አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ቼክ ተከፋይ (payee) የሆነ ሰው ቼኩን ያገኘበትን ውል የማስረዳት ሆነ በውሉ መሰረት ክፍያ እንዳልተፈጸመለት የማስረዳት ግዴታ የለበትም።
ይልቁንስ ለቼኩ መውጣት ምክንያት ነው የሚለዉን የግል ግንኙነትን በመከላከያነት በማንሳት ክፍያ ለመክፈል እንደማይገደድ የሚከራከር የቼኩ አውጪ (drawer) በቼኩ ክፍያ የማይፈጽምበት ህጋዊ ምክንያት ስለመኖሩ በቀዳሚነት የማስረዳት ሸክም (ግዴታ) አለበት።
ከዚህ አኳያ ፍርድ ቤት በቀዳሚነት መመርመር የሚገባዉ ጉዳይ የቼኩ አውጪ ለቼኩ መውጣት ምክንያት ነዉ ያለውንና ክፍያ የማይፈጸምበት ምክንያት መኖር አለመኖሩን እና በተገቢው ማስረጃ ማስረዳት መቻል አለመቻሉን መለየት ነዉ።
#habeshaadvocatesllp
የኢትዮጵያ ሕጎችና የሰበር ውሳኔዎች ዳታቤዝ ተሻሽሏል!

ሕጎችን እና የሰበር ውሳኔዎችን በፒዲኤፍ” በቀላሉ ማግኘት የሚያስችለዎትን ዳታቤዝ አሻሽለው አቀርበውልናል።

We are thrilled to announce the release of the beta version of our new Legal search engine! This powerful tool is designed specifically for legal professionals and researchers, providing fast and accurate results for all of your legal queries. With our comprehensive database and intuitive search interface, you'll be able to find the information you need quickly and easily.

Try it out today and let us know what you think!

https://pocketlaw.abyssinialaw.com
*ለሁሉም ጊዜ አለው።
ጊዜውን ዋጁ‼️
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
የድል ቀን እንጂ የነፃነት ቀን አናከብርም !!!
We don't Celebrate Indipendence day
We do celebrate Victory day !!!

ክብር ለአባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው እናት ኢትዮጵያን ላቆዮልን !!!

እንኳን ለ 127ኛው አድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ::
#Adwa Victory #African Victory
ቅጽ 25 መዝገብ ቁጥር 188881
******
ከሳሽ የከተማ ባዶ ቦታ መሸጡን አምኖ ውሉ እንዲፈርስ ሲጠይቅ ተከሳሽ ደግሞ ውሉ ከአስር ቆርቆሮ ቤትጋ የተደረገ ነው ውሉ ይናገራል በሚል ተከራክሯል።

በግራ ቀኙ መሀከል የተደረገው ውል በውል አዋዋይ ፊት ያልተደረገ ስለሆነ ሽያጩ ከ10 ቆርቆሮ ቤትጋር ስመደረጉ ውሉ ቢያሳይም ባዶ ቦታ ላይ የተደረገ ውል ነው፣ የት ቦታ ያለ ቤት ነው.....የሚል አከራካሪ ነገር ካለ ውሉ ታምኗል ሊባል የማይችል መሆኑን እና ለቤት መስሪያ የሚሆን ቦታ ላይ ከሆነ ውሉ የተደረገው በከሳሽ ምርጫ አፍርሶ መውሰድ ወይም የመስሪያ ዋጋውን(book value) መጠየቅ ይችላል።
የሰበር መዝገብ ቁጥር 207446 ቅጽ 25
ስለ ማስመሰል ውል ስለ አጭበርባሪነት ውል (የፍ/ህ/ቁ1988-2000) ተይዞ የህግ ትርጉም የተሰጠበት።

አንድ ሰው ለምሳሌ ከውል ውጭ በሆነ ክስ የሚወሰንበትን በመፍራት፣ የእቁብ እዳ ይኖርበት እና ላለመክፈል ወይም በሌላ ክስ ባለእዳ ንብረቱን ለማሸሽ የሚጠቀምባቸው መንገዶች
ፍርድ ቤት ላይ ባለእዳው ለከሰሰው ሰው አዎ ቤቱን ሸጫለው ብሎ ያምን እና ቤቱ ለከሳሽ ይወሰናል።

ወይም ውል አዋዋይ ፊት ቀርበው ውል ይፈጽማሉ፣

ባል እና ሚስት ሆነው በስምምነት ይፋቱ እና ንብረቱን እዳ ለሌበት ወገን የግል እዲሆን ተስማምተናል ይላሉ፣

የተወሰነውን እና ዋናውን የቤት ክፍል ልጁን አምጥቶ ተፈቅዶልኝ በግል ገንዘቤ ነው የሰራሁት እንዲል ያደርጋል።

ብቻ አይቱ ብዙ የሆነ ባለእዳ ገንዘቡን ላለመክፈል መንገድ ይጠቀማል።

እንዲህ ያለውን ተግባር እንዴት መመራት እንዳለበት የሚያመላክት የሰበር ውሳኔ ነው በንባብ እና በስራ ቢዳብር።
ስለ ታክስ ተመላሽ አፈጻጸም

የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመላሽ ስለሚደረግበት ሁኔታ ለመወሰን በወጣ መመሪያ ቁጥር 148/2011 መሰረት፡-

1. ማንኛውም ታክስ ከፋይ የንግድ ፈቃድ ከተሰረዘ በኋላ በሚያከናውነው ግዥ ላይ ለከፈለው ተጨማሪ እሴት ታክስ የተመላሽ ጥያቄ ማቅረብ አይችልም፤
2. ለህንጻ ግንባታ በሚውል ግብዓት ላይ የተከፈለ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመላሽ የሚደረገው የህንጻው ግንባታ ተጠናቆ ገቢ ማመንጨት በተጀመረበት የመጀመሪያው የሂሳብ ጊዜ ከሰበሰበው ታክስ ላይ እንዲቀናነስ ከተደረገ በኋላ ቀሪ ሂሳብ ካለ ታክስ ከፋዩ ገቢ ማመንጨት ከጀመረበት ወር ቀጥሎ ባለው ወር ውስጥ ይሆናል፤
3. በተራ ቁጥር ሁለት የተገለጸው ቢኖርም ለህንጻው ግንባታ በዋለ ግብዓት ላይ የተከፈለ ተጨማሪ እሴት ታክስ ግንባታው ተጠናቆ ታክስ የሚከፈልበት ገቢ ማመንጨት ከመጀመሩ በፊት በተደረጉ ሌሎች ታክስ የሚከፈልባቸው ግብይቶች ላይ ከተሰበሰበ ታክስ ጋር ሊቀናነስ አይችልም፤
4. ማንኛውም የተመዘገበ ታክስ ከፋይ በግብዓት ላይ የከፈለው ታክስ የካፒታሉ አካል ሆኖ ከተመዘገበ እና የእርጅና ቅናሽ ወጪ እንዲታሰብለት ከተደረገ ታክሱ ተመላሽ አይደረግም፤
5. የልዩ መብት ተጠቃሚ የታክስ ተመላሽ ጥያቄ በሚያቀርቡበት ጊዜ የልዩ መብት ተጠቃሚው የፊርማ ናሙና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተረጋግጦ ለታክስ ባለስልጣኑ መላክ አለበት፡፡
6. ባለ ልዩ መብቶች ለገዙት ዕቃ ወይም አገልግሎት ክፍያ የፈጸሙት ከNT ወይም ከNR የኮምፒውተር አካውንት ላይ ከሆነ ታክሱ ተመላሽ የሚደረገው ገንዘቡ ወጪ በተደረገበት አካውንት መልሶ በማስገባት ነው፡፡
7. ማንኛውም ባለ ልዩ መብት በዕቃ ወይም በአገልግሎት ግዥ ላይ የከፈለው ታክስ ተመላሽ የሚደረገው የተመላሽ ጥያቄውን ባቀረበ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ሲሆን በማንኛውም ሁኔታ ለግብይቱ ክፍያ ከተፈጸመ ከአንድ አመት በኋላ የሚቀርብ የታክስ ተመላሽ ጥያቄ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
የወጭና_ኪሳራ_አስተዳደር_በኢትዮጵያ_የፍትሐብሄር_ስነስርዓት_ህግ_.pdf
393.2 KB
“የወጭና ኪሳራ አስተዳደር በኢትዮጵያ የፍትሐብሄር ስነ-ስርዓት ህግ”

ጸሐፊ፡- አያሌው አባተ (ዶ/ር)
ጋብቻ እና ፍቺ ባለፉት 6 ወራት በአዲስ አበባ
 
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት 1ሺህ342 ፍቺዎች እና 14ሺህ 136 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታውቋል።

አል ዐይን
ገና ዛሬ አይደል እንዴ አውራሪስ ምን እንደሚመስል ያየሁት!🙈
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties
ፎቶ መላክ የሚጠበቅባቸው update.pdf
1.6 MB
ፎቶ ግራፍ መረጃ ላላሟላችሁ ጠበቆች
**
የኢ
.ፌ.ጠ.ማ  የአባልነት ማረጋገጫ  ደረጃውን የጠበቀ መታወቂያ  ለማሰራት  በዝግጅት  ላይ መሆኑን እና በምዝገባ ወቅት መረጃ  ያላሟላችሁ  እንድታሟሉ  ከአሁን በፊት አሳውቀናል።

በመሆኑም  እስካሁን ድረስ ፎቶ ግራፍ  ያልሰጣችሁ  ጠበቆች ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረ ስለሆነ ለመጨረሻ ጊዜ  እስከ ሐሙስ መጋቢት 08 ቀን 2015  ዓ.ም ድረስ  ከማህበሩ መ/ቤት  አራዳ ምድብ የፌዴራል ፍርድ ቤት በሚገኘው የፍትህ አካለት ህንፃ 9ኛ ፎቅ  በአካል በመምጣት እና በስልክ ቁጥር 0913- 661578/ 0912432335  በመጠቀም በቴሌግራም የተሟላ መረጃ (ፎቶ፣ መሉ ስም በአማረኛና እንግሊዘኛ፣ ጥብቅና ቁጥር፣ TIN No)  እንድትልኩ እናሳውቃለን ለመጨረሻ ጊዜ።

ሁሉም የማህበሩ አባል  መረጃውን የሰማ፤ ላልሰማ በማጋራት  ኃላፊነታችሁን እንድትወጡና ትብብር እንድታደርጉ አደራ ማለት እንወዳለን።
መጋቢት 06 ቀን 2015  ዓ.ም
#አለ_ህግ #Ale_Hig #ህግ #Lawsocieties #አለ_ህግ #Ale_Hig
https://t.me/lawsocieties