አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በአከራይ ተከራይ መመሪያ 7/2016 ዙሪያ አንቀፅ 22 ስለአስተዳደራዊ እርምጃ እና ቅጣት ለግንዛቤ የተወሰደ

አስተዳደራዊ ቅጣት 👇

ማንኛውም አከራይ ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ የመኖሪያ ቤት ያለ አገልግሎት እንዲቀመጥ ያደረገ እንደሆነ:-

ሀ/ ከአንድ እስከ ሁለት ዓመት 5%፤
ለ/ከሁለት በላይ እስከ ሶስት ዓመት 10%፤
ሐ/ከሶስት በላይ እስከ አራት ዓመት 15%፤
መ/ከአራት እስከ አምስት ዓመት 20%፤
ሠ/ ከአምስት አመት በላይ 25%፤

በንብረት ግብር ክፍያ ላይ ተጨማሪ እንደ ቅጣት እንዲከፍል ይደረጋል።

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
Forwarded from ስለፍትሕ (Entrust and PIN)
አዲሱ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ሞዴል ውል.pdf
262.4 KB
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሚኒስትሮች ም/ቤት ፀድቀው ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት እየቀረቡ ያሉ አዳዲስ አዋጆች እናየአዋጅ ማሻሻያ ሃሳቦች በተለያዩ የሰብዓዊ መብቶች ላይ ጫና የሚያደረጉ፤ የአስፈፃሚዉን አካል ሥልጣን ከሚገባው በላይየሚያጠናክሩ፤ በአንፃሩ ደግሞ የዳኝነት አካሉን ሚና ዝቅ የሚያደርጉ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል፡፡
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በሴራሊዮን ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ልጃገረዶችን ማግባት እስከ 15 ዓመት እስራት ሊያስቀጣ ነው፤ በኢትዮጵያስ?

የሴራሊዮን ፓርላማ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ልጃገረዶችን ማግባት እስከ 15 ዓመት እስራት በሚደርስ የወንጀል ጥፋት እና ከ2,000 ዶላር ጋር የሚመጣጠን ቅጣት የሚጥል ህግ አጽድቋል።

በተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) መሰረት በሴራሊዮን ከሚገኙት ወጣት ሴቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ያህሉ የተዳሩት 18 ዓመት ሳይሞላቸው ነው።

እንደ ዩኒሴፍ መረጃ በሀገሪቱ 800,000 የሚሆኑ እድሜያቸው ሳይደርስ የተዳሩ ሴቶች ያሉ ሲሆን 400,000 የሚያህሉት ጋብቻ የፈጸሙት ከ15 ዓመታቸው በፊት ነው።

የሴራሊዮን ፓርላማ ያጸደቀው ህግ ከኢትዮጵያ ሲነጻጸር፦

እንደ ዩኒሴፍ መረጃ በኢትዮጵያ ከ15 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ እድሜያቸው ሳይደርስ የተዳሩ ሴቶች ያሉ ሲሆን 6 ሚሊየኑ ጋብቻ የፈጸሙት ከ15 ዓመታቸው በፊት ነው።

በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ መሰረት ለጋብቻ ዝቅተኛው እድሜ ለሁለቱም ጾታዎች 18 ዓመት ሆኖ ተቀምጧል። የወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ደግሞ ያለ እድሜ ጋብቻ ላይ ከ3 እስከ 7 ዓመት እስራት የሚደርስ ቅጣት ያስቀምጣል።

@tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia

የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ፣ ካሳ የሚከፈልበት እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበት አዋጅ በ4 ተቃውሞ በ6 ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል።

አዋጁ ፤ ከዚህ በፊት በልማት ተነስተው የካሳ ክፍያ ያላገኙትን እና አሁንም ድረስ እየጠበቁ ያሉ የልማት ተነሺ ሰዎችን እንደማያካትት ተሰምቷል።
 
ከምክር ቤት አባላት ምን ተጠየቀ ? ምን ምላሽ ተሰጠ ?

Q. ከዚህ በፊት በርካታ የካሳ ክፍያዎች አዲሱ የካሳ ክፍያ እና ተነሺዎች መልሶ የሚቋቋሙበት አዋጅ እስከ ሚፀድቅ ድረስ እንዲቆዩ ተደርገዋል ይህ አዋጅ እንዴት ሊያስተናግዳቸው አስቧል ?
 
Q. ካሳ የመክፈሉ ኃላፊነት ለክልሎች በአዲሱ አዋጅ መስጠቱ ለሰራተኞቻቸው እንኳን ደሞዝ መክፈል ያልቻሉ ክልሎች ባሉበት ሰዓት እንዴት እንዲህ አይነት ክፍያ ሊከፍሉ ይችላል ?

Q. አንዳንድ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች በተመለከተ ለፌደራል የመጀመሪያ ፍ/ቤት መስጠቱ አግባብነት የለውም። ይህ እንዴት ሊታይ ታስቦ ነው ለከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ችግሮችን ለማየት ስልጣን የተሰጠው ?


ሌላው ፤ ከዚህ በፊት ከፍተኛ የሆነ ምዝበራ ይፈፀም የነበረው በክልሎችና በወረዳዎች በሚጣሉ የካሳ ተመኖች ነበር አዋጁ ይህ እንዲባባስ ሊያደር ይችላል የሚል ስጋት ተነስቷል።
 
በተ/ም/ቤት የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፥ ከዚህ በፊት ከልማት ጋር በተያያዘ ያልተከፈሉ ክፍያዎች የሚዳኙት በቀድሞ አዋጅ መሰረት ነው ብለዋል።

አዲሱ አዋጅ የሚመለከተው ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ያሉ የካሳ ክፍያዎች ብቻ እንደሆነ ገልጸዋል።
 
በክልሎች ያለው በጀት ጉድለት እንዳለ ሆኖ ለልማት ተነሺዎች የሚከፈለው የካሳ ክፍያ የሚፈፀመው የፌደራል መንግስት ለክልሎች በሚሰጠው የበጀት ድጎማ እንደሆነ ተመላክቷል።

በክልሎች አዳዲስ ፕሮጀክቶች ሲታቀዱ ለክልሎች የሚመደበው በጀት ላይ የካሳ ክፍያ ታሳቢ ይሆናል።
 
ከዳኙነቱ ጋር በተያያዘም ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ሌላኛው የቋሚ ኮሚቴ አባል ፤ " ውሳኔውን ለመስጠት የተፈለገው ልማቶች ሲካሄዱ ፈጣን ፍርድ ለማሰጠትና ሀብትን ከምዝበራ ለመታደግ በማሰብ ነው " ብለዋል።

#ShegerFM
#HoPR
 
@tikvahethiopia
Forwarded from Đáŵĩť
Mehari Redai 2.pdf
55.1 MB
yihew ye dr. mehari leteyekachu
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 17/2016 ዓ/ም አንዲት መና ከበደ የተባለች የ26 ዓመት ወጣት ሴትን በመኪና ስርቆት ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ፥ ግለሰቧ ጥዋት 12:30 ገደማ ' ቤተል ቢጫ ፎቅ ' አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-B32912 አ.አ የሆነች ተሽከርካሪን የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ሞተር ሳያጠፋ አቁሞት ጃኬት ለመደረብ በገባበት ይዛ መሰወሯንና ከግማሽ ቀን ፍለጋ በኋላ ሰሚት አካባቢ መያዟን አስረድቷል።

ፖሊስ ግለሰቧንም ከነተሽከርካሪው ፎቶ በማንሳት አሰራጭቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ግለሰቧን እናውቃታለን ያሉ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ፤ መኪናውን መውሰድ አለመውሰዷን በግልጽ ባያሰፍሩም የሃብታም ልጅ እንደሆነች ፣ ስህተት እንደተፈጠረና ከወንጀሉ ነጻ ተብላ ወደ ቤት መግባቷን ጽፈዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ በተሽከርካሪ ስርቆት የተጠረጠረችው ግለሰብ መና ከበደ ክስ እንደተመሰረተባት አሳውቋል።

በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት መቅረቧንም አመልክቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ግለሰቧ ተሽከርካሪውን በመስረቋ ፓሊስ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን አስረድቷል።

" በአንዳንድ  ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ' ግለሰቧ ተለቃለች ' እና ' ወንጀሉን ሳታውቅ ነው የፈፀመችው ' የሚሉ መረጃዎች እየተሰራጩ  ይገኛል " ያለው ፖሊስ የግል ተበዳይ መኪናቸው መሰረቁን ለፖሊስ እንዳመለከቱ ግለሰቧም ተሽከርካሪውን ለረጅም ሰዓት ይዛ መሰወሯ  ታሳቢ በማድረግና ድርጊቷም በማስረጃ በመረጋገጡ ዓቃቤ ህግ በተሽከርካሪ ስርቆት ክስ መመስረቱን አሳውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አቶ ተክሌ በዛብህ የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባን አስመልክቶ ለኢቲቪ 57 የሰጡት ማብራሪይ
#አለሕግ #Alehig #Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
መደብ -የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ረዳት ዳኛ
ደመወዝ _10000+5500+1500
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please follow our Tiktok👇👇👇
https://vm.tiktok.com/ZMrk1ERat/
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM