አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የሕዝብ_በዓላት_እና_የበዓላት_አከባበር_ረቂቅ_አዋጅ_.pdf
420.3 KB
" የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀ ረቂቃ አዋጅ " ምን ይዟል ?

የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ ተከብረው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ናቸው ፡-

1. መስከረም አንድ ቀን የዘመን መለወጫ (እንቁጣጣሽ) በዓል
2. የካቲት ሃያ ሶስት ቀን የአድዋ ድል በዓል
3. ሚያዚያ ሃያ ሶስት ቀን የዓለም የሠራተኞች (የላብአደሮች) ቀን
4. ሚያዚያ ሃያ ሰባት ቀን የአርበኞች (የድል) ቀን በዓል

በተጠቀሱት ብሔራዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ይሆናሉ፡፡

የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ ታስበው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ናቸው ፡-

1. የካቲት አስራ ሁለት ቀን የሰማዕታት ቀን
2. ሕዳር ሃያ ዘጠኝ ቀን የኢትዮጵያ ህብረ-ብሄራዊነት (የብሔር ብሔረሰቦች) ቀን

በተጠቀሱት ብሔራዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት ይሆናሉ፡፡

የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ የሚከበሩ ኃይማኖታዊ በዓላት ናቸው ፡-

1. መስከረም አስራ ሰባት ቀን የመስቀል በዓል
2. በየአራት አመቱ የሚመጣው ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ታህሳስ ሃያ ዘጠኝ ቀን የሚውለው የገና ወይም የልደት በዓል
3. ጥር አስራ አንድ ቀን የጥምቀት በዓል
4. የስቅለት በዓል
5. የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓል
6. የኢድ-አልአድሃ (አረፋ) በዓል
7. የመውሊድ በዓል
8. የኢድ አልፈጥር በዓል

በተጠቀሱት ኃይማኖታዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ይሆናሉ።

⚠️ ይህ ገና ረቂቅ አዋጅ ሲሆን ገና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት #አልጸደቀም። ረቂቅ አዋጁ በም/ቤት ሲጸድቅና በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ ነው የጸና የሚሆነው።

ከላይ በተያያዘው ፋይል ሙሉውን ያንብቡ።

@tikvahethiopia