Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
90.5K subscribers
3.58K photos
134 videos
2 files
399 links
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Download Telegram
የመልካም ሳምንት መልዕክት ለሁላችሁም!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በፈገግታ ታጅበዉ ከእኛ ጋር ይጓዙ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
መግለጫ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ዓርብ ወደ ደሴ (ኮምቦልቻ)፣ ጎንደር፣ ላሊበላ እና ባህርዳር የሚደረጉ በረራዎች የተሰረዙ መሆናቸውን ለክቡራን ደንበኞቹ ለመግለጽ ይወዳል፡፡
ወደሥፍራው ለመጓዝ ትኬት የቆረጣችሁ ክቡራን ደንበኞቻችን ትኬታችሁ ለአንድ ዓመት ያህል የሚያገለግል መሆኑን አውቃችሁ ወደፊት በፈለጋችሁት ቀን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ መቀየር የምትችሉ መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ነገር ግን ገንዘብ ተመላሽ እንዲሆንላችሁ የምትፈልጉ ክቡራን ደንበኞቻችን አቅራቢያችሁ ወዳሉ የአየር መንገዱ የትኬት መሸጫ ቢሮዎች ወይንም የጉዞ ወኪሎቻችሁ በመቅረብ መስተናገድ እንደምትችሉ በትህትና እንገልጻለን፡፡
አየር መንገዱ በዚህ ረገድ ለሚፈጠረው መጉላላት ልባዊ ይቅርታውን ያቀርባል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ይጎብኙ!
ነሐሴ 2 ቀን 2015 ዓ.ም.
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
መግለጫ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህር ዳር እና ጎንደር ከተሞች በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን እየገለጸ፣ ክቡራን መንገደኞቻችን በአቅራቢያችሁ በሚገኙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሽያጭ ቢሮዎች ወይም ወደጥሪ ማዕከላችን (6787/+251116179900) በመደወል መስተናገድ የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ይጎብኙ!
ነሐሴ 3 ቀን 2015 ዓ.ም.
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ በልዩ ልዩ የአቪዬሽን ዘርፎች የወጣ ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ! https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies
አብራሪዎች የቅድመ በረራ ፍተሻ በማድረግ ላይ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ትውስታ
መግለጫ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ደሴ (ኮምቦልቻ) በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን እየገለጸ፣ ክቡራን መንገደኞቻችን እንደተለመደው ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ወይም የሞባይል መተግበሪያዎቻችንን (https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app) በመጠቀም ለጉዟችሁ የሚያስፈልጉ ተግባራትን ካሉበት መከወን የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ተጨማሪ ዕገዛ የምትሹ መንገደኞቻችን በአቅራቢያችሁ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሽያጭ ቢሮዎች ወይም ወደጥሪ ማዕከላችን (6787) በመደወል መስተናገድ የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ይጎብኙ!

ነሐሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም.

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ወደሚወዱት መዳረሻዎ ልናደርስዎ ዝግጁ ነን!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
መግለጫ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረውን መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን እየገለጸ፣ ክቡራን መንገደኞቻችን እንደተለመደው ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ወይም የሞባይል መተግበሪያዎቻችንን (https://www.ethiopianairlines.com/aa/ethiopian-app) በመጠቀም ለጉዟችሁ የሚያስፈልጉ ተግባራትን ካሉበት መከወን የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ተጨማሪ ዕገዛ የምትሹ መንገደኞቻችን በአቅራቢያችሁ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሽያጭ ቢሮዎች ወይም ወደጥሪ ማዕከላችን (6787) በመደወል መስተናገድ የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናሳውቃለን፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ድረ-ገጻችንን (www.ethiopianairlines.com) ይጎብኙ!

የክቡራን መንገደኞቻችንን ፍላጎት በማጤን በድጋሚ ወደከፈትናቸው የአገር ውስጥ መዳረሻዎቻችን የበረራ ምልልሶቻችንን ለመጨመር ዝግጁ መሆናችንን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡


ነሐሴ 5 ቀን 2015 ዓ.ም.
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ባልተቋረጠ ትጋት እና ስኬት የደመቀ ጉዞ ! መልካም የስራ ሳምንት!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ET-AAP ዳግላስ DC-3 አውሮፕላን እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1968 ዓ.ም ኦሞ ብሔራዊ ፓርክ አካባቢ በሚገኝ አየር ማረፊያ ሲያርፍ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ትውስታ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አዲስ አፍሪካ ዓለም-አቀፍ ኮንቬንሽን እና ኤግዚቢሽን ማዕከል አ.ማ. ቱሪዝምንና ንግድን በማቀላጠፍ የአገር ገጽታን የሚገነባ፣ ዘርፈ ብዙ እና ዓለም አቀፍ የንግድ ሁነቶችን ለማስተናገድ የሚያስችል ዘመናዊ የኮንቬንሽን እና ኤግዚቢሽን ማዕከል በአዲስ አበባ ለማቋቋም የሚያስችላቸውን የጋራ የኢንቨስትመንት ስምምነት ተፈራረሙ።
ለተጨማሪ ንባብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://shorturl.at/AMNT5
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
ሁሌም በፈገግታ በታጀበው አገልግሎታችን ይደሰቱ።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አየር መንገዱ በቂሊንጦ 2 የኢንዱስትሪ ፓርክ የአውሮፕላን አካላትን የሚያመርትበት መሬት በሊዝ ለመረከብ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን አካላትን በማምረት ለቦይንግ ድርጅት እያቀረበ እንደሆነ ይታወቃል፤ ሆኖም ምርቱ እያደገ ስለሚሄድና ከዚህ በፊት ሲያመርታቸው ከነበረው የአውሮፕላን አካላት ተጨማሪ ሌሎች ምርቶችንም የማምረት ዕቅድ ስላለው ይህን ሰፊ ዕቅድ የሚመጥን የማምረቻ ስፍራ በኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባቱ አየር መንገዱ ምርቶቹን በስፋት ለማምረት፣ በዚህም ከፍተኛ የሆነ የስራ ዕድል ለመፍጠርና ከዘርፉም የሚያገኘውን የውጭ ምንዛሪ ለማሳደግ ያስችለዋል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለዚሁ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር የ15ሚለዮን ዶላር ኢንቨስትመንት የሚያደርግ ይሆናል፡፡
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ19ኛዉ የቡዳፔስት የዓለም አትሌትክስ ሻምፒዮና የሴቶች የ10 ሺ ሜትር ሩጫ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች ጉዳፍ ፀጋይ ወርቅ፣ ለተሰንበት ግደይ ብር እና እጅጋየሁ ታዬ ነሃስ በማምጣት ባስመዘገቡት አኩሪ ድል የተሰማውን ታላቅ ደስታ ይገልፃል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ