የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአመታዊው “APEX” የመንገደኞች ምርጫ “ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ “ ሽልማት አሸናፊ ሆነ። አየር መንገዳችን ሽልማቱን የተቀዳጀው በምርጥ የበረራ መስተንግዶ ዘርፍ ፣ በምርጥ የበረራ ላይ መዝናኛ ዘርፍ፣ በምርጥ የበረራ ላይ ምግብ እና መጠጥ ዘርፍ፣ በምርጥ የበረራ ላይ ምቾት ዘርፍ እንዲሁም በምርጥ የበረራ ላይ የገመድ ዓልባ ኢንተርኔት “Wi-Fi”አገልግሎት ዘርፍ ነው። ልማቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ዛሬ አየርላንድ ደብሊን ከተማ በተካሔደ የሽልማት አሰጣጥ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ተቀብለዋል።
ከ 145 በላይ መዳረሻዎች ከምርጥ ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ ጋር!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
በኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን ዩኒቨርስቲ ሰልጥነው ብቁ የአቪየሽን ባለሙያ ይሁኑ።
#የኢትዮጵያአቪዬሽንዩኒቨርስቲ
#የኢትዮጵያአቪዬሽንዩኒቨርስቲ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመታዊውን የሰራተኞች ቀን በደማቅ ሁኔታ አከበረ። በአከባበር ስነስርዓቱ ላይ የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ዋቄ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ፣ የአመራር አባላት ፣ ሰራተኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን የላቀ የስራ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞችም የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ