በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 34(1) ላይ ተጋቢዎች በትዳር ዘመናቸው በሁሉ ነገር ላይ እኩል መብት እንዳላቸው ይገልፃል፡፡ እንዲሁም በአንቀፅ 35(7) ላይ ሴቶች ንብረት በማስተዳደር ከወንዶች ጋር እኩል መብት አላቸው በማለት ደንግጎአል፡፡ እነኚህ የህገ መንግስቱ መርሆች በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀፅ 66(1)ላይ በማካተት ባልና ሚስቱ የጋራ ሀብታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ በማለት ገልጾታል፡፡ ስለዚህም በመርህ ደረጃ ባልና ሚስት የጋራ ንብረታቸውን በጋራ ያስተዳድራሉ፡፡ነገር ግን ባልና ሚስቱ በስምምነት የጋራ ንብረታቸውን አንዳቸው እንዲያስተዳድሩ ማድረግ ይችላሉ፡፡ይህም በውል ለአንደኛው ወገን እንዲያስተዳድር ሲሰጥ ነው፡፡ በተለያየ አጋጣሚ (ምክነያት) ከተጋቢዎች አንዱ ችሎታ ሲያጣ ወይም ንብረት የማስተዳደር መብቱ በፍ/ቤት ሊገፈፍ ይችላል፡፡ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሌላኛው ተጋቢ ንብረቱን የማስተዳደር ተግባር ያከናውናል፡፡ በውልም ሆነ ንብረት የማስተዳደር መብቱ በመገፈፉ ወይም ችሎታ በማጣቱ አንደኛው ተጋቢ ንብረቱን በሚያስተዳድርበት ጊዜ ሌላኛው ንብረቱን የሚያስተዳድረው ተጋቢ የንብረቱን አስተዳደር በተመለከተ ለሌላኛው ተጋቢ መረጃ የመስጠት ግዴታ እንዳለበት በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀፅ 67 ላይ ተቀምጧል፡፡
ተጋቢዎች በትዳር ተሳስረው የጋራ ንብረት አፍርተው ሲኖሩ ይህን የጋራ ንብረት በጋራ ማስተዳደር እንዳለባቸው ከላይ በተገለጸው መልኩ ለመረዳት ችለናል፡፡ እነዚህን የጋራ ንብረቶች ተጋቢዎቹ በጋራ በሚያስተዳድሩበት ወቅት ንብረቱን መሸጥ መለወጥ ያስፈልጋቸው ይሆናል፡፡ ይህ ጋራ ንብረት መሸጥ መለወጥ ከፈለጉ በሌላ የሕግ የተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር የተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት አስፈላጊ ነው፡፡ በአንቀጽ 68 የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው የጋራ ንብረትና ሀብት ወደሌላ ሶስተኛ ወገን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የሚቀየረው በተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት ብቻ መሆኑን ይገልፃል፡፡ እዚህ ላይ በጋራ ንብረት የሆነውን አንደኛው ተጋቢ ሌላኛውን ተጋቢ ፈቃድ ወይም ስምምነት ሳያገኝ ብቻውን ለሌላ 3ኛ ወገን በሽያጭም ሆነ በሌላ መንገድ ቢያስተላልፍ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው እንዲፈርስ መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህ ግዴታ እንደፈረሰ የሚጠይቀው ተጋቢ ለፍ/ቤት ጥያቄውን የሚያቀርበው ግዴታው መገባቱን ካወቀበት ቀን ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ወይም በሌላ በማንኛውም ሁኔታ በ2 አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ይህ የተባለው ጊዜ ካለፈ ይህን ጥያቄ ማቅረብ እንደማይቻል በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 69(2) ላይ ተገልፆል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 38126 በአመልካች ዲያቆን ኃ/ጊዮርጊስ ወንድም እና ተጠሪዎች እነ የሺ ተፈሪ መካከል በነበረው ክርክር የአሁኑ 2ኛ ተጠሪ ከ1ኛ ተጠሪ ባለቤት ከሆኑት የጋራ ንብረታቸው የሆነውን ቤት ለአሁኑ አመልካች በ01/03/1995 ዓ.ም ያለ 1ኛ ተጠሪ ፍቃድ ይሸጥለታል፡፡ 1ኛ ተጠሪም በስር ፍርድ ቤት ውሉ ያለ እሳቸው ፍቃድ የተፈጸመ በመሆኑ እነዲፈርስ በማለት በ09/08/1999 ዓ.ም ክስ ታቀርባለች፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰበር ችሎት የአሁን 1ኛ ተጠሪ የሆነችው ክስ ያቀረበችው በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 69/2/ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ማለትም ሽያጩን ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ወይም በማንኛውም ሁኔታ በ2 አመት ጊዜ ውስጥ ክሶን ያላቀረበች ስለሆነ (ክሶን ያቀረበችው ከ4 አመት በሆላ ነው) ውሉ እንዲፈርስ ክስ የማቅረያ ጊዜ አልፎል፡፡ ስለሆነም ውሉ አይፈርስም በማለት ውሳኔ ሰጥቶላ፡፡
የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ ሲኖር እለት በለት ኑሮውን ለመደጎም ወጪዎችን ያወጣል፡፡ በትዳር ውስጥም ተጋቢዎ ትዳራቸውን ለማቃናትና ዘላቂነቱን ለማስቀጠል የተለያዩ ወጪዎች ማውጣታቸው የማይቀር ሀቅ ነው፡፡ በመሆኑም ተጋቢዎች የትዳራቸውን ወጪ ለመሸፈን እያንዳንዳቸው እንዳቅማቸውና ችሎታቸው አስተዋፅኦ የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡ የህይወት መንገድ ሁልጊዜም አልጋ በአልጋ አይሆንም ውጣ ውረድ በህይወት ውስጥ ማጋጠሙ አይቀርም፡፡ በዚህ ጊዜ ወደ ብድር እና እዳ መገባት ሊያጋጥም ይችላል፡፡ በትዳር ውስጥም ተጋቢዎቹ ለግላቸው ወይም ለትዳራቸው ሲሉ እዳ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሆነበት ጊዜ እዳውን ለመክፈል እዳው ለግል የተወሰደ ከሆነ ከባለእዳው ተጋቢ የግል ሀብት ይሸፈናል፡፡ ነገር ግን የግል ሀብቱ ይህን ለመሸፈን የማይችል ከሆነ ተጋቢዎች የመረዳዳትና የመተጋገዝ ግዴታ ስላለባቸው ይህ እዳ ከጋራ ሀብታቸው ይከፈላል፡፡ እዳው ግን ለትዳራቸው ጥቅም ከሆነ ከጋራ ሀብታቸው የሚከፈል ይሆናል፡፡ ነገር ግን የጋራ ሀብቱ በቂ ካልሆነ ከተጋቢወቹ የግል ሀብት ይከፈላል፡፡
#legalconsulting limited
@lawsocieties
@lawsocieties https://t.me/lawsocieties
ተጋቢዎች በትዳር ተሳስረው የጋራ ንብረት አፍርተው ሲኖሩ ይህን የጋራ ንብረት በጋራ ማስተዳደር እንዳለባቸው ከላይ በተገለጸው መልኩ ለመረዳት ችለናል፡፡ እነዚህን የጋራ ንብረቶች ተጋቢዎቹ በጋራ በሚያስተዳድሩበት ወቅት ንብረቱን መሸጥ መለወጥ ያስፈልጋቸው ይሆናል፡፡ ይህ ጋራ ንብረት መሸጥ መለወጥ ከፈለጉ በሌላ የሕግ የተለየ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር የተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት አስፈላጊ ነው፡፡ በአንቀጽ 68 የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው የጋራ ንብረትና ሀብት ወደሌላ ሶስተኛ ወገን በሽያጭ ሆነ በስጦታ የሚቀየረው በተጋቢዎቹ የጋራ ስምምነት ብቻ መሆኑን ይገልፃል፡፡ እዚህ ላይ በጋራ ንብረት የሆነውን አንደኛው ተጋቢ ሌላኛውን ተጋቢ ፈቃድ ወይም ስምምነት ሳያገኝ ብቻውን ለሌላ 3ኛ ወገን በሽያጭም ሆነ በሌላ መንገድ ቢያስተላልፍ ሌላኛው ተጋቢ ለፍርድ ቤት በሚያቀርበው ጥያቄ ግዴታው እንዲፈርስ መጠየቅ ይችላል፡፡ ይህ ግዴታ እንደፈረሰ የሚጠይቀው ተጋቢ ለፍ/ቤት ጥያቄውን የሚያቀርበው ግዴታው መገባቱን ካወቀበት ቀን ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ወይም በሌላ በማንኛውም ሁኔታ በ2 አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ይህ የተባለው ጊዜ ካለፈ ይህን ጥያቄ ማቅረብ እንደማይቻል በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 69(2) ላይ ተገልፆል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 38126 በአመልካች ዲያቆን ኃ/ጊዮርጊስ ወንድም እና ተጠሪዎች እነ የሺ ተፈሪ መካከል በነበረው ክርክር የአሁኑ 2ኛ ተጠሪ ከ1ኛ ተጠሪ ባለቤት ከሆኑት የጋራ ንብረታቸው የሆነውን ቤት ለአሁኑ አመልካች በ01/03/1995 ዓ.ም ያለ 1ኛ ተጠሪ ፍቃድ ይሸጥለታል፡፡ 1ኛ ተጠሪም በስር ፍርድ ቤት ውሉ ያለ እሳቸው ፍቃድ የተፈጸመ በመሆኑ እነዲፈርስ በማለት በ09/08/1999 ዓ.ም ክስ ታቀርባለች፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰበር ችሎት የአሁን 1ኛ ተጠሪ የሆነችው ክስ ያቀረበችው በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 69/2/ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ማለትም ሽያጩን ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ወይም በማንኛውም ሁኔታ በ2 አመት ጊዜ ውስጥ ክሶን ያላቀረበች ስለሆነ (ክሶን ያቀረበችው ከ4 አመት በሆላ ነው) ውሉ እንዲፈርስ ክስ የማቅረያ ጊዜ አልፎል፡፡ ስለሆነም ውሉ አይፈርስም በማለት ውሳኔ ሰጥቶላ፡፡
የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ ሲኖር እለት በለት ኑሮውን ለመደጎም ወጪዎችን ያወጣል፡፡ በትዳር ውስጥም ተጋቢዎ ትዳራቸውን ለማቃናትና ዘላቂነቱን ለማስቀጠል የተለያዩ ወጪዎች ማውጣታቸው የማይቀር ሀቅ ነው፡፡ በመሆኑም ተጋቢዎች የትዳራቸውን ወጪ ለመሸፈን እያንዳንዳቸው እንዳቅማቸውና ችሎታቸው አስተዋፅኦ የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡ የህይወት መንገድ ሁልጊዜም አልጋ በአልጋ አይሆንም ውጣ ውረድ በህይወት ውስጥ ማጋጠሙ አይቀርም፡፡ በዚህ ጊዜ ወደ ብድር እና እዳ መገባት ሊያጋጥም ይችላል፡፡ በትዳር ውስጥም ተጋቢዎቹ ለግላቸው ወይም ለትዳራቸው ሲሉ እዳ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሆነበት ጊዜ እዳውን ለመክፈል እዳው ለግል የተወሰደ ከሆነ ከባለእዳው ተጋቢ የግል ሀብት ይሸፈናል፡፡ ነገር ግን የግል ሀብቱ ይህን ለመሸፈን የማይችል ከሆነ ተጋቢዎች የመረዳዳትና የመተጋገዝ ግዴታ ስላለባቸው ይህ እዳ ከጋራ ሀብታቸው ይከፈላል፡፡ እዳው ግን ለትዳራቸው ጥቅም ከሆነ ከጋራ ሀብታቸው የሚከፈል ይሆናል፡፡ ነገር ግን የጋራ ሀብቱ በቂ ካልሆነ ከተጋቢወቹ የግል ሀብት ይከፈላል፡፡
#legalconsulting limited
@lawsocieties
@lawsocieties https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/