ከአሜሪካን ጠበቆች ማህበር American Bar Association /ABA/ ጋር ውይይት ተደረገ
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ተ/ፕሬዚደንት እና የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት ም/ፕሬዚደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው በአሜሪካን ሀገር ለግል ስራቸው በነበሩበት ከአሜሪካን የጠበቆች ማህበር American Bar Association (ABA) አመራሮች ጋር ጠቃሚ ውይይት ማድረጋቸውን ገለፁ::
በእለቱም ከአሜሪካን የጠበቆች ማህበር የመካከለኛው ምስራቅ እና የአፍሪካ አካባቢያዊ ሀላፊ ከሆኑት #ብሌርታ ፒካሪ እና የኢንተርናሽናል ዴስክ ከሆኑት ጠበቃ ታይለር የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ከአሜሪካ የጠበቆች ማህበር ABA ጋር በትብብር ሊያከናውኗቸው በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል::
በውይይታቸውም ሊደረጉ ስለሚችሉ የአቅም ግንባታ እና ተቋማዊ ድጋፎች ፤ የተከታታይ የህግ ስልጠና ትብብሮች ፤ በጥናትና ምርምር ዘርፍ፤ በህግ የበላይነት ዙሪያ ሊከናወኑ ስለሚችሉ ተግባራት ፤ በግልግል ዳኝነት መሰል ተያያዥ ርእሶች እንዲሁም በአጠቃላይ ተቋማዊ የልምድ ልውውጥ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል::
እነዚህም በተለያየ መልኩ መግባባት ላይ የተደረሰባቸው ሆነው በቀጣይ ግንኙነቱ ቀጥሎ ወደ መግባቢያ ስምምነት MoU ማደግ እንደሚችሉና እንደሚገባ በአጠቃላይም ግንኙነቱ በዚህ መልኩ መጀመሩ በጣም አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል::
ABA ከተመሰረተ 140 አመት በላይ የሆነውና 400 ሺህ የሚጠጉ አባላትን የያዘ ከአሜሪካና አውሮፓ አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ ተፅእኖ ፈጣሪ የሙያ ማህበር መሆኑ ይታወቃል::
ቴዎድሮስ በአጭር ግዜ ጥያቄ ከአሜሪካን የጠበቆች ማህበር ጋር ለውይይት ያቀረቡት ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ በማግኘቱ እና ለዚህም ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ተ/ፕሬዚደንት እና የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት ም/ፕሬዚደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው በአሜሪካን ሀገር ለግል ስራቸው በነበሩበት ከአሜሪካን የጠበቆች ማህበር American Bar Association (ABA) አመራሮች ጋር ጠቃሚ ውይይት ማድረጋቸውን ገለፁ::
በእለቱም ከአሜሪካን የጠበቆች ማህበር የመካከለኛው ምስራቅ እና የአፍሪካ አካባቢያዊ ሀላፊ ከሆኑት #ብሌርታ ፒካሪ እና የኢንተርናሽናል ዴስክ ከሆኑት ጠበቃ ታይለር የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ከአሜሪካ የጠበቆች ማህበር ABA ጋር በትብብር ሊያከናውኗቸው በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል::
በውይይታቸውም ሊደረጉ ስለሚችሉ የአቅም ግንባታ እና ተቋማዊ ድጋፎች ፤ የተከታታይ የህግ ስልጠና ትብብሮች ፤ በጥናትና ምርምር ዘርፍ፤ በህግ የበላይነት ዙሪያ ሊከናወኑ ስለሚችሉ ተግባራት ፤ በግልግል ዳኝነት መሰል ተያያዥ ርእሶች እንዲሁም በአጠቃላይ ተቋማዊ የልምድ ልውውጥ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል::
እነዚህም በተለያየ መልኩ መግባባት ላይ የተደረሰባቸው ሆነው በቀጣይ ግንኙነቱ ቀጥሎ ወደ መግባቢያ ስምምነት MoU ማደግ እንደሚችሉና እንደሚገባ በአጠቃላይም ግንኙነቱ በዚህ መልኩ መጀመሩ በጣም አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል::
ABA ከተመሰረተ 140 አመት በላይ የሆነውና 400 ሺህ የሚጠጉ አባላትን የያዘ ከአሜሪካና አውሮፓ አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ ተፅእኖ ፈጣሪ የሙያ ማህበር መሆኑ ይታወቃል::
ቴዎድሮስ በአጭር ግዜ ጥያቄ ከአሜሪካን የጠበቆች ማህበር ጋር ለውይይት ያቀረቡት ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ በማግኘቱ እና ለዚህም ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል::