የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር የስራ አመራር ኅዳር 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የማህበሩ ፕሬዝደንት ያቀረቡት የሥራ መልቀቂያ ላይ ከመከረ በኋላ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል።
በጥብቅና ፍቃድ አሰጣጥና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 66 ንዑስ አንቀጽ 3 የማኅበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሬዝዳንቱ በማይኖሩበት ጊዜ ወይም ሥራቸውን ሊሠሩ በማይችሉበት ጊዜ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ፕሬዝዳንቱን ተክቶ ሥራውን ማከናወን እንዳለበት ይደነግጋል።
በዚሁ መሠረት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት የነበሩት ኃላፊነታቸውን በራሳቸው ፈቃድ የተዉ መሆኑን በጽሑፍ ስላሳወቁ የማህበሩ ም/ፕሬዝደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ፕሬዝደንቷን ተክተው እንዲሰሠሩ የሥራ አስፈጻሚው በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የማህበሩ ም/ፕሬዝደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ከዛሬ ጀምሮ ለሚሰጡት አመራርና ለሚያከናውኗቸው ተግባራት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሙሉ ድጋፉን የሚሰጥ ሲሆን አቶ ቴዎድሮስ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ከፍ ባለ ትጋት እና ውጤታማ አመራር በመስጠት እንደሚወጡት በመተማመን መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ሥራ አስፈጻሚው ይመኛል!
ማህበሩ በቀጣይ እንቅስቃሴዎቹን በተመለከተ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም ለመላው አባላቱ እና ወደ ሦስተኛ አካላት የሚደርስ መሆኑን ያሳውቃል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ህዳር 14 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በጥብቅና ፍቃድ አሰጣጥና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2013 አንቀጽ 66 ንዑስ አንቀጽ 3 የማኅበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሬዝዳንቱ በማይኖሩበት ጊዜ ወይም ሥራቸውን ሊሠሩ በማይችሉበት ጊዜ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ፕሬዝዳንቱን ተክቶ ሥራውን ማከናወን እንዳለበት ይደነግጋል።
በዚሁ መሠረት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት የነበሩት ኃላፊነታቸውን በራሳቸው ፈቃድ የተዉ መሆኑን በጽሑፍ ስላሳወቁ የማህበሩ ም/ፕሬዝደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ፕሬዝደንቷን ተክተው እንዲሰሠሩ የሥራ አስፈጻሚው በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
የማህበሩ ም/ፕሬዝደንት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ከዛሬ ጀምሮ ለሚሰጡት አመራርና ለሚያከናውኗቸው ተግባራት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሙሉ ድጋፉን የሚሰጥ ሲሆን አቶ ቴዎድሮስ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ከፍ ባለ ትጋት እና ውጤታማ አመራር በመስጠት እንደሚወጡት በመተማመን መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ሥራ አስፈጻሚው ይመኛል!
ማህበሩ በቀጣይ እንቅስቃሴዎቹን በተመለከተ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም ለመላው አባላቱ እና ወደ ሦስተኛ አካላት የሚደርስ መሆኑን ያሳውቃል::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ህዳር 14 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
👍15❤1
መርህ እና የህግ የበላይነት
አንድ ጊዜ ልምምድ ለማድረግ ዘግይቼ ደርሸ ነበር እናም አሰልጣኙ ዙር እንድሮጥ አድርጎኛል። ወደ ስልጠናው የወሰደኝ አባቴ ነበር። አሰልጣኙም አባቴ ነበር።
One time was late to practice and coach made me run laps. My dad was the coach. And he drove me to practice.
https://t.me/lawsocieties
አንድ ጊዜ ልምምድ ለማድረግ ዘግይቼ ደርሸ ነበር እናም አሰልጣኙ ዙር እንድሮጥ አድርጎኛል። ወደ ስልጠናው የወሰደኝ አባቴ ነበር። አሰልጣኙም አባቴ ነበር።
One time was late to practice and coach made me run laps. My dad was the coach. And he drove me to practice.
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
👍3👏3😁2🤔1
Audio
👍3
#Ethiopia Road Authority(ERA)#🚩For Fresh & Exp
▪️25 Open Positions
▪️Qualification: Automotive Technology, Electro Mechanical Engineering, LLB law, Construction Law, Machine Operator, 8th, 10th, 12th & relateds.
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3OG5huH
▪️Deadline: December 09/2022
▪️25 Open Positions
▪️Qualification: Automotive Technology, Electro Mechanical Engineering, LLB law, Construction Law, Machine Operator, 8th, 10th, 12th & relateds.
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3OG5huH
▪️Deadline: December 09/2022
👍4👎2
ሀ.👉የራስ ታክስ ስሌት የማሻሻያ ጥያቄ አቀራረብና አፈጻጸም መመሪያ ረቂቅ
ለ.👉የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ መመሪያ ረቂቅ
ሐ.👉የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት አሰጣጥ መመሪያ ረቂቅ
ረቂቁ የቀደሙትን መመሪያዎች ( መመሪያ 144/2011,142/2011 እና 139/2010 ( መመሪያ 128/2009 እና 55/2003 ጨምሮ ) እንደሚተኩ የሚጠበቅ ሲሆን, በገቢ ሚንስትር ከተፈረሙበት ጀምሮ ተፈፃሚ ናቸው::
_//_................
Hima _ Tax Solutions
Source: HIMA_Xpress_Tax
ለ.👉የታክስ ክፍያ ጊዜ ማራዘሚያ መመሪያ ረቂቅ
ሐ.👉የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት አሰጣጥ መመሪያ ረቂቅ
ረቂቁ የቀደሙትን መመሪያዎች ( መመሪያ 144/2011,142/2011 እና 139/2010 ( መመሪያ 128/2009 እና 55/2003 ጨምሮ ) እንደሚተኩ የሚጠበቅ ሲሆን, በገቢ ሚንስትር ከተፈረሙበት ጀምሮ ተፈፃሚ ናቸው::
_//_................
Hima _ Tax Solutions
Source: HIMA_Xpress_Tax
👍3
ተገዶ_የመያዝ_Habeas_corpus_ስረ_ነገር_ስልጣን.pdf
320.7 KB
የሰበር መዝ/ቁ. 230167፣ 230168፣ 230169 /ያልታተሙ/
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 5(1)(ኘ) መሰረት ተገድዶ የመያዝን ህጋዊነት ለማረጋገጥ የሚቀርብን አቤቱታ / Habeas corpus/ ተቀብሎ የማየት የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣን ያለው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አይደለም ።
#Click Ethiopian Laws
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 5(1)(ኘ) መሰረት ተገድዶ የመያዝን ህጋዊነት ለማረጋገጥ የሚቀርብን አቤቱታ / Habeas corpus/ ተቀብሎ የማየት የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣን ያለው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አይደለም ።
#Click Ethiopian Laws
👍9
የማስረጃ ህግ ጽንሰ ሀሳቦች
= ማስረጃ ምንድነዉ ?
ማስረጃ በመመርመር ላይ ያለ ወይም አከራካሪ የሆነ ፍሬ ነገር ስለመኖር/ያለመኖሩ፣ እውነት /ሀሰት ስለመሆኑ ከሚረጋገጥባቸው ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ፍሬ ነገር ሲብራራ ደግሞ ሰዎች በስሜት ህዋሳቶቻቸው የሚረዱአቸው/የሚለዩአቸው ኩነቶች ወይም ክስተቶች ናቸው፡፡ በመሆኑም ማስረጃ ማለት ሰዎች በስሜት ህዋሳቶቻቸው የሚረዱአቸው/የሚለዩአቸው ኩነቶች ወይም ክስተቶች ስለመኖር/ያለመኖሩ፣ እውነት /ሀሰት ስለመሆኑ ከሚረጋገጥባቸው ነገሮች አንዱ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ፡፡ ሰዎችም ብዙ ግዜ ወደ ፍርድ ቤት የሚመጡት የዚህን ፍሬ ነገር መኖር አለመኖር ወይም እዉነት/ሀሰት መሆን እንዲረጋገጥላቸዉ ስለሚፈልጉ ነዉ፡፡ የዳኞችም ስራ ይህ ፍሬ ነገር በማስረጃ መረጋገጡን ማጣራት ነዉ፡፡
= የማስረጃ አይነቶች
1. የቃል ማስረጃ፡- በምስክር አንደበት የሚነገር ወይም የሚሰማ
2. የሰነድ ማስረጃ፡-ወረቀት ላይ ሰፍሮ የሚገኝና የሚነበብ ወይም ሀሳብ የያዘ ነገር
3. የቁሳዊ/ገላጭ ማስረጃ፡-መጠኑን ፣ዓይነቱን…ወዘተ የሚያሳይ ነዉ፡፡ዳኞች በራሳቸው የስሜት ህዋሳት ተረድተው ውሳኔ ላይ እንዲደርሱ የሚቀርብ ዳኞች በአካል የሚመለከቱትን፣ የሚሰሙትን…የሚያመለከት ነው፡፡
4. የሳይንሳዊ ማስረጃ፡-የህክምና ሳይንስን ጨምሮ በሌሎች ሳይንሳዊ ዘዴዎች የተሰበሰበን፣ የተገኘን፣ የታወቀን፣ የተረጋገጠን… ፍሬ ነገር የሚመለከት
5. የኤሌክትሮኒክስ ማስረጃ፡-በኮምፒውተር፣ በኢንተርኔት ወይም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ውስጥ የሚገኝ የማይጨበጥ/የማይዳሰስ መረጃ ናቸዉ።
= በማስረጃ የሚረጋገጥ እና የማይረጋገጥ ፍሬ ነገር ምን ማለት ነዉ?
የሚረጋገጡ ፍሬ ነገሮች
1. ከመሰረታዊ ህግ በመነጨ በጭብጥ የሚያዙ
2. ከማስረጃ ህግ በመነጨ በጭብጥ የሚያዙ ተቀጽላ ወይም ተጓዳኝ ፍሬ ነገሮች፤
3. በጭብጥ ለተያዙ ፍሬ ነገሮች አግባብነት ያላቸው ፍሬ ነገሮች ናቸዉ፡፡
እነዚህንም ፍሬ ነገሮች
በፍሬ ነገር ማረጋገጫ ዓይነቶች-
• በፍርድ ቤት ፊት የሚሰጥ የእምነት ቃል (Formal Admission)፣
• የዳኞች ግንዛቤ መዉሰድ/መያዝ (Judicial Notice)፣
• የህግ ግምት (Presumption)፣
• የመኃላ ቃል (Oath)፣
• ማስረጃ (Evidence) ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
= የማይረጋገጡ ፍሬ ነገሮች
- በፍ/ቤት ፊት በተከራካሪ ወገን የታመኑ (Formally Admitted Facts)
- በዳኞች ግንዛቤ የሚያዝባቸው (Facts which judges take Judicial Notice)
- በህግ ግምት የሚወሰድባቸው (Presumed Facts) ሆነው ከተገኙ ነው፡፡
ስለዚህ እነዚህን ፍሬ ነገሮች ተጨማሪ ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ በነዚህ በቀረቡት ሁኔታዎች ብቻ ማስረዳት ይቻላል፡፡
= አግባብነት ወይም አስፈላጊነት እና ተቀባይነት ያለዉ ማስረጃ ምንነት
አግባብነት፡- አግባብነት ሲባል አንድ ፍሬ ነገር ወይም ማስረጃ ከሌላ ፍሬ ነገር ወይም ማስረጃ ጋር ያለውን ተዛመዶ ወይም ትስስር የሚገልጽ ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት በተከራካሪ ወገን የሚቀርብ ማንኛዉም ማስረጃ ሳይሆን በግራቀኝ ለቀረበዉ ክርክር ተገቢነት ኖሮት ሊያስረዳ የሚችል ማለት ነዉ፡፡
ተቀባይነት፡- ሲባል አንድ ማስረጃ ለፍርድ ቤት ሲቀርብ ችሎቱ ይቀበለዋል ወይስ አይቀበለዉም የሚለዉን የሚያሳይ ነዉ፡፡ ችሎትም ማስረጃዉን ሊቀበለዉ ወይም ማስረጃዉን ሊተወዉ የሚችለዉ ደስ ስላለዉ ወይም ስላላለዉ ሳይሆን ማስረጃዉ በህጋዊ ሁኔታ መምጣት አለመምጣት ማጣራት እንዳለበት የሚያሳይ ሃሳብ ነዉ፡፡
= ማስረጃ ለማቅረብ ማን ይገደዳል ወይም የማን ሸክም ይሆናል?
ማስረጃ ለማቅረብ ማን ይገደዳል ሲባል መጀመሪያ ማስረጃ ማን ማቅረብ አለበት የሚለዉን ሃሳብ የሚያንጸባርቅ ነዉ፡፡ይህም ከሁለቱ ወገኖች አቤቱታ ይዘትና በህግ ተለይቶ ከተቀመጠው አንጻር ታይቶ የሚለይ ነው፡፡ በመሆኑም አንድ ነገር እንዳለ የሚከራከር ወገን ይህ ፍሬ ነገር ስለመኖሩ ቀድሞ የማስረዳት ወይም ማስረጃ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡ ፍሬነገሩም እንዳለ ተከራካሪዉ ካስረዳ ይህን ማስረጃ በማቅረብ መቀልበስ ወይም መቃወም ያለበት የሌላኛዉ ወገን ድርሻ ይሆናል ማለት ነዉ፡፡ይህም የማስረዳት ሸክም ዞረ ይባላል፡፡
= የማስረጃ አቀራረብ መንገዶች
በመሰረቱ ማስረጃ ለፍርድ ቤት መቅረብ ያለበት ከአቤቱታ ወይም ከመልስ ጋር ነዉ፡፡ ነገር ግን አንድ አንድ ማስረጃዎች በምንፈልገዉ ሰሀት እና በምንጠይቀዉ ሰአት ላናገኛቸዉ እንችላለን፡፡ እነዚህንም ማስረጃዎች በወንጀልም ይሁን በፍትሐብሔር ክርክሮች እንድናቀርብ የምንጠይቅባቸዉ አግባቦች አሉ፡፡ ይህም ሊሆን የሚችለዉ በማስረጃ ዝርዝራችን ላይ በፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲቀርቡ በመጠየቅ፣ክስ ከመሰማቱ በፊት በችሎት በማቅረብ፣ እንዲሁም ክርክሩ እየተካሄደ ባለበት ግዜ በበቂ ምክንያት ሳይቀርቡ የቀሩ ማስረጃዎች ለችሎቱ በማቅረብ ነዉ፡፡
ዉበአለም መስፍን የቦ/ክ/ከ/ፍ/ጽ/ቤት/የህ/ስ/ም/መ ዳይሬክቶሬት ዐ/ህግ
ምንጭ የቦሌ ክ/ከተማ የሕግ ስርፀትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት
= ማስረጃ ምንድነዉ ?
ማስረጃ በመመርመር ላይ ያለ ወይም አከራካሪ የሆነ ፍሬ ነገር ስለመኖር/ያለመኖሩ፣ እውነት /ሀሰት ስለመሆኑ ከሚረጋገጥባቸው ነገሮች አንዱ ነው፡፡ ፍሬ ነገር ሲብራራ ደግሞ ሰዎች በስሜት ህዋሳቶቻቸው የሚረዱአቸው/የሚለዩአቸው ኩነቶች ወይም ክስተቶች ናቸው፡፡ በመሆኑም ማስረጃ ማለት ሰዎች በስሜት ህዋሳቶቻቸው የሚረዱአቸው/የሚለዩአቸው ኩነቶች ወይም ክስተቶች ስለመኖር/ያለመኖሩ፣ እውነት /ሀሰት ስለመሆኑ ከሚረጋገጥባቸው ነገሮች አንዱ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ፡፡ ሰዎችም ብዙ ግዜ ወደ ፍርድ ቤት የሚመጡት የዚህን ፍሬ ነገር መኖር አለመኖር ወይም እዉነት/ሀሰት መሆን እንዲረጋገጥላቸዉ ስለሚፈልጉ ነዉ፡፡ የዳኞችም ስራ ይህ ፍሬ ነገር በማስረጃ መረጋገጡን ማጣራት ነዉ፡፡
= የማስረጃ አይነቶች
1. የቃል ማስረጃ፡- በምስክር አንደበት የሚነገር ወይም የሚሰማ
2. የሰነድ ማስረጃ፡-ወረቀት ላይ ሰፍሮ የሚገኝና የሚነበብ ወይም ሀሳብ የያዘ ነገር
3. የቁሳዊ/ገላጭ ማስረጃ፡-መጠኑን ፣ዓይነቱን…ወዘተ የሚያሳይ ነዉ፡፡ዳኞች በራሳቸው የስሜት ህዋሳት ተረድተው ውሳኔ ላይ እንዲደርሱ የሚቀርብ ዳኞች በአካል የሚመለከቱትን፣ የሚሰሙትን…የሚያመለከት ነው፡፡
4. የሳይንሳዊ ማስረጃ፡-የህክምና ሳይንስን ጨምሮ በሌሎች ሳይንሳዊ ዘዴዎች የተሰበሰበን፣ የተገኘን፣ የታወቀን፣ የተረጋገጠን… ፍሬ ነገር የሚመለከት
5. የኤሌክትሮኒክስ ማስረጃ፡-በኮምፒውተር፣ በኢንተርኔት ወይም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ውስጥ የሚገኝ የማይጨበጥ/የማይዳሰስ መረጃ ናቸዉ።
= በማስረጃ የሚረጋገጥ እና የማይረጋገጥ ፍሬ ነገር ምን ማለት ነዉ?
የሚረጋገጡ ፍሬ ነገሮች
1. ከመሰረታዊ ህግ በመነጨ በጭብጥ የሚያዙ
2. ከማስረጃ ህግ በመነጨ በጭብጥ የሚያዙ ተቀጽላ ወይም ተጓዳኝ ፍሬ ነገሮች፤
3. በጭብጥ ለተያዙ ፍሬ ነገሮች አግባብነት ያላቸው ፍሬ ነገሮች ናቸዉ፡፡
እነዚህንም ፍሬ ነገሮች
በፍሬ ነገር ማረጋገጫ ዓይነቶች-
• በፍርድ ቤት ፊት የሚሰጥ የእምነት ቃል (Formal Admission)፣
• የዳኞች ግንዛቤ መዉሰድ/መያዝ (Judicial Notice)፣
• የህግ ግምት (Presumption)፣
• የመኃላ ቃል (Oath)፣
• ማስረጃ (Evidence) ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
= የማይረጋገጡ ፍሬ ነገሮች
- በፍ/ቤት ፊት በተከራካሪ ወገን የታመኑ (Formally Admitted Facts)
- በዳኞች ግንዛቤ የሚያዝባቸው (Facts which judges take Judicial Notice)
- በህግ ግምት የሚወሰድባቸው (Presumed Facts) ሆነው ከተገኙ ነው፡፡
ስለዚህ እነዚህን ፍሬ ነገሮች ተጨማሪ ማስረጃ ማቅረብ ሳያስፈልግ በነዚህ በቀረቡት ሁኔታዎች ብቻ ማስረዳት ይቻላል፡፡
= አግባብነት ወይም አስፈላጊነት እና ተቀባይነት ያለዉ ማስረጃ ምንነት
አግባብነት፡- አግባብነት ሲባል አንድ ፍሬ ነገር ወይም ማስረጃ ከሌላ ፍሬ ነገር ወይም ማስረጃ ጋር ያለውን ተዛመዶ ወይም ትስስር የሚገልጽ ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት በተከራካሪ ወገን የሚቀርብ ማንኛዉም ማስረጃ ሳይሆን በግራቀኝ ለቀረበዉ ክርክር ተገቢነት ኖሮት ሊያስረዳ የሚችል ማለት ነዉ፡፡
ተቀባይነት፡- ሲባል አንድ ማስረጃ ለፍርድ ቤት ሲቀርብ ችሎቱ ይቀበለዋል ወይስ አይቀበለዉም የሚለዉን የሚያሳይ ነዉ፡፡ ችሎትም ማስረጃዉን ሊቀበለዉ ወይም ማስረጃዉን ሊተወዉ የሚችለዉ ደስ ስላለዉ ወይም ስላላለዉ ሳይሆን ማስረጃዉ በህጋዊ ሁኔታ መምጣት አለመምጣት ማጣራት እንዳለበት የሚያሳይ ሃሳብ ነዉ፡፡
= ማስረጃ ለማቅረብ ማን ይገደዳል ወይም የማን ሸክም ይሆናል?
ማስረጃ ለማቅረብ ማን ይገደዳል ሲባል መጀመሪያ ማስረጃ ማን ማቅረብ አለበት የሚለዉን ሃሳብ የሚያንጸባርቅ ነዉ፡፡ይህም ከሁለቱ ወገኖች አቤቱታ ይዘትና በህግ ተለይቶ ከተቀመጠው አንጻር ታይቶ የሚለይ ነው፡፡ በመሆኑም አንድ ነገር እንዳለ የሚከራከር ወገን ይህ ፍሬ ነገር ስለመኖሩ ቀድሞ የማስረዳት ወይም ማስረጃ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡ ፍሬነገሩም እንዳለ ተከራካሪዉ ካስረዳ ይህን ማስረጃ በማቅረብ መቀልበስ ወይም መቃወም ያለበት የሌላኛዉ ወገን ድርሻ ይሆናል ማለት ነዉ፡፡ይህም የማስረዳት ሸክም ዞረ ይባላል፡፡
= የማስረጃ አቀራረብ መንገዶች
በመሰረቱ ማስረጃ ለፍርድ ቤት መቅረብ ያለበት ከአቤቱታ ወይም ከመልስ ጋር ነዉ፡፡ ነገር ግን አንድ አንድ ማስረጃዎች በምንፈልገዉ ሰሀት እና በምንጠይቀዉ ሰአት ላናገኛቸዉ እንችላለን፡፡ እነዚህንም ማስረጃዎች በወንጀልም ይሁን በፍትሐብሔር ክርክሮች እንድናቀርብ የምንጠይቅባቸዉ አግባቦች አሉ፡፡ ይህም ሊሆን የሚችለዉ በማስረጃ ዝርዝራችን ላይ በፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲቀርቡ በመጠየቅ፣ክስ ከመሰማቱ በፊት በችሎት በማቅረብ፣ እንዲሁም ክርክሩ እየተካሄደ ባለበት ግዜ በበቂ ምክንያት ሳይቀርቡ የቀሩ ማስረጃዎች ለችሎቱ በማቅረብ ነዉ፡፡
ዉበአለም መስፍን የቦ/ክ/ከ/ፍ/ጽ/ቤት/የህ/ስ/ም/መ ዳይሬክቶሬት ዐ/ህግ
ምንጭ የቦሌ ክ/ከተማ የሕግ ስርፀትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት
👍5😁2
Characterization
ካልታተሙት የሰበር ውሳኔዎች መካከል በምርጥነት ከሚፈረጁት አንዱ ሰ/መ/ቁ 197753 ነው።
በዚህ መዝገብ ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ሲሰጡ መርሳት የሌለባቸውን መሰረታዊ ቁምነገር ያስጨብጣል። በችሎቱ የተነሳው ነጥብ ተፈጻሚውን ህግ አስቀድሞ መለየት ይመለከታል።
ተፈጻሚውን ህግ ለመለየት በመጀመሪያ ጉዳዩ በምን የህግ ክፍል ስር እንደሚወድቅ መመደብ characterization ያስፈልጋል። characterization በተለይ በ conflict of laws ክርክሩ በየትኛው አገር ህግ እንደሚገዛ ለመለት ወሳኝ ሂደት / stage of the procedure to resolve a lawsuit that involves foreign law/ ነው። አንድ ፍርድ ቤቱ ለክርክሩ ተፈጻሚነት ያለው ህግ የቻይና አሊያም የፈረንሳይ ወይም የኢትዮጵያ መሆኑን ለመወሰን በቅድሚያ የጉዳዩ ዓይነት የቤተሰብ፡ የውርስ፡ የውል፡ ከውል ውጭ ሀላፊነት ስር እንደሚወድቅ መወሰን አለበት። አንዳንድ ጊዜ በአንዱ የህግ ክፍል ስር እንዲሁ ንዑስ የህግ መደቡን መለየት አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ ጉዳዩ የቤተሰብ ህግ ስር የሚመደብ ቢሆንም ጋብቻ፡ እንደ ባልና ሚስት፡ ጉዲፈቻ ወዘተ ስር የሚወድቅ መሆኑ ካልተፈረጀ በስተቀር ተፈጻሚውን አገር ህግ ለመለየት የሚያስችሉትን conflict of laws ደንቦች ማወቅ ያስቸግራል።
ሁለተኛው characterization አስፈላጊ የሚሆንበት ሁኔታ በአንድ ክስ ላይ የተነሳ/ሱ/ መቃወሚያ/ዎች/ ለመወሰን ነው። አንድ ፍርድ ቤት የይርጋ ደንቦችን ተፈጻሚ ለማድረግ ጉዳዩ በየትኛው የህግ ክፍል ስር እንደሚወድቅ መወሰን ይኖርበታል። በተለይ በፍ/ህ/ቁ የተመለከተውን የይርጋ ደንብ ተፈጻሚ ለማድረግ ፍርድ ቤቱ በልዩ ህግ ላይ የተመለከተ ይርጋ አለመኖሩን ማረጋገጥ ይኖርበታል። “በልዩ ህግ ላይ ይርጋ የለም” ለማለት ጉዳዩ በየትኛው ልዩ ህግ ስር እንደሚመደብ መወሰን ይኖርበታል። ይህን ሳያደርግ የፍ/ህ/ቁ 1845 ተፈጻሚ ሊያደርግ አይችልም።
የሰበር ችሎት ከላይ በተጠቀሰው ሰ/መ/ቁ 197753 ላይ ተፈጻሚውን ህግ መለየትን አስመልክቶ የሰጠው ትርጉም የስር ፍርድ ቤቶች አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መመሪያ ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል።
ተፈጻሚውን ህግ አስቀድሞ መለየት የአንድ ፍርድ ቤት ዓይነተኛ ተግባርና ግዴታ ስለመሆኑ ችሎቱ በግልጽ አብራርቶ የሰጠው የህግ ትርጉም እንደሚከተለው ይነበባል።
የፍትሐብሔር ጉዳይ የቀረበለት ፍርድ ቤት በቀዳሚነት እንዲያከናውን ከሚጠበቁበት ተግባራት ውስጥ አንዱ እና መሠረታዊዉ ለቀረበለት ጉዲይ ተፈፃሚነት ያለዉ የህግ ክፍል የመለየት ተግባር (identification of applicable law) ነው፡፡ አስቀድሞ ይህን ማድረግ የቀረበው ክስ የክስ ምክንያት ያለው መሆን አለመሆኑ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ያለው መሆን አለመሆኑን እና ሌሎች የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ካሉ አስቀድሞ በመለየት መርምሮ ተገቢዉን ዉሳኔ ለመስጠት የሚያስችለዉ ሲሆን፣ ጉዳዩ ወደ ሙሉ የክርክር ሂደትት (full scale trial) የሚገባ ከሆነም በጉዳዩ ላይ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችለዉን ጭብጥ ይዞ ክርክሩን በመምራት ለጉዳዩ ተፈፃሚነት ያለዉን ድንጋጌ በአግባቡ ለይቶ ፍትሐዊ ውሳኔ ለመስጠት ያስችላል።
By Abrham Yohannes
https://t.me/lawsocieties
ካልታተሙት የሰበር ውሳኔዎች መካከል በምርጥነት ከሚፈረጁት አንዱ ሰ/መ/ቁ 197753 ነው።
በዚህ መዝገብ ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ሲሰጡ መርሳት የሌለባቸውን መሰረታዊ ቁምነገር ያስጨብጣል። በችሎቱ የተነሳው ነጥብ ተፈጻሚውን ህግ አስቀድሞ መለየት ይመለከታል።
ተፈጻሚውን ህግ ለመለየት በመጀመሪያ ጉዳዩ በምን የህግ ክፍል ስር እንደሚወድቅ መመደብ characterization ያስፈልጋል። characterization በተለይ በ conflict of laws ክርክሩ በየትኛው አገር ህግ እንደሚገዛ ለመለት ወሳኝ ሂደት / stage of the procedure to resolve a lawsuit that involves foreign law/ ነው። አንድ ፍርድ ቤቱ ለክርክሩ ተፈጻሚነት ያለው ህግ የቻይና አሊያም የፈረንሳይ ወይም የኢትዮጵያ መሆኑን ለመወሰን በቅድሚያ የጉዳዩ ዓይነት የቤተሰብ፡ የውርስ፡ የውል፡ ከውል ውጭ ሀላፊነት ስር እንደሚወድቅ መወሰን አለበት። አንዳንድ ጊዜ በአንዱ የህግ ክፍል ስር እንዲሁ ንዑስ የህግ መደቡን መለየት አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ ጉዳዩ የቤተሰብ ህግ ስር የሚመደብ ቢሆንም ጋብቻ፡ እንደ ባልና ሚስት፡ ጉዲፈቻ ወዘተ ስር የሚወድቅ መሆኑ ካልተፈረጀ በስተቀር ተፈጻሚውን አገር ህግ ለመለየት የሚያስችሉትን conflict of laws ደንቦች ማወቅ ያስቸግራል።
ሁለተኛው characterization አስፈላጊ የሚሆንበት ሁኔታ በአንድ ክስ ላይ የተነሳ/ሱ/ መቃወሚያ/ዎች/ ለመወሰን ነው። አንድ ፍርድ ቤት የይርጋ ደንቦችን ተፈጻሚ ለማድረግ ጉዳዩ በየትኛው የህግ ክፍል ስር እንደሚወድቅ መወሰን ይኖርበታል። በተለይ በፍ/ህ/ቁ የተመለከተውን የይርጋ ደንብ ተፈጻሚ ለማድረግ ፍርድ ቤቱ በልዩ ህግ ላይ የተመለከተ ይርጋ አለመኖሩን ማረጋገጥ ይኖርበታል። “በልዩ ህግ ላይ ይርጋ የለም” ለማለት ጉዳዩ በየትኛው ልዩ ህግ ስር እንደሚመደብ መወሰን ይኖርበታል። ይህን ሳያደርግ የፍ/ህ/ቁ 1845 ተፈጻሚ ሊያደርግ አይችልም።
የሰበር ችሎት ከላይ በተጠቀሰው ሰ/መ/ቁ 197753 ላይ ተፈጻሚውን ህግ መለየትን አስመልክቶ የሰጠው ትርጉም የስር ፍርድ ቤቶች አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መመሪያ ተደርጎ መወሰድ ይኖርበታል።
ተፈጻሚውን ህግ አስቀድሞ መለየት የአንድ ፍርድ ቤት ዓይነተኛ ተግባርና ግዴታ ስለመሆኑ ችሎቱ በግልጽ አብራርቶ የሰጠው የህግ ትርጉም እንደሚከተለው ይነበባል።
የፍትሐብሔር ጉዳይ የቀረበለት ፍርድ ቤት በቀዳሚነት እንዲያከናውን ከሚጠበቁበት ተግባራት ውስጥ አንዱ እና መሠረታዊዉ ለቀረበለት ጉዲይ ተፈፃሚነት ያለዉ የህግ ክፍል የመለየት ተግባር (identification of applicable law) ነው፡፡ አስቀድሞ ይህን ማድረግ የቀረበው ክስ የክስ ምክንያት ያለው መሆን አለመሆኑ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ያለው መሆን አለመሆኑን እና ሌሎች የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያዎች ካሉ አስቀድሞ በመለየት መርምሮ ተገቢዉን ዉሳኔ ለመስጠት የሚያስችለዉ ሲሆን፣ ጉዳዩ ወደ ሙሉ የክርክር ሂደትት (full scale trial) የሚገባ ከሆነም በጉዳዩ ላይ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችለዉን ጭብጥ ይዞ ክርክሩን በመምራት ለጉዳዩ ተፈፃሚነት ያለዉን ድንጋጌ በአግባቡ ለይቶ ፍትሐዊ ውሳኔ ለመስጠት ያስችላል።
By Abrham Yohannes
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
❤3
አለአግባብ መበልጸግ በኢትዮጵያ ህግ
=============================⤵️
ያለአግባብ መበልፀግ ህግ የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጭ ያለ ሃላፊነት ህግ ክፍል በተጨማሪ የፍታብሔር ግንኙነትን የሚገዛ የህግ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህግ ክፍል የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጪ ያለ ሃላፊነት ህጎች የማይገዙትን የሰው ግንኝኑነት ክፍተት ለመሙላት በስፋት ጥቅም ላይ የሚውል ህግ ሲሆን ከዚህ ባሻገር ይህ የህግ ክፍል የሰዎችን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከመግዛት አኳያ ሰፊ ድርሻ ያለው ነው፡፡
ያለአግባብ መልፀግ ህግ በመሰረታዊነት የሚመነጨው ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መበልፀግ የለበትም ከሚለው መርህ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛው ሰው በሌላ ሰው ጉዳት ወይም ኪሳራ ምክንያት ያለአግባብ የበለፀገ እንደሆነ ጉዳት ወይም ኪሳራ ለደረሰበት ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት ይህ የህግ ክፍል ያስገድዳል፡፡
አጠቃላይ መርሆዎች
የዚህ ህግ ዋንኛ አላማ ሰዎች በገንዘባቸው፣ በንብረታቸው እና በጉልበታቸው ላይ ሚኖራቸውን ህጋዊ መብት መጠበቅ ነው፡፡
ይቀጥላል..... 👇👇👇👇👇👇
=============================⤵️
ያለአግባብ መበልፀግ ህግ የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጭ ያለ ሃላፊነት ህግ ክፍል በተጨማሪ የፍታብሔር ግንኙነትን የሚገዛ የህግ ክፍል ነው፡፡ ይህ የህግ ክፍል የውል፣ የንብረት እና ከውል ውጪ ያለ ሃላፊነት ህጎች የማይገዙትን የሰው ግንኝኑነት ክፍተት ለመሙላት በስፋት ጥቅም ላይ የሚውል ህግ ሲሆን ከዚህ ባሻገር ይህ የህግ ክፍል የሰዎችን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከመግዛት አኳያ ሰፊ ድርሻ ያለው ነው፡፡
ያለአግባብ መልፀግ ህግ በመሰረታዊነት የሚመነጨው ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መበልፀግ የለበትም ከሚለው መርህ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛው ሰው በሌላ ሰው ጉዳት ወይም ኪሳራ ምክንያት ያለአግባብ የበለፀገ እንደሆነ ጉዳት ወይም ኪሳራ ለደረሰበት ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርበት ይህ የህግ ክፍል ያስገድዳል፡፡
አጠቃላይ መርሆዎች
የዚህ ህግ ዋንኛ አላማ ሰዎች በገንዘባቸው፣ በንብረታቸው እና በጉልበታቸው ላይ ሚኖራቸውን ህጋዊ መብት መጠበቅ ነው፡፡
ይቀጥላል..... 👇👇👇👇👇👇
👍5
አለአግባብ መበልጸግ በኢትዮጵያ ህግ
=============================⤵️የቀጠለ👆👆👆👆👆
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ስለሆነም የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2162 ስር ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም የሌላ ሰው ሀብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ እና ባለሀብቱ ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ጥቅም ባገኘበት ልክ ለባለሀብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ በስሩ የያዛቸው ነጥቦችን ስንመለከት ያለአግባብ የመበልጸግ ህግ ማንኛውም ሰው (ማለትም የተፈጥሮ ወይም የህግ ሰውነት ያለው ሰው) ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን እንደመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ በዚህ ህግ ተጠያቂ የሚሆን ሰው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም ሊያገኝ ይገባል፡፡ ይህም ማለት ጥቅሙ በንብት ላይ የተቋቋመ (right in rem) ወይም ከሌላ ሰው የሚጠየቅ መብት (right in personam) ወይም የነበረ እዳ የመሰረዝ፣ ግዴታ የመቅረት አይነት ወይም የኪሳራ መቅረት አይነት ጥቅም ሊሆን የሚችል ሲሆን ይህ ጥቅም ያለአግባብ የመበልፀግ የህግ ክፍል ስር ሊያስቀጣ የሚችለው ጥቅሙ የህሊና እርካታ ሊያስገኝ የሚችል ብቻ ሳይሆን በገንዘብ ሊለካ የሚችል ሲሆን ብቻ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ የተገኘው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም በሌላ ሰው የሚንቀሳቀስ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ወይም ስራ ምክንያት የተገኘ መሆን ያለበት ሲሆን ጥቅሙን ያገኘው ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት የሌለው መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆንም በዚህ የህግ ክፍል ተጠያቂ የሚያደርግ ክስ የቀረበበት ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ማንኛውም ህጋዊ ምክንያት ያቀረበ እንደሆነ ካሳ መክፈል ግዴታ አይኖርበትም፡፡ ሌላው በህጉ የተቀመጠው ቅድመሁኔታ በተከሳሽ ድርጊት ምክንያት ከሳሽ የሚታወቅ ኪሳራ ወይም ድህነት ሊደርስበት ሚገባ ሲሆን የከሳሽ ጥቅም ማጣት (ኪሳራ) እና የተከሳሽ ጥቅም ማግኘት ምክንያት አንድ መሆን አለበት፡፡ ይህም ማለት በደረሰው ኪሳራ እና በተገኘው ጥቅም መካከል የውጤት እና የምክንያት ግንኝነት መኖር አለበት፡፡
ከላይ የተዘረዘሩ ሁኔታዎች ከተሟሉ በኋላ ሃላፊነትን የሚወስድ ሰው በምን ያህል መጠን ከሳሽን የመካስ ግዴታ አለበት የሚለውን በተመለከተ የተገኘው ጥቅም እና የደረሰው ኪሳራ እኩል በሚሆንበት ግዜ ምንም አይነት ችግር ሊገጥም አይችልም ምክንያቱም ተከሳሽ አለአግባብ የበለፀገበት መጠን እና ከሳሽ ላይ የደረሰው ጉዳት እኩል ስለሆነ በዚሁ ልክ ካሳ እንዲከፍ ይደረጋል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ ሁኔታዎች ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት ሊያንስ ወይም ሊበልጥ ይችላል፡፡ እንዲህ አይነት ሁኔታ በሚያጋጥምበት ግዜ ምንም እንኳን የደረሰው ጉዳት ከተገኘው ብልፅግና የሚያንስ ቢሆንም ህጉ በግልፅ ተከሳሽ መክፈል ያለበት ኪሳራ ያለአግባብ ባገኘው ብልፅግና መጠን መሆን እንደሚገባው ያስቀምጣል፡፡ በተመሳሳይ ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት የሚያንስ ከሆነ ወይም ጉዳቱ ከብፅግናው የሚበልጥ በሚሆንበት ግዜ የተከሳሽ ተጠያቂነት መጠን በተገኘው ብልፅግና ልክ ብቻ በመሆኑ ካሳ እንዲከፍል የሚገደደውም በዚሁ መጠን ብቻ ይሆናል፡፡
በአጠቃላይ ያአለአግባብ መበልፀግ በመሰረታዊነት ሶስት ሁኔታዎችን ያካተተ ሲሆን አንድን ሰው በዚህ የህግ ክፍል በመክሰስ ካሳ ለማስከፈል እነዚህ ሶስት ሁኔታዎች በድምር መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ የመጀመሪያው ተከሳሽ በገንዘብ ሊለካ የሚችል ጥቅም ያገኘ መሆኑ ሁለተኛው ይህ ጥቅም የተገኘው በከሳሽ ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መሆኑ እንዲሁም ሶስተኛው የተገኘበት መንገድ አለአግባብ ወይም ምንም አይነት ህጋዊ መንገድ/ምክንያት የማይቀርብበት መንገድ መሆኑ ናቸው፡፡
ያለአግባብ የመበልፅ ክሶችን ይበልጥ ለመረዳት ፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 34406 የሰጠውን ውሳኔ መመልከት ይቻልል፡፡ በዚህ መዝገብ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ሰዎች ባለቤት እና አባት የሆኑት ግለሰብ መኖሪያ ቤታቸውን ያከራዩት ሰው ለተከሳሽ ቤቱን አስረክቦ ይጠፋል፡፡ የቤቱ ህጋዊ ዋራሽ ከሳሾች ቤቱን ለተረከቡት ግለሰብ ቤቱን ለቀው እንዲያስረክቧቸው ቢጠይቋቸውም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲያስረክቡ እና ንብረቱን በያዙበት ወቅት ያለክራይ በመኖር ያገኙትን ያለአግባብ ብልፅግና እንዲከፍሉ ክስ አቅርበዋል፡፡ ተከሳሽም በሰጡት መልስ ቤቱን ያለአግባብ ይዛለች ከተባለ እንኳን ይህን ካወቁ 10 ዓመት በላይ ስለሆነ በይርጋ ይታገዳል፣ የደረሰባቸው የጥቅም ጉዳት ከውል ውጪ እንደመሆኑ የኪራይ ማስከፈል ጥያቄአቸው ሁለት አመት ካለፈው በይርጋ ይታገዳል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን ከመረመሩ በኋላ ተከሳሽ ያለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲመልሱ እና ከንብረቱ ያለአግባብ የተጠቀሙትን መጠን ካሳ እንዲከፍሉ ወስነው ተከሳሽም በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለሰበር ሰሚ ችሎቱ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ የሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ግለሰቦች ይዞታችን በሃይል ተወስዷል ወይም በይዞታችን ላይ ሁከት ተፈጥሯል በማለት ያቀረቡት ክስ የለም ክሣቸው በኪራይ የተረከቡትን ቤት ተከሳሽ መብት ሣይኖራቸው ገብተው አልወጣም ብለዋልና አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲለቁ የቀረበ ክስ ስለሆነ 10 ዓመት ቢያልፈው እንኳን በይርጋ አይታገድም፡፡ በጨማሪም ተከሳሽ የቀረበው የካሣ ጥያቄም ቢሆን በይርጋ ቀሪ ይሆናል በሚል ያቀረቡት ክርክር በተመለከተ ማንኛውም በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም በሌላ ሰው ሃብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ ሰው ጥቅም ባገኘበት መጠን ለባለሃብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ኪሣራ መክፈል እንዳለበት በፍ/ህ/ቁ. 2162 ሥር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ከሳሽ በቤቱ አላግባብ በበለፀጉበት መጠን ኪሣራ እንዲከፈላቸው መጠየቃቸው ህጉን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የካሣ ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባበት የጊዜ ገደብ በተመለከተ ክርክር ቀርቧል፡፡ ያለአግባብ ስለመበልፀግ የሚናገረው ምእራፍ የካሣ ጥያቄ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ አይናገርም፡፡ ነገር ግን አላግባብ ስለመበልፀግና ከውል ውጪ ስለሚደርስ ሃላፊነት የሚናገሩት ድንጋጌዎች በአንድ አንቀጽ ውስጥ ተካትተው መገኘታቸው እንዲሁም ያለአግባብ መበልፀግም ከውል ውጪ የሚደርስ ሃላፊነት በመሆኑ ከውል ውጭ የሚደርስ ሃላፊነት ሥር የተመለከተው የይርጋ ዘመን በተመሣሣይ አላግባብ መበልፀግ በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡ በዚህ መሰረት ከውል ውጭ ሃላፊነትን በተመለከተ ተበዳዩ ክስ ማቅረብ የሚችለው ካሣ የሚጠይቅበት ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 2 አመት ድረስ መሆኑ በፍ/ህ/ቁ 2143/1/ ሥር ተመልክቷል፡፡ ስለሆነም ተከሳሽ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ ላሉት ሁለት አመታት አላግባብ በቤቱ በተገለገሉበት መጠን እንዲከፈሉ የተጠየቁት ካሣ በይጋ የሚታገድ አይሆንም:: ሆኖም ከዛ በፊት ያሉት ግዜያት የተጠቀሙት ክፍያ ግን በይርጋ ቀሪ የሚሆኑ ናቸው በማለት ወስኗል፡፡
=============================⤵️የቀጠለ👆👆👆👆👆
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ስለሆነም የፍታብሔር ህጋችን በቁጥር 2162 ስር ማንኛውም ሰው በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም የሌላ ሰው ሀብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ እና ባለሀብቱ ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ጥቅም ባገኘበት ልክ ለባለሀብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ካሳ የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡ ይህ ድንጋጌ በስሩ የያዛቸው ነጥቦችን ስንመለከት ያለአግባብ የመበልጸግ ህግ ማንኛውም ሰው (ማለትም የተፈጥሮ ወይም የህግ ሰውነት ያለው ሰው) ላይ ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን እንደመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ በዚህ ህግ ተጠያቂ የሚሆን ሰው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም ሊያገኝ ይገባል፡፡ ይህም ማለት ጥቅሙ በንብት ላይ የተቋቋመ (right in rem) ወይም ከሌላ ሰው የሚጠየቅ መብት (right in personam) ወይም የነበረ እዳ የመሰረዝ፣ ግዴታ የመቅረት አይነት ወይም የኪሳራ መቅረት አይነት ጥቅም ሊሆን የሚችል ሲሆን ይህ ጥቅም ያለአግባብ የመበልፀግ የህግ ክፍል ስር ሊያስቀጣ የሚችለው ጥቅሙ የህሊና እርካታ ሊያስገኝ የሚችል ብቻ ሳይሆን በገንዘብ ሊለካ የሚችል ሲሆን ብቻ ነው፡፡ በተጨማሪም ይህ የተገኘው የገንዘብ ወይም የንብረት ጥቅም በሌላ ሰው የሚንቀሳቀስ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ወይም ስራ ምክንያት የተገኘ መሆን ያለበት ሲሆን ጥቅሙን ያገኘው ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት የሌለው መሆን ይኖርበታል፡፡ ስለሆንም በዚህ የህግ ክፍል ተጠያቂ የሚያደርግ ክስ የቀረበበት ሰው ጥቅሙን ላገኘበት ማንኛውም ህጋዊ ምክንያት ያቀረበ እንደሆነ ካሳ መክፈል ግዴታ አይኖርበትም፡፡ ሌላው በህጉ የተቀመጠው ቅድመሁኔታ በተከሳሽ ድርጊት ምክንያት ከሳሽ የሚታወቅ ኪሳራ ወይም ድህነት ሊደርስበት ሚገባ ሲሆን የከሳሽ ጥቅም ማጣት (ኪሳራ) እና የተከሳሽ ጥቅም ማግኘት ምክንያት አንድ መሆን አለበት፡፡ ይህም ማለት በደረሰው ኪሳራ እና በተገኘው ጥቅም መካከል የውጤት እና የምክንያት ግንኝነት መኖር አለበት፡፡
ከላይ የተዘረዘሩ ሁኔታዎች ከተሟሉ በኋላ ሃላፊነትን የሚወስድ ሰው በምን ያህል መጠን ከሳሽን የመካስ ግዴታ አለበት የሚለውን በተመለከተ የተገኘው ጥቅም እና የደረሰው ኪሳራ እኩል በሚሆንበት ግዜ ምንም አይነት ችግር ሊገጥም አይችልም ምክንያቱም ተከሳሽ አለአግባብ የበለፀገበት መጠን እና ከሳሽ ላይ የደረሰው ጉዳት እኩል ስለሆነ በዚሁ ልክ ካሳ እንዲከፍ ይደረጋል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ ሁኔታዎች ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት ሊያንስ ወይም ሊበልጥ ይችላል፡፡ እንዲህ አይነት ሁኔታ በሚያጋጥምበት ግዜ ምንም እንኳን የደረሰው ጉዳት ከተገኘው ብልፅግና የሚያንስ ቢሆንም ህጉ በግልፅ ተከሳሽ መክፈል ያለበት ኪሳራ ያለአግባብ ባገኘው ብልፅግና መጠን መሆን እንደሚገባው ያስቀምጣል፡፡ በተመሳሳይ ያለአግባብ የተገኘው ብልፅግና ከደረሰው ጉዳት የሚያንስ ከሆነ ወይም ጉዳቱ ከብፅግናው የሚበልጥ በሚሆንበት ግዜ የተከሳሽ ተጠያቂነት መጠን በተገኘው ብልፅግና ልክ ብቻ በመሆኑ ካሳ እንዲከፍል የሚገደደውም በዚሁ መጠን ብቻ ይሆናል፡፡
በአጠቃላይ ያአለአግባብ መበልፀግ በመሰረታዊነት ሶስት ሁኔታዎችን ያካተተ ሲሆን አንድን ሰው በዚህ የህግ ክፍል በመክሰስ ካሳ ለማስከፈል እነዚህ ሶስት ሁኔታዎች በድምር መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ የመጀመሪያው ተከሳሽ በገንዘብ ሊለካ የሚችል ጥቅም ያገኘ መሆኑ ሁለተኛው ይህ ጥቅም የተገኘው በከሳሽ ኪሳራ ወይም ጉዳት ምክንያት መሆኑ እንዲሁም ሶስተኛው የተገኘበት መንገድ አለአግባብ ወይም ምንም አይነት ህጋዊ መንገድ/ምክንያት የማይቀርብበት መንገድ መሆኑ ናቸው፡፡
ያለአግባብ የመበልፅ ክሶችን ይበልጥ ለመረዳት ፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 34406 የሰጠውን ውሳኔ መመልከት ይቻልል፡፡ በዚህ መዝገብ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ሰዎች ባለቤት እና አባት የሆኑት ግለሰብ መኖሪያ ቤታቸውን ያከራዩት ሰው ለተከሳሽ ቤቱን አስረክቦ ይጠፋል፡፡ የቤቱ ህጋዊ ዋራሽ ከሳሾች ቤቱን ለተረከቡት ግለሰብ ቤቱን ለቀው እንዲያስረክቧቸው ቢጠይቋቸውም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲያስረክቡ እና ንብረቱን በያዙበት ወቅት ያለክራይ በመኖር ያገኙትን ያለአግባብ ብልፅግና እንዲከፍሉ ክስ አቅርበዋል፡፡ ተከሳሽም በሰጡት መልስ ቤቱን ያለአግባብ ይዛለች ከተባለ እንኳን ይህን ካወቁ 10 ዓመት በላይ ስለሆነ በይርጋ ይታገዳል፣ የደረሰባቸው የጥቅም ጉዳት ከውል ውጪ እንደመሆኑ የኪራይ ማስከፈል ጥያቄአቸው ሁለት አመት ካለፈው በይርጋ ይታገዳል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች ጉዳዩን ከመረመሩ በኋላ ተከሳሽ ያለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲመልሱ እና ከንብረቱ ያለአግባብ የተጠቀሙትን መጠን ካሳ እንዲከፍሉ ወስነው ተከሳሽም በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ለሰበር ሰሚ ችሎቱ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ የሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ የሆኑት ግለሰቦች ይዞታችን በሃይል ተወስዷል ወይም በይዞታችን ላይ ሁከት ተፈጥሯል በማለት ያቀረቡት ክስ የለም ክሣቸው በኪራይ የተረከቡትን ቤት ተከሳሽ መብት ሣይኖራቸው ገብተው አልወጣም ብለዋልና አለአግባብ የያዙትን ንብረት እንዲለቁ የቀረበ ክስ ስለሆነ 10 ዓመት ቢያልፈው እንኳን በይርጋ አይታገድም፡፡ በጨማሪም ተከሳሽ የቀረበው የካሣ ጥያቄም ቢሆን በይርጋ ቀሪ ይሆናል በሚል ያቀረቡት ክርክር በተመለከተ ማንኛውም በሌላ ሰው የስራ ድካም ወይም በሌላ ሰው ሃብት በሆነ ነገር በመገልገል በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅም ያገኘ ሰው ጥቅም ባገኘበት መጠን ለባለሃብቱ ወይም ጉልበቱ ለደከመው ሰው ኪሣራ መክፈል እንዳለበት በፍ/ህ/ቁ. 2162 ሥር ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም ከሳሽ በቤቱ አላግባብ በበለፀጉበት መጠን ኪሣራ እንዲከፈላቸው መጠየቃቸው ህጉን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የካሣ ጥያቄ ሊቀርብ የሚገባበት የጊዜ ገደብ በተመለከተ ክርክር ቀርቧል፡፡ ያለአግባብ ስለመበልፀግ የሚናገረው ምእራፍ የካሣ ጥያቄ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ አይናገርም፡፡ ነገር ግን አላግባብ ስለመበልፀግና ከውል ውጪ ስለሚደርስ ሃላፊነት የሚናገሩት ድንጋጌዎች በአንድ አንቀጽ ውስጥ ተካትተው መገኘታቸው እንዲሁም ያለአግባብ መበልፀግም ከውል ውጪ የሚደርስ ሃላፊነት በመሆኑ ከውል ውጭ የሚደርስ ሃላፊነት ሥር የተመለከተው የይርጋ ዘመን በተመሣሣይ አላግባብ መበልፀግ በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት ሊኖረው ይገባል፡፡ በዚህ መሰረት ከውል ውጭ ሃላፊነትን በተመለከተ ተበዳዩ ክስ ማቅረብ የሚችለው ካሣ የሚጠይቅበት ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 2 አመት ድረስ መሆኑ በፍ/ህ/ቁ 2143/1/ ሥር ተመልክቷል፡፡ ስለሆነም ተከሳሽ ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ኋላ ላሉት ሁለት አመታት አላግባብ በቤቱ በተገለገሉበት መጠን እንዲከፈሉ የተጠየቁት ካሣ በይጋ የሚታገድ አይሆንም:: ሆኖም ከዛ በፊት ያሉት ግዜያት የተጠቀሙት ክፍያ ግን በይርጋ ቀሪ የሚሆኑ ናቸው በማለት ወስኗል፡፡
👍8