አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Eelaa:
የቴልኮም ማጭበርበር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ፦

ተከሳሽ #ኤልያስ_አብዱርቃድር የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሕጋዊ ፈቃድ ሳይኖረው በህገ-ወጥ መንገድ ዓለም አቀፍ ጥሪ በማስተላለፍ የኢትዮ ቴሌኮምን ከ518 ሺ ብር በላይ እንዲያጣ በማድረጉ በፈፀመው ወንጀል በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ፡፡

ተከሳሽ #የቴሌኮም መሳሪያዎችን ወደ ሀገር ዉስጥ ለማስገባትና ለመጠቀም ብሎም የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሕጋዊ ፈቃድ ሳይኖረው በኮልፌ ቀራኒዎ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ቤት በመከራየት የዲንስታር ጌትዌይ የስልክ መደወያና ቲፒ ሊንክ የሚባል የቴሌኮም መሳሪያዎችን በመጠቀም የቴሌኮም አገልግሎት በመስጠት ከሐምሌ 2010 እስከ ታህሳስ 12 ቀን 2011 ዓ.ም ባለው ጊዜ 95,378.73 ደቂቃ ከውጭ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ አለም አቀፍ የስልክ ጥሪዎችን በማስተላለፍ ኢትዮ ቴሌኮም ያገኝ የነበረዉን 18,121.96 ዶላር ወይም 518,568.70 ብር እንዲያጣ በማድረጉ በቴሌኮም ማጭበርበር አዋጅ ቁጥር 761/2004 አንቀፅ 9 (1ለ) ስር የተመለከተውን የወንጀል ድርጊት በመተላለፍ የተከሰሰ መሆኑን የዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ ያስረዳል፡፡ ዐቃቤ ሕግም የሰው ምስክሮች፣ የሰነድና የኢግዚቢት ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ በማቅረብ ተከራክሯል፡፡

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 20ኛ የወንጀል ችሎት መዝገቡን መርምሮ፣ ተከሳሽን በፈፀመው ወንጀል ጥፋተኛ በማለት ሰኔ 28 ቀን 2011 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ10 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ500 ሺ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ሲል ወስኗል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia