አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የኪራይ ቤቶችን ዋጋ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል!

ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶችን ዋጋ ደረጃ ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ በዚህ አመት ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ተናገሩ።በተለይ በከተሞች ያለው የመኖሪያ ቤት ከራይ መወደድና የአከራይና ተከራይ ጭቅጭቅ መላ ሊበጅለት እንደሚገባ በርካቶች ያምናሉ።

ለችግሩ እልባት ለመስጠት ተዘጋጅቶ ሚኒስትሮች ምክር ቤት የደረሰው ረቂቅ አዋጅ፥ የኪራይ ውል ጊዜን ከመወሰን ባለፈ ለኪራይ የሚዘጋጁ ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቧቸውን መሰረተ ልማቶች በግልጽ ያስቀምጣል ብለዋል።በረቂቅ አዋጁ እንደተቀመጠውም አከራዮች የኪራይ ዋጋ መጨመር ሲፈልጉ በምን ያህል ጊዜና ምን ያህል የሚለውም ተለይቷል።ተከራዮችም በኪራይ የወሰዷቸውን ቤቶች በአግባቡ መያዝ እንደሚገባቸውና ሌሎች ግዴታዎቻቸውንም አስፍሯል ነው የተባለው።

ረቂቅ አዋጁ በደላሎች የሚዘወረውን የኪራይ ቤቶች ዋጋና አቅርቦት በማስተካከል አከራይንና ተከራይን ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ይታደጋልም ተብሎ ታምኖበታል።የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒም ረቂቅ አዋጁ በዚህ አመት ፀድቆ ወደ ስራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው የተናገሩት።
Via #EthiopiaBusinessDaily