አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.87K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
=========== የዉል ህግ ======
============== የዉል ምንነት
==
ዉል ማለት አንድ ሰዉ፣ተፈጥሮአዊ ሆነ በህግ ሰዉነት የተሰጠዉ፣ አንድን ተግባር ለመፈጸም ወይም ከመፈጸም ለመቆጠብ የሚገባዉን ግዴታ የሚያስርበት የስምምነት አይነት ነዉ፡፡ ይህ ዉል እቃዎችን ለመግዛት፣ ለመሸጥ ወይም አገልግሎት ለመስጠት፣ መብት ለመስጠት ወይም መብት ለማስቀረት፣ ስጦታ ለመስጠት፣ የስራ ቅጥር ለመፈጸም እንዲሁም የተለያዩ ተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ ተመስርቶ ሊፈጸም ይችላል፡፡
አንድ ዉል ምን አይነት ሁኔታዎችን ማሟላት አለበት?
የዉል ህግ የሚገዛዉ በሀገራችን የፍትሐብሔር ህግ ስር ነዉ፤ የተለያዩ ልዩ ሁኔታዎች እሚያስቀምጡ ህጎች ካሉ የእነሱ ተፈጻሚነት እንደተጠበቀ ሆኖ፡፡ ይህም የሆነዉ ከጠቅላላ ህግ ልዩ ህግ ቅድሚያ ስለሚሰጠዉ ነዉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የአገራችን ዉል ህግ በአራተኛዉ መጽሃፍ ስር ከአንቀጽ 1675 ጀምሮ ባለዉ ይገዛል፡፡ አንቀጽ 1675 ዉልን ሲተረጉም “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል የሚደረግ ስምምነት ነዉ፡” በማለት ያስቀምጠዋል፡፡ ከዚህ ትርጉም መረዳት እንደምንችለዉ ዉል አንዱ ንብረት መፍጠሪያ መንገድ ነዉ፡፡ ይህም መብት የሚፈጠረዉ ሁለት ወይም ከሁለት በላይ በሆኑ ሰዎች ሆኖ ግዴታዎች ላይ በመመርኮዝ ነዉ፡፡ ግዴታ ተቋቋመ ፣ተለወጠ ወይም ቀረ የሚባለዉ እነዚህ ሰዎች በሚገቡት ዉል ላይ በሚያስቀምጡት መዘርዝር ነዉ፡፡ በመሆኑም አንድ ዉል እነዚህን መብቶች መፍጠሩን በግልጽ ማሳየት አለበት፡፡
አንድ ዉልም ዉል ለመባል፡-
1. ዉሉ ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች የተፈጸመ መሆን አለበት፡፡
አንድ ሰዉ ችሎታ አለዉ የሚባለዉ በህጉ የተቀመጠዉን የእድሜ ገደብ ሲሞላ ወይም ምንም አይነት የአእምሮ እክል ከሌለበት፣ ወይም በህግ የተከለከለ ካልሆነ ነዉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎችም ተሟልተዉ ቢሆን ዉሉን የሚገባዉ ሰዉ ሙሉ ፈቃዱን የሰጠ መሆን አለበት፡፡ ማንም ሰዉ ቢሆን በማስፈራራት፣ በመደለል፣ በማታለል ሆነ በማስገደድ የዉል ግዴታ ዉስጥ ማስገባት አይቻልም፡፡
2. በዉሉ ላይ እንዲፈጸም የተቀመጠዉ ጉዳይ በአግባቡ ትርጉም የተሰጠዉ ወይም እርግጠኝነት ያለዉ፣ ሊፈጸም የሚቻልና ህጋዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ አለም ዉጪ የሆነ ወይም ለመፈጸም በማንኛዉም መልኩ ቢሆን አዳጋች የሆነ እንዲሁም ህገ-ወጥ ተግባር ለመፈጸም ዉል መግባት አይቻልም፡፡
3. በህጉ በአንድ በተለየ ፎርም እንዲፈጸም የተቀመጠ ዉል ከሆነና ይህንም ፎርም ያልተከተለ ከሆነ የሚጸና ዉል አይሆንም፡፡ ህጎች ብዙ ግዜ አንድን ዉል በጽሁፍ መሆን አለበት ካሉ በኋላ መልሰዉ የተለየ ሁኔታ የሚያስቀምጡበት ሁኔታ አለ፡፡ ለምሳሌ አንድ ዉል በጽሁፍ የሰፈረ መሆን አለበት ካለ በኋላ መልሶ ደግሞ ዉሉ መፈጸሙን በምስክር ማስረዳት ይቻላል ሲል ሊያስቀምጥ ይችላል፡፡ ይህም ሆኖ ግን ህጉ የተለየ ፎርም አስቀምጦ ከሆነ በዛዉ መልኩ መፈጸሙ ወደፊት ሊነሱ የሚችሉ ክርክሮች ሊያስቀርና የህግም ድጋፍ  ያገኛል።
ውብአለም መስፍን
የቦሌ/ክ/ከ/የህ/ስ/ም/መ ዳይሬክቶሬት ዐ/ህግ

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አለ_ህግ🔵Ale_Hig:
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
👍12🥰1
Addis Ababa City Administration Residence ID Proclamation.pdf
941.9 KB
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 145/2015
=====+++++++
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአስፈጻሚ አካላትን ለማቋቋም በወጣዉ አዋጅ ቁጥር 74/2014 ዓ.ም አንቀጽ 55 እና አንቀጽ 15 (2) (ሠ) ላይ በተጠቀሰዉ መሠረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አለ_ህግ🔵Ale_Hig:
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
👍122
የነጋዴ ግዴታዎች ምንድን ናቸው?
          ================
አዲስ አበባ 21/01/2015ዓ.ም (ንቀትሚ)

1. የንግድ ዕቃዎቹንና የአገልግሎቶቹን ታክስ፣ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና ሌሎች ሕጋዊና ክፍያዎችን ያካተተ የዋጋ ዝርዝር በንግድ ቤቱ በግልፅ በሚታይ ቦታ የማመልከት ወይም በንግድ ዕቃዎቹ ላይ መለጠፍ (አንቀፅ 15)፤

2. በሚሸጣቸው የንግድ ዕቃዎች ላይ መግለጫ የመለጠፍ ወይም በተለየ ወረቀት ላይ ጽፎ ለሸማቹ መስጠት (አንቀፅ 16)፤

3. መግለጫው የዕቃውን ስም፣ የተሠራበትን ሀገር፣ ክብደቱን፣ ብዛቱን፣ ጥራቱን፣ ይዘቱን፣ አጠቃቀሙን፣ የአገልግሎት ማብቂያ ጊዜ …ወዘተ ያካትታል፤ (አንቀፅ 16/2 ሀ-ኀ)

ለነጋዴ የተከለከሉ ድርጊቶች (አንቀጽ 22)
1. የንግድ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ስላላቸው ጥራት ወይም መጠን ወይም ብዛት ወይም ተቀባይነት ወይም ምንጭ ወይም ባህርይ ወይም ውሁድ ወይም ጥቅም የተሳሳተ መረጃ መስጠት(22/1)፤
2. የንግድ ዕቃዎች ስለአዲስነታቸው ወይም ስለሞዴላቸው ወይም አገልግሎታቸው የቀነሰ ወይም የተለወጡ ወይም እንደገና የተሠሩ ወይም በአምራቹ እንዲሰበሰቡ የተባሉ ወይም ያገለገሉ ስለመሆናቸው በትክክል አለመግለጽ(22/2)፤
3. የሌላውን ነጋዴ የንግድ ዕቃዎች በአሳሳች ሁኔታ መግለፅ(22/3)፤
4. የንግድ ዕቃዎችና አገልግሎቶችን በማስታወቂያ እንደተነገረላቸው አለመሸጥ ወይም ማስታወቂያው የመጠን ውሱንነት መኖሩን ካልገለፀ በስተቀር ሸማቾች በሚፈልጉት መጠን ልክ አለመሸጥ (22/4)፤
5. ስለዋጋ ቅናሽ ሀሰተኛ ወይም አሳሳች መረጃ ማስተላለፍ(22/5)
6. የሸማቹን መብት የሚጠብቅ ባልሆነ ምክንያት የንግድ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን አልሸጥም ማለት(22/12)፤
7. የንግድ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን በንግድ መደብሩ ውስጥ ከተለጠፈው ዋጋ አስበልጦ መሸጥ(22/14)፤
8. ከሽያጭ ጋር በተያያዘ የተገባ የዋስትና ግዴታን አለመወጣት(22/7)፤
9. የንግድ ዕቃ የሚያስፈልገው ጥገና ወይም የሚተኩ ክፍሎች      እንደማያስፈልጉት አድርጎ ማቅረብ(22/8)
10. የንግድ ዕቃዎች የተሠሩበትን ሀገር አሳስቶ መግለጽ(22/15)፤
11. በሸማቾች መካከል ተገቢ ያልሆነ አድልዎ መፈጸም(22/16)፤
12. ማንኛውንም አገልግሎት የመስጠት ሥራን በንግድ ሥራው ከሚታወቀው ደረጃ በታች ወይም ባልተሟላ ሁኔታ መስጠት922/9)፤
13. በግብይት ወቅት ማንኛውንም የማጭበርበር ወይም የማደናገር ተግባር መፈፀም(22/11)፤
14. ደረጃ የሚያስፈልጋቸውን የንግድ ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች ያለደረጃ ማህተም ለሽያጭ ማቅረብ (22/13)፤
15. አንድን የንግድ ዕቃ ወይም አገልግሎት ለመሸጥ ሸማቹ ያልፈለገውን ሌላ የንግድ ዕቃ አብሮ እንዲገዛ ማስገደድ(22/17)፤
16. ሕገ ወጥ በሆነ ማንኛውም የመለኪያ መሣሪያ መጠቀም(22/18)፤
17. ለሰው ጤናና ደህንነት አደገኛ የሆነ፣ ምንጩ ያልታወቀ፣ የጥራት ደረጃው የወረደ፣ ወይም የተመረዘ፣ አገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈ ወይም ከባዕድ ነገሮች ጋር የተደባለቁ የንግድ ዕቃዎችን ለሽያጭ ማቅረብ ወይም መሸጥ(22/10)፤
18. አንድ ሸማች አንድን የንግድ ዕቃ ወይም አገልግሎት በመግዛቱ ወይም የገንዘብ መዋጮ በማድረጉ እና በሸማቹ አሻሻጭነት ከእሱ ቀጥሎ ሌሎች ሸማቾች የንግድ ዕቃውን ወይም አገልግሎቱን የሚገዙ ወይም የገንዘብ መዋጮ የሚያደርጉ ከሆነ ወይም በሽያጭ ስልቱ ውስጥ የሚገቡ ከሆነ በሸማቾቹ ቁጥር ልክ ተጨማሪ የገንዘብ ወይም የዓይነት ጥቅም እንደሚያገኝ የሚገልጽ ፒራሚዳዊ የሽያጭ ስልት ተግባራዊ ማድረግ(22/6)፤
• ከላይ ከተጠቀሱት መብቶች ውስጥ ያልተከበረ ካለ ግብይቱን በፈጸሙበት አካባቢ ለመገኝ ንግድ ቢሮ ወይም ለፖሊስ በማቅረብ በሕግ ምላሽ እንዲሰጥዎ ያድርጉ፡፡
• በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ በተፈጸመ ግብይት በሸማቹ ላይ ለደረሰ ጉዳት የካሳ ትያቄ በፍትህ ሚኒስቴር የንግድ ውድድና የሸማቾች ጥበቃ ዳኝነት ችሎት ማቅረብ ይቻላል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን:-
Email: fdremotri@gmail.com
fdremotri@motri.gov.et
FB: Ethiopian ministry of trade and regional itegration
👍4👏1
ለጥብቅና ፍቃድ
ፈተና የሚሰጥበት ቀን መቀየሩን ለማሳወቅ የቀረበ ማስታወቂያ

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጥብቅና ፍቃድ ለማግኘት ይቻል ዘንድ ፈተናው መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ በማስታወቂያ መነገሩ ይታወቃል፡፡

ነገር ግን መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ.ም የኢሬቻ በአል የሚከበርበት ቀን በመሆኑና ለፈተናው አሰጣጥ አመቺነት ሲባል ፈተናው የሚሰጥበት ቀን ወደ ጥቅምት 03 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲቀየር ተወስኗል፡፡

በዚህም መሰረት ተፈታኞች ይህንን አውቃችሁ እንድትዘጋጁ እያሳሰብን ፈተናው የሚሰጥበትን ቦታና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን በቀጣይ የምናሳውቃችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የኢፌዲሪ ፍትህ ሚኒስቴር
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አለ_ህግ🔵Ale_Hig:
https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ
#Share #ሼር
#አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
#አለ_ህግ 
2👍1