ማሳሰቢያ
እራሱን “እንቻለው ልጥገብ የአቪዬሽን ተቋም” ብሎ የሚጠራ ድርጅት ወይም ግለሰብ ሰራተኞችን ለቅጥር እንዲያቀርብ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፍቃድ የሰጠው በማስመሰል ሰዎችን በማሳሳት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የከፈተውን የሂሳብ አካውንት በመጠቀም ገንዘብ በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከተጠቀሰው ድርጅትም ይሁን ከየትኛውም ሰራተኞችን ለቅጥር ከሚያቀርብ ድርጅት ጋር የስራ ስምምነት የለውም፡፡ አየር መንገዱ ሰራተኞችን የሚቀጥረው በራሱ ዌብሳይት በመግለጽ ሲሆን ከተቀጣሪዎች ምንም አይነት ክፍያ አይቀበልም፡፡
በመሆኑም ስራ ፈላጊዎች በነዚህ ድርጅቶች ሳይታለሉ ለስራ ቅጥር መረጃዎች የአየር መንገዳችንን ድረገጽ https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers እንዲከታተሉ እናሳስባለን፡፡
እራሱን “እንቻለው ልጥገብ የአቪዬሽን ተቋም” ብሎ የሚጠራ ድርጅት ወይም ግለሰብ ሰራተኞችን ለቅጥር እንዲያቀርብ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፍቃድ የሰጠው በማስመሰል ሰዎችን በማሳሳት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የከፈተውን የሂሳብ አካውንት በመጠቀም ገንዘብ በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከተጠቀሰው ድርጅትም ይሁን ከየትኛውም ሰራተኞችን ለቅጥር ከሚያቀርብ ድርጅት ጋር የስራ ስምምነት የለውም፡፡ አየር መንገዱ ሰራተኞችን የሚቀጥረው በራሱ ዌብሳይት በመግለጽ ሲሆን ከተቀጣሪዎች ምንም አይነት ክፍያ አይቀበልም፡፡
በመሆኑም ስራ ፈላጊዎች በነዚህ ድርጅቶች ሳይታለሉ ለስራ ቅጥር መረጃዎች የአየር መንገዳችንን ድረገጽ https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers እንዲከታተሉ እናሳስባለን፡፡
👍101❤39🥰16
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲበሩ በካሜራዎ ያስቀሩትን ምስል በመልዕክት መቀበያ ሳጥናችን በኩል ይላኩልን ፤ መልሰን እናጋራዎታለን።
#የመስኮትምልከታ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የመስኮትምልከታ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
❤71👍38😍16🥰12🎉1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአለም የንግድ ማዕከልነታቸው ከሚጠቀሱት መካከል አንዷ ወደሆነችው ሲንጋፖር ከተማ በሳምንት አራት ግዜ የሚያደርገውን በረራ እንደገና ጀምሯል። ቻንጊ አለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ( Changi Airport) ሲደርስም ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍81❤29🎉9🥰8👏6
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይና መብረር የጀመረበትን 50ኛ ዓመት አከበረ። አየር መንገዳችን ወደ ሻንግሀይ ከተማ የካቲት 14 ቀን 1965 ዓ.ም የመጀመሪያ የቻይና በረራውን በማድረግ አገልግሎቱን የጀመረ ሲሆን ከጥቅምት 28 ቀን 1966 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ መዳረሻውን ወደ ቤጂንግ ከተማ በመቀየር አገልግሎን ቀጥሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በ5 የመንገደኛ እና 9 የእቃ ጭነት መደበኛ በረራዎች በአጠቃላይ 66 ሳምንታዊ በረራዎችን ወደ 10 የቻይና ከተሞች ማለትም ቤጂንግ፣ ጓንዡ፣ ሼንጁ፣ሻንግሀይ፣ ሸንዘን ፣ ውሀን፣ቻንግሻ፣ዢያመን፣ቸንዱ እና ሆንግ ኮንግ ያደርጋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት በ5 የመንገደኛ እና 9 የእቃ ጭነት መደበኛ በረራዎች በአጠቃላይ 66 ሳምንታዊ በረራዎችን ወደ 10 የቻይና ከተሞች ማለትም ቤጂንግ፣ ጓንዡ፣ ሼንጁ፣ሻንግሀይ፣ ሸንዘን ፣ ውሀን፣ቻንግሻ፣ዢያመን፣ቸንዱ እና ሆንግ ኮንግ ያደርጋል።
❤47👍34🎉6😍4👏2🥰1