አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በወንጀል ስነስርአት ይግባኝ የማይባልባቸው ጉዳዮችን ዘርዝር
የቀዳሚ ምርመራ ክስ ግለጹ
በአጭር ሥነ-ሥርዓት እና በተፋጠነ ሥነ-ሥርአት የሚቀርቡ ጉዳዮችን ዘርዝር
የውል መሰረዝ እና መፍረስ አንድነት እና ልዩነት?
ይቅርታ እና ምህረት ልዩነቱ ምንድነው?
Proclmation1072.2018 (1).pdf
809.1 KB
የኤሌትሮኒክ ፊርማ ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ቁጥር 1072/2010
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 358 እና 418 ተፈፃሚ የሚሆኑበት አግባብ ከሰበር ውሳኔዎች ጋር በማገናዘብ
================
የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት ቅጽ 8 በመ/ቁ. 32143 እና ቅጽ 7 በመ/ቁ. 25031 በሰጠው ውሳኔ የሁለቱንም ልዪነት ማብራሪያ በመስጠት ትርጉም ሰጥቷል። ለክርክሩ ምክንያት በሆነው ንብረት ላይ ፍርድ አርፎበታል ከተባለ ይሄው ፍርድ ሊሰረዝልኝ ይገባል የሚለው ወገን አቤቱታ ማቅረብ ያለበት በፍ/ብ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 358 መሠረት እንጂ ፍ/ብ/ሥ/ሥ/ቁ በ418 መሠረት ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱ የሥነ ሥርዓት ድንጋጌዎች የተለያየ ዓላማና ውጤት ያላቸው ስለሆነ ነው፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ. 418 መሠረት አቤቱታ አቅራቢ በዋናው ፍርድ ላይ ምንም ዓይነት ክርክር የሌለውና አፈጻጸም እንዲቀጥል ትዕዛዝ በተሰጠበት ንብረት ላይ መብት አለኝ የሚል ወገን መሆን አለበት፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ.358 መሠረት መብቱ የተነካው ወገን ፍርዱን ለሰጠው ፍ/ቤት መቃወሚያ ማቅረብ ይችሏል፡፡

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 358 መሠረት አቤቱታ /መቃወሚያ/ የሚቀርበው ቀደም ሲል የተሰጠን ውሣኔ ለመቃወም ነው፡፡ መቃወሚያውን ማቅረብ የሚችሉትም ቀደም ሲል በተደረገው ክርክር ተካፋይ ያልነበሩት ወገኖች ናቸው፡፡ ቀደም ሲል በተደረገው የአፈፃፀም ክርክር ተካፋይ የነበረ እና የተወሰነበት ሰው በዚህ ሥነሥርዓት ክርክር ማንሳት የሚችልበት የህግ አግባብ የለም፡፡ ውሳኔ ከተወሰነ በኋላ ተቃዋሚ ሆኖ የሚቀርብበት አግባብ የለም፡፡ ከዚህም በሌላ መንገድ በአፈፃፀም በተያዘ ወይም በተከበረ ንብረት ላይ መብት አለን ባዮች አቤቱታ ማቅረብ የሚችሉት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 418 መሠረት ሆኖ ማቅረብ ያለባቸውም ሣይዘገዩ እንደሆነ በዚሁ ቁ. 418/1/ ተመልክቶአል፡፡ አቤቱታው በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ. 418 መሠረት ዘግይቶ የክርክሩን ውጤት በመጠበቅ ሳይሆን መቅረብ የሚገበውም ንብረቱ መከበሩን እንዳወቀ ነው።
Via Tsegaye Demeke _Lawyer
#ሼር @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የቤተሰብ ሕግ ሐተታ ዘምክንያት.pdf
840.6 KB
የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ማብራሪያ
የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ሕግ.pdf
552.9 KB
የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ሕግ፡- ለዳኞችና ዓቃብያነ ሕግ ሥልጠና የተዘጋጀ
የፍትሐብሔር_ጉዳዮችን_የሚመለከቱ_ፎርሞች.pdf
4.6 MB
የፍትሐብሔር ጉዳዮችን የሚመለከቱ የክስ፣ የመልስ፣ የይግባኝ፣ የአፈጻጸም፣ የሰበር፣ የውሳኔ እና የትዕዛዝ ፎርሞች፡፡