የኪራይ ቤቶችን ዋጋ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል!
ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶችን ዋጋ ደረጃ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ተናገሩ።በተለይ በከተሞች ያለው የመኖሪያ ቤት ከራይ መወደድና የአከራይና ተከራይ ጭቅጭቅ መላ ሊበጅለት እንደሚገባ በርካቶች ያምናሉ።
ለችግሩ እልባት ለመስጠት ተዘጋጅቶ ሚኒስትሮች ምክር ቤት የደረሰው ረቂቅ አዋጅ፥ የኪራይ ውል ጊዜን ከመወሰን ባለፈ ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቧቸውን መሰረተ ልማቶች በግልጽ ያስቀምጣል ብለዋል።በረቂቅ አዋጁ እንደተቀመጠውም አከራዮች የኪራይ ዋጋ መጨመር ሲፈልጉ በምን ያህል ጊዜና ምን ያህል የሚለውም ተለይቷል።ተከራዮችም በኪራይ የወሰዷቸውን ቤቶች በአግባቡ መያዝ እንደሚገባቸውና ሌሎች ግዴታዎቻቸውንም አስፍሯል ነው የተባለው።
ረቂቅ አዋጁ በደላሎች የሚዘወረውን የኪራይ ቤቶች ዋጋና አቅርቦት በማስተካከል አከራይንና ተከራይን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ይታደጋልም ተብሎ ታምኖበታል።የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒም ረቂቅ አዋጁ በዚህ አመት ፀድቆ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው የተናገሩት።
Via #EthiopiaBusinessDaily
ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶችን ዋጋ ደረጃ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ተናገሩ።በተለይ በከተሞች ያለው የመኖሪያ ቤት ከራይ መወደድና የአከራይና ተከራይ ጭቅጭቅ መላ ሊበጅለት እንደሚገባ በርካቶች ያምናሉ።
ለችግሩ እልባት ለመስጠት ተዘጋጅቶ ሚኒስትሮች ምክር ቤት የደረሰው ረቂቅ አዋጅ፥ የኪራይ ውል ጊዜን ከመወሰን ባለፈ ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቧቸውን መሰረተ ልማቶች በግልጽ ያስቀምጣል ብለዋል።በረቂቅ አዋጁ እንደተቀመጠውም አከራዮች የኪራይ ዋጋ መጨመር ሲፈልጉ በምን ያህል ጊዜና ምን ያህል የሚለውም ተለይቷል።ተከራዮችም በኪራይ የወሰዷቸውን ቤቶች በአግባቡ መያዝ እንደሚገባቸውና ሌሎች ግዴታዎቻቸውንም አስፍሯል ነው የተባለው።
ረቂቅ አዋጁ በደላሎች የሚዘወረውን የኪራይ ቤቶች ዋጋና አቅርቦት በማስተካከል አከራይንና ተከራይን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ይታደጋልም ተብሎ ታምኖበታል።የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒም ረቂቅ አዋጁ በዚህ አመት ፀድቆ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው የተናገሩት።
Via #EthiopiaBusinessDaily