የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ከተማ ለሚያስገነባው ሜጋ ኤርፖርት ከዳር አል ሀንዳሽ የግንባታ አማካሪ ድርጅት ጋር የቴክኒካል፣ የአርክቴክቸር፣ የኢንጅነሪንግ እና ፕሮጀክት ማኔጅመንት ስምምነት ተፈራረመ። ይህ ግዙፍ ኤርፖርት በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኛ ማስተናገድ የሚያስችል አቅም ያለው ሲሆን ይህም ኤርፖርቱ አሁን በዓመት የሚስተናገደውን መንገደኛ ቁጥር በአራት እጥፍ ያሳድገዋል።
ይህ አዲስ ኤርፖርት የሚገነባበት ስፍራ ከመሬት ወለል ያለው ከፍታ (lower altitude) ዝቅተኛ በመሆኑ ለአውሮፕላኖች እንቅስቃሴ ምቹ የሆነና የኤርፖርቱ አጠቃላይ ግንባታም አካባቢያዊ ተስማሚነትን ጠብቆ የሚከናወን ይሆናል።
ለበለጠ ንባብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ: rb.gy/6mytah
ይህ አዲስ ኤርፖርት የሚገነባበት ስፍራ ከመሬት ወለል ያለው ከፍታ (lower altitude) ዝቅተኛ በመሆኑ ለአውሮፕላኖች እንቅስቃሴ ምቹ የሆነና የኤርፖርቱ አጠቃላይ ግንባታም አካባቢያዊ ተስማሚነትን ጠብቆ የሚከናወን ይሆናል።
ለበለጠ ንባብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ: rb.gy/6mytah
በፈረንሳይ ፓሪስ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሮ በፓሪስ ኦሎምፒክ ሀገራችንን ወክሎ የተሳተፈው የኦሎምፒክ ቡድን ትናንት ምሽት ከፓሪስ ቻርልስ ደጎል አለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ሲነሳ ደማቅ አሸኛኘት አድርጓል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ኮፐንሀገን፣ ዋርሳው እና አቴንስ የ” አንድ ትኬት ይግዙ አንድ በነፃ ይሸለሙ” ልዩ የጉዞ ጥቅል አዘጋጅቶ ይጠብቅዎታል። ይፍጠኑ የዚህ ልዩ ጥቅል ተጠቃሚ ይሁኑ! ትኬትዎን እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ይግዙ፤ በረራዎን ከመስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ሕዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም ያድርጉ። ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ዱባይ፣ ኢስታንቡል እና ጆሀንስበርግ ለሚጓዙ መንገደኞቹ የ500 ማይልስ ሽልማት እንካችሁ ይላል። አሁኑኑ ምዝገባዎን በመያዝ ጉዞዎን ከሽልማት ጋር ያድርጉ። #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የዛሬ አስራ ሁለት ዓመት ልክ በዛሬው ቀን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአፍሪካ የመጀመሪያውን የቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን ከቦይንግ ተረከበ። ይህ ዕለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአቪዬሽኑ ዓለም የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና ልህቀት ለአህጉራችን አፍሪካ በማስተዋወቅ ረገድ ያለውን ቁርጠኝነት እና ቀዳሚነት ያረጋገጠበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው። አሁንም ለመንገደኞች ደህንነት እና ምቾት መረጋገጥ ዘመኑ ያፈራቸውን አዳዲስ አውሮፕላኖች ስራ ላይ በማዋል በአፍሪካ ብሎም በዓለም ደረጃ ያለንን የመሪነት ሚና አጠናክረን እንቀጥላለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ድሪምላይነር
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ድሪምላይነር
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመብረር እንኳን ደህና መጡ። እኛን ምርጫዎ በማድረግ ዓለምን ይጎብኙ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሼባ ማይልስ ሲልቨር ደንበቾቹ የተለያዩ የመዝናኛ እና ማረፊያ አገልግሎት የሚሰጥ የሲልቨር ላውንጅ አስመርቆ ለአገልግሎት አበቃ። ይህ ላውንጅ የተከፈተው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ውስጥ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባ ማይልስ ሲልቨር ደንበኞች መንፈስን የሚያድሱና እና ዘና የሚያደርጉ አገልግሎቶች የሚያገኙበት ስፍራ ነው። ለተጨማሪ ንባብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://rb.gy/jqrjem
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ሼባማይልስ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ሼባማይልስ
መግለጫ
እ.ኤ.አ. ኦገስት 16 ቀን 2024 ዓ.ም. ጠዋት ከህንድ ሙምባይ ወደ አዲስ አበባ ለመብረር በዝግጅት ላይ ወደነበረ አውሮፕላን የሚጫኑ ሻንጣዎችን ይዞ ወደ አውሮፕላኑ በመጎተት ላይ በነበረ ጋሪ ላይ ከተጫኑ ሻንጣዎች በአንዱ እሳት ታይቷል። ክስተቱ ጋሪው ከራምፕ አካባቢ ወደ አውሮፕላኑ በመሄድ ላይ ሳለ እንደተከሰተ ተስተውሏል። ይህንንም ክስተት የተመለከቱ በሙምባይ ያሉ የደህንነት ፣ የጸጥታ እና የእሳት አደጋ ባለሞያዎች እሳት የያዘውን ሻንጣ በመለየት እሳቱን በቁጥጥር ስር አውለዋል። አውሮፕላኑ አስፈላጊው ተጨማሪ የደህንነት ፍተሻ ከተደረገለት በኋላ እና አስጊ ነገር አለመኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ በረራውን አካሂዷል።
የሙምባይ ኤርፖርት ባለስልጣናትና የሚመለከታቸው አካላት የክስተቱን ምንጭ በመመርመር ላይ በመሆናቸው ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን የምናሳውቅ ይሆናል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አልያንስ አባል
እ.ኤ.አ. ኦገስት 16 ቀን 2024 ዓ.ም. ጠዋት ከህንድ ሙምባይ ወደ አዲስ አበባ ለመብረር በዝግጅት ላይ ወደነበረ አውሮፕላን የሚጫኑ ሻንጣዎችን ይዞ ወደ አውሮፕላኑ በመጎተት ላይ በነበረ ጋሪ ላይ ከተጫኑ ሻንጣዎች በአንዱ እሳት ታይቷል። ክስተቱ ጋሪው ከራምፕ አካባቢ ወደ አውሮፕላኑ በመሄድ ላይ ሳለ እንደተከሰተ ተስተውሏል። ይህንንም ክስተት የተመለከቱ በሙምባይ ያሉ የደህንነት ፣ የጸጥታ እና የእሳት አደጋ ባለሞያዎች እሳት የያዘውን ሻንጣ በመለየት እሳቱን በቁጥጥር ስር አውለዋል። አውሮፕላኑ አስፈላጊው ተጨማሪ የደህንነት ፍተሻ ከተደረገለት በኋላ እና አስጊ ነገር አለመኖሩ ከተረጋገጠ በኋላ በረራውን አካሂዷል።
የሙምባይ ኤርፖርት ባለስልጣናትና የሚመለከታቸው አካላት የክስተቱን ምንጭ በመመርመር ላይ በመሆናቸው ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን የምናሳውቅ ይሆናል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የስታር አልያንስ አባል