አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በዋና ጥያቄ ላይ ያልተነሳ
ምስክር መስቀለኛ ጥያቄ በሚጠየቅበት ወቅት በጣም የተለመደው መቃወሚያ በዋና ጥያቄ አልተነሳም የሚል ሲሆን ፍርድ ቤቶች በደፈናው ይቀበሉታል፡፡ ይሁን እንጂ ሁለቱም የስነ ስርዓት ህጎች ለጥያቄ መለኪያ የሚያስቀምጡት አግባብነት /relevance/ እንጂ ጥያቄው በዋና ጥያቄ መነሳት አለመነሳቱ አይደለም፡፡

#ምሳሌ
ምስክሩ በዋና ጥያቄ ወቅት "መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ጠዋት 3 ሰዓት አካባቢ መኖሪያ ቤቴ አካባቢ ተከሳሽ ተበዳዩን ሲመታው አይቻለው" በማለት ምስክርነት ሰጠ። በቀጣይ የቀረበለት መስቀለኛ ጥያቄ እና የሰጠው መልስ ይህንን ይመስላል።

ጥ---ልጅ አለህ?
መ--አዎ
ጥ--ስንት ልጅ?
መ--አንድ
ጥ--ወንድ ወይስ ሴት?
መ--ሴት
ጥ--መቼ ነው የተወለደችው?
መ--መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም.
ጥ--ጥሩ፤ መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ብለሀል። ጠዋት ነው ወይስ ሌሊት?
መ--ጠዋት። 1 ሰዓት አካባቢ ወደ ሆስፒታል ወስድኳት። 5 ሰዓት አካባቢ ተገላገለች።
ጥ--ባለቤትህን ሆስፒታል ከወስድክበት ጊዜ ጀምሮ እስክትወልድ ድረስ አብረሃት ነበርክ?
መ--አዎ። ከዛ በኋላም እስከ 7 ሰዓት ድረስ አብሬያት ነበርኩኝ።

ቀጣዩ ጥያቄ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አይከብድም። ተከሳሽ ተበዳይን ሲመታው አየሁኝ ያለበት ቀንና ሰዓት ሆስፒታል ነበርኩኝ ካለበት ቀንና ሰዓት ጋር ተመሳሳይ ነው። ሆኖም እዚህ ላይ ለመድረስ እስካሁን የተጠየቁት ጥያቄዎች በዋና ጥያቄ ያልተነሱ ናቸው።
ስለሆነም በመስቀለኛ ጥያቄ ወቅት የጠያቂው ግዴታ የጥያቄውን አግባብነት ማስረዳት ብቻ ነው። ይህንን ሲያደርግ ከተቃራኒው ተከራካሪ ጋር ወደ ዳኛው ተጠግቶ አግባብነቱን ማስመዝገብ አለበት።
ምስክሩ እየሰማ የሚናገር ከሆነ ግን ምስክሩ እንዲነቃና ቀድሞ ለመልሱ እንዲዘጋጅበት /ምናልባትም ሐሰተኛ ምስክርነት እንዲሰጥ/ ያደርገዋል።
በአብርሐም ዩሐንስ
ኢትዮ-ሕግ🇪🇹👇
#ethiolawtips
#አለ_ህግ #ale_hig #lawsocieties #ህግ
https://t.me/lawsocieties