማዘጋጀት፣በኢትዮጵያ አየር መንገድ ፋውንዴሽን በኩል በተለያዩ ጊዜያትና ሁኔታ በመንገደኞች የተረሱ ሃይማኖታዊ መጻሕፍትን ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በክብር በማስረከብ እና በተለያዩ ተያያዥ አገልግሎቶች ሀገራዊ ሀላፊነቱን አቅም በፈቀደ መጠን ሲወጣ ቆይቷል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ