Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.74K photos
140 videos
2 files
410 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለክቡራን መንገደኞቹ ምቹ የበረራ አማራጭ ሰዓት ለማቅረብ በሚያደርገው ያላሰለሰ ጥረት ከሕዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሳምንት ሶስት ቀናት ከአዲስ አበባ ሮም ከእኩለ ቀን በኋላ እንዲሁም ከሮም አዲስ አበባ በማለዳ የሚነሳ ተጨማሪ በረራ የሚጀምር መሆኑን ሲያበስር ደስታ ይሰማዋል። ትኬትዎን በድረ ገፃችን www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያችን https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app በመጠቀም ይቁረጡ የዚህ አዲስ የበረራ ሰአት አማራጭ ተጠቃሚ ይሁኑ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ሮም
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ደምቢዶሎ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ በማሳደግ ከሕዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከአዲስ አበባ ደምቢዶሎ ዕለታዊ በረራ የሚጀምር መሆኑን ለክቡራን ደንበኞቹ እያበሰረ ደንበኞች በድረ ገፅ www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app በመጠቀም ትኬታቸውን ቆርጠው በዕለታዊ በረራ አገልግሎቱ እንዲጠቀሙ ይጋብዛል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
አስደሳች ዜና!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሕዳር24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሳምንት ሶስት ቀናት ከአዲስ አበባ ወደ አቴንስ ከእኩለ ቀን በኋላ እንዲሁም ከአቴንስ አዲስ አበባ በማለዳ የሚነሳ ተጨማሪ በረራ የሚጀምር መሆኑን እያሳወቀ ክቡራን ደንበኞች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረገጽ www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app ትኬታቸውን ገዝተው የዚህ አዲስ የበረራ አማራጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይጋብዛል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #አቴንስ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የበረራ ክፍል ባልደረቦቻችን ወደ አውሮፕላን ከመግባታቸው በፊት የሚያከናውኗቸው ተግባራት እና የሚያሟሏቸው ቅድመ ሁኔታዎች ምንድናቸው? በዛሬው የኢትዮጵያ መርሐግብር ይህንን ልናስቃኝዎ ወደናል፤ ይከታተሉን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአመታዊው የኡጋንዳ “ኢኩላ ቱሪዝም ሽልማት” የ2024ዓ.ም ምርጥ የቢዝነስ ክፍል ዘላቂ አገልግሎት (Best Sustainable Airline of 2024-Business Class Category) ሽልማትተቀዳጀ። መርሐግብሩ በካምፓላ ሸራተን ሆቴል የተካሄደ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለኡጋንዳ ቱሪዝም ኢንደስትሪ ዕድገት ላበረከተው የላቀ አስተዋፅዖ ሽልማቱ ተበርክቶለታል። በዚህ ዓመታዊ ሽልማት ለሀገሪቱ ቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት በጎ አሻራ ያሳረፉ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዕውቅና ይሰጣቸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን ምስለ በረራ (Flight Simulator) ቴክኖሎጂ ዘመኑ የደረሰባቸው ዘመናዊ ምስለ በራራዎች ባለቤት ሲሆን እነዚህ ምስለ በረራዎች በአውሮፕላኑ ላይ ተጨማሪ ስልጠና ሳያስፈልግ ወደ በረራ የመግባት ክህሎትን የሚያስጨብጡ የአቪዬሽኑ ኢንደስትሪ የልሕቀት ማሳያዎች ናቸው።”
ካፒቴን ፍሰሀ ተስፋዬ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፍላይት ኦፐሬሽን የስልጠና ክፍል ዳይሬክተር
https://www.youtube.com/watch?v=g3aigMvftMg&t=121s
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ኒውዮርክ ሲያደርገው የነበረውን አራት ሳምንታዊ በረራ በማሳደግ ከህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ከተማዋ እለታዊ በረራ የሚጀምር መሆኑን እያበሰረ ደንበኞች በድረ ገፅ www.ethiopianairlines.com አሊያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app በመጠቀም ትኬታቸውን ቆርጠው በዕለታዊ በረራ አገልግሎቱ እንዲጠቀሙ ይጋብዛል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላይቤሪያ ሞንሮቪያ የመንገደኞች በረራውን ዛሬ ህዳር 21 ቀን 2017 ዳግም ጀምሯል።

በፕሮግራሙ ላይ የላይቤርያ ትራንስፖርት ሚኒስትር ሰርሊፍ ቴይለር፣በኢትዮጵያ የላይቤርያ አምባሳደር ሉዊስ ሻሬን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማኔጅመንት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በአፍሪካ አቪዬሽን ኢንደስትሪ የመሪነት ሚና እየተጫወተ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን እርስ በርስ ብሎም ከተቀረው ዓለም ጋር የማገናኘት መርሁን ይበልጥ በማጠናከር በቅርብ ግዜ ወደ ፖርት ሱዳን እንዲሁም ባንግላዴሽ ዳካ በረራ የጀመረ ሲሆን በዛሬው ዕለት ወደ ላይቤሪያ ዋና ከተማ ሞንሮቪያ ዳግም በረራ ጀምሯል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ “Asian Infrastructure Investment Bank” (AIIB) ፕሬዝደንት ጂን ሊኩን የተመራ የልዑክ ቡድን በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅጥር ግቢ ተገኝቶ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እንዲሁም ከአየር መንገዳችን አመራር አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት አደረገ።

የልዑክ ቡድኑ ከውይይቱ በተጨማሪ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አጠቃላይ የስራ እስቅስቃሴ ተዘዋውሮ የጎበኘ ሲሆን አየር መንገዳችን በአፍሪካ አህጉር በመሪነት የሚጠቀስባቸውንና በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪነቱን ያስጠበቀባቸውን የስራ ክፍሎችና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎች ተመልክቷል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ