👇👇👇👇👇👇የቀጠለ👇👇
#ጠበቆች የባለጉዳዮች ወኪል ብቻ ሳይሆኑ የፍትህ አስተዳደሩም ዋልታ በመሆናቸው ጭምር ፍርድ ቤቶች በእውነት ላይ እንዲያደርሱና ፍትሃዊና ሚዛናዊነትን የተላበሰ ውሳኔ እንዲሰጡ መርዳት አለባቸው፡፡
ከዚህ አንፃር የፌዴራል ፍ/ቤቶች ጠበቆች ስነ ምግባር ደንብ የሚከተሉትን ግዴታዎች በጠበቆች ላይ ጥሏል፡፡
I) #በምቀኝነት ወይም በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ሌላውን ወገን የሚጎዳ ክስ ወይም ክርክር አለማቅረብ፣
#ደንበኛው የወራዳነት ወይም የማጭበርበር ድርጊት እንዲፈፅም አለማበረታታት ወይም አለመፍቀድ፣
#ዳኛን ወይም ሌላ የፍ/ቤት ሰራተኛን በህግ መሰረት ከማሳመን ውጪ ሌላ ተገቢ ያልሆነ ማንኛውም አይነት ዘዴ በመጠቀም ተፅህኖ ለማሳደር አለመሞከር ወይም ሌላ ሰው እንዲሞክር አለመገፋፋት ፣
#ሆነ ብሎ ፍ/ቤትን የሚያሳስት የተጋነነ ፅሁፈ ንግግር ለፍርድ ቤት አለማቅረብ፣
#በምስክርነት ቃል ወይም የሰነድ ይዘት ላይ የሀሰት ድርጊት በመፈፀም ፍርድ ቤትን ለማሳሳት አለመሞከር፣
#በግልፅ ለጉዳዮ አግባብነት የሌለውን ማስረጃ አግባብነት ያለው አስመስሎ ለፍርድ ቤት አለማቅረብ፣
#ለጉዳዮ በምስክርነት መቅረብ የሚገባው ሰው ፍርድ ቤት እንዳይቀርብ አለማባበል ወይም አለመሞከር
አንድን ምስክር ተገቢ ባልሆነ መንገድ አለማመናጨቅ፣ አለማስጨነቅ፣ወይም አለማስፈራራት ናቸው፡፡
በጥቅሉ የባለጉዳይን ጥቅም ከማስጠበቅ የተሻገረ ኃላፊነት እንዳለበት አውቆ ፍርድ ቤቱ ከእውነተኛና ፍትሃዊ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ የሚጠበቅበት ሲሆን የጥብቅና ስራውንም በቅን ልቦና ማከናወን ይጠበቅበታል፡፡
ሌላኛውና ዋንኛው የጠበቆች የስነ ምግባር ግዴታ ጠበቆች ከደንበኞቻቸው አንፃር ያለባቸው ግዴታ ነው፡፡
J) #በዚህ ረገድ የጠበቆች ዋንኛ ግዴታ የሚሆነው ባለጉዳዮች ዳኝነት ከጠየቁበት የክርክር ጭብጥ አንፃር ያላቸውን መብትና ግዴታ እንዲሁም መብታቸውን ለማስከበርና ግዴታቸውን ለመወጣት ህጉ የሚደነግጋቸውን አካሄዶችና ስነ ስርዓቶች እንዲያውቁ ማድረግ ነው፡፡ ከዚሀ ጋር ተያይዞ የባለጉዳዮችን መብትና ጥቅም ለማስከበር እነርሱን ወክሎ ክርክር በማቅረብ መብታቸውና ጥቅማቸው እንዲከበር ዕውቀቱንና የስራ ልምዱን ስራ ላይ ማዋል ነው፡፡ ከዚህም በላይ የደንበኛውን ጉዳይ ከመደበኛ ፍርድ ቤት ወይም አስተዳደራዊ የዳኝነት አካላት ዘንድ በመውሰድ የደንበኛውን ጉዳይ በትጋት መከታተል፣ አፋጣኝና ፍትሃዊ ውሳኔ እንዲያገኝም ሙያዊ ጥንቃቄ ብርቱ ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥም ጉዳዩ የደረሰበትን ደረጃ በየጊዜው ለደንበኛው የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
ጠበቆች ሁሌም ቢሆን የደንበኞቻቸው ጥቅም ለማስጠበቅ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ለደንበኞቻቸው ጥቅም መከበርም በፍፁም ታማኝነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል፡፡
K) #በዚህ ረገድ በጠበቃውና በደንበኛው፣ ወይም በጠበቃው ዘመዶችና በደንበኛው፣ወይም ጠበቃው በወከላቸው የተለያዩ ደንበኞች መካከል የጥቅም ግጭት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም በጥብቅና አገልግሎቱ ምክንያት ያወቃቸውን የደንበኛውን የግል ወይም የስራ ሚስጥሮችን መጠበቅ አለበት፡፡ ደንበኛው ሳይፈቅድለት በሙያው ምክንያት እጁ የገቡትን ማናቸውንም የደንበኛውን ሚስጥሮች ለሌላ አካል አሳልፎ ሊሰጥ አይችልም፡፡ ራሱም ቢሆን በህግ በተፈቀዱለት ጥቂት ሁኔታዎች ካልሆነ በቀር ሊጠቀምበት አይችልም፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ጠበቆች ለሌሎች ሶስተኛ ወገኖችም ቅን የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡ በተለይም ሌሎች ተከራካሪዎችን ለማጉላላት በማሰብ አከራካሪ የሆነ ጭብጥ ወይም በሌላኛው ተከራካሪ ላይ ኃላፊነትን ሊያስከትል የሚችል ውጤት የሌለ መሆኑ በግልፅ አኳኋን የሚታይበት ሁኔታ ቅንነትን በማጣት ተገቢ ያልሆነ ክርክር በተቃራኒ ወገኖች ላይ መጀመር የለበትም፡፡
L) #ከዚህ አንፃር በተለይም ከዚህ በታች ከተገለፁት ድርጊቶች መቆጠብ አለበት፡፡ እነዚህም፡-
ተቃራኒ ወገን ማስረጃ እንዳያገኝ ማንኛውንም እንቅፋት መፍጠር ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር ወይም መረዳት፣
ማስረጃን ማሳሳት ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር መርዳት፣
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌለው ወይም በማስረጀ ሊደገፍ የማይችል ነገር ማቅረብ
በምስክርነት ካልቀረበ በቀር በግል የሚያውቀውን የጭብጥ ነገሮች መሰንዘር ወይም የጉዳዩን ፍትሃዊነት የአንድን ምስክር ተዓሚነት፣ የተከሳሽን ጥፋተኛ ወይም ተጠያቂ መሆንና አለመሆን አስመልክቶ የግል አስተያየቱን መስጠት
ደንበኛው ወይም ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ የማይገደዱ ሰዎችን በተመለከተ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ማንኛውንም ሰው ለተቃራኒ ወገን የምስክርነት ቃሉን ወይም ሌላ አግባብነት ያለው ማስረጃ እንዳይሰጥ መገፋፋት ናቸው፡፡
በመጨረሻም ጠበቆችም ፍትሃዊ ዳኝነት እንዲጎለብት እንዲሁም የደንበኞቻቸው መብትና ጥቅም እንዲጠበቅ የማድረግ ድርብ ኃላፊነት ሲኖርባቸው እነዚህን ኃላፊነቶች በተጣጣመ መልኩ ነው ማከናወን ያለባቸው፡፡ ከዚህ አኳያ ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነፃነቶች መከበር በትጋት መቆምና መስራት ይኖርባቸዋል፡፡
M) #በዚህ ረገድ የደንበኛቸውን ጥቅም ማስጠበቅና ለፍትህ መከበርም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ መካከል የሚታየውን ክፍተት ለማጣጣመና ሚዛናዊ ለማድረግ መጣር አለባቸው፡፡ ጠበቆች ሙያቸው የግለሰቦች መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች እንደከበሩና እንዲጐለብቱ የማድረግ ልዩ ኃላፊነት ወይም ግዴታ እንደጣለባቸው በመገንዘብ ይህንን ከፍተኛ የሙያ ግዴታ ለመወጣት ከፍተኛ ስነምግባር መላበስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለፍትህ ሥርዓቱ መጐልበትና ለሰብዓዊ መብቶች መከበርም ዘወትር የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት መሥራት እንደሚገባቸውና በዚህ ሂደት ውስጥም ለሙያቸው ስነምግባር መገዛት እንደሚጠበቅባቸው ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡
https://t.me/lawsocieties
#ጠበቆች የባለጉዳዮች ወኪል ብቻ ሳይሆኑ የፍትህ አስተዳደሩም ዋልታ በመሆናቸው ጭምር ፍርድ ቤቶች በእውነት ላይ እንዲያደርሱና ፍትሃዊና ሚዛናዊነትን የተላበሰ ውሳኔ እንዲሰጡ መርዳት አለባቸው፡፡
ከዚህ አንፃር የፌዴራል ፍ/ቤቶች ጠበቆች ስነ ምግባር ደንብ የሚከተሉትን ግዴታዎች በጠበቆች ላይ ጥሏል፡፡
I) #በምቀኝነት ወይም በክፉ ልቦና ተነሳስቶ ሌላውን ወገን የሚጎዳ ክስ ወይም ክርክር አለማቅረብ፣
#ደንበኛው የወራዳነት ወይም የማጭበርበር ድርጊት እንዲፈፅም አለማበረታታት ወይም አለመፍቀድ፣
#ዳኛን ወይም ሌላ የፍ/ቤት ሰራተኛን በህግ መሰረት ከማሳመን ውጪ ሌላ ተገቢ ያልሆነ ማንኛውም አይነት ዘዴ በመጠቀም ተፅህኖ ለማሳደር አለመሞከር ወይም ሌላ ሰው እንዲሞክር አለመገፋፋት ፣
#ሆነ ብሎ ፍ/ቤትን የሚያሳስት የተጋነነ ፅሁፈ ንግግር ለፍርድ ቤት አለማቅረብ፣
#በምስክርነት ቃል ወይም የሰነድ ይዘት ላይ የሀሰት ድርጊት በመፈፀም ፍርድ ቤትን ለማሳሳት አለመሞከር፣
#በግልፅ ለጉዳዮ አግባብነት የሌለውን ማስረጃ አግባብነት ያለው አስመስሎ ለፍርድ ቤት አለማቅረብ፣
#ለጉዳዮ በምስክርነት መቅረብ የሚገባው ሰው ፍርድ ቤት እንዳይቀርብ አለማባበል ወይም አለመሞከር
አንድን ምስክር ተገቢ ባልሆነ መንገድ አለማመናጨቅ፣ አለማስጨነቅ፣ወይም አለማስፈራራት ናቸው፡፡
በጥቅሉ የባለጉዳይን ጥቅም ከማስጠበቅ የተሻገረ ኃላፊነት እንዳለበት አውቆ ፍርድ ቤቱ ከእውነተኛና ፍትሃዊ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ የሚጠበቅበት ሲሆን የጥብቅና ስራውንም በቅን ልቦና ማከናወን ይጠበቅበታል፡፡
ሌላኛውና ዋንኛው የጠበቆች የስነ ምግባር ግዴታ ጠበቆች ከደንበኞቻቸው አንፃር ያለባቸው ግዴታ ነው፡፡
J) #በዚህ ረገድ የጠበቆች ዋንኛ ግዴታ የሚሆነው ባለጉዳዮች ዳኝነት ከጠየቁበት የክርክር ጭብጥ አንፃር ያላቸውን መብትና ግዴታ እንዲሁም መብታቸውን ለማስከበርና ግዴታቸውን ለመወጣት ህጉ የሚደነግጋቸውን አካሄዶችና ስነ ስርዓቶች እንዲያውቁ ማድረግ ነው፡፡ ከዚሀ ጋር ተያይዞ የባለጉዳዮችን መብትና ጥቅም ለማስከበር እነርሱን ወክሎ ክርክር በማቅረብ መብታቸውና ጥቅማቸው እንዲከበር ዕውቀቱንና የስራ ልምዱን ስራ ላይ ማዋል ነው፡፡ ከዚህም በላይ የደንበኛውን ጉዳይ ከመደበኛ ፍርድ ቤት ወይም አስተዳደራዊ የዳኝነት አካላት ዘንድ በመውሰድ የደንበኛውን ጉዳይ በትጋት መከታተል፣ አፋጣኝና ፍትሃዊ ውሳኔ እንዲያገኝም ሙያዊ ጥንቃቄ ብርቱ ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥም ጉዳዩ የደረሰበትን ደረጃ በየጊዜው ለደንበኛው የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
ጠበቆች ሁሌም ቢሆን የደንበኞቻቸው ጥቅም ለማስጠበቅ ተገቢውን ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ለደንበኞቻቸው ጥቅም መከበርም በፍፁም ታማኝነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል፡፡
K) #በዚህ ረገድ በጠበቃውና በደንበኛው፣ ወይም በጠበቃው ዘመዶችና በደንበኛው፣ወይም ጠበቃው በወከላቸው የተለያዩ ደንበኞች መካከል የጥቅም ግጭት እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም በጥብቅና አገልግሎቱ ምክንያት ያወቃቸውን የደንበኛውን የግል ወይም የስራ ሚስጥሮችን መጠበቅ አለበት፡፡ ደንበኛው ሳይፈቅድለት በሙያው ምክንያት እጁ የገቡትን ማናቸውንም የደንበኛውን ሚስጥሮች ለሌላ አካል አሳልፎ ሊሰጥ አይችልም፡፡ ራሱም ቢሆን በህግ በተፈቀዱለት ጥቂት ሁኔታዎች ካልሆነ በቀር ሊጠቀምበት አይችልም፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ጠበቆች ለሌሎች ሶስተኛ ወገኖችም ቅን የመሆን ግዴታ አለባቸው፡፡ በተለይም ሌሎች ተከራካሪዎችን ለማጉላላት በማሰብ አከራካሪ የሆነ ጭብጥ ወይም በሌላኛው ተከራካሪ ላይ ኃላፊነትን ሊያስከትል የሚችል ውጤት የሌለ መሆኑ በግልፅ አኳኋን የሚታይበት ሁኔታ ቅንነትን በማጣት ተገቢ ያልሆነ ክርክር በተቃራኒ ወገኖች ላይ መጀመር የለበትም፡፡
L) #ከዚህ አንፃር በተለይም ከዚህ በታች ከተገለፁት ድርጊቶች መቆጠብ አለበት፡፡ እነዚህም፡-
ተቃራኒ ወገን ማስረጃ እንዳያገኝ ማንኛውንም እንቅፋት መፍጠር ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር ወይም መረዳት፣
ማስረጃን ማሳሳት ወይም ሌሎች ሰዎች ይህን መሰል አድራጎት እንዲፈፅሙ መሞከር መርዳት፣
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌለው ወይም በማስረጀ ሊደገፍ የማይችል ነገር ማቅረብ
በምስክርነት ካልቀረበ በቀር በግል የሚያውቀውን የጭብጥ ነገሮች መሰንዘር ወይም የጉዳዩን ፍትሃዊነት የአንድን ምስክር ተዓሚነት፣ የተከሳሽን ጥፋተኛ ወይም ተጠያቂ መሆንና አለመሆን አስመልክቶ የግል አስተያየቱን መስጠት
ደንበኛው ወይም ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ የማይገደዱ ሰዎችን በተመለከተ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ማንኛውንም ሰው ለተቃራኒ ወገን የምስክርነት ቃሉን ወይም ሌላ አግባብነት ያለው ማስረጃ እንዳይሰጥ መገፋፋት ናቸው፡፡
በመጨረሻም ጠበቆችም ፍትሃዊ ዳኝነት እንዲጎለብት እንዲሁም የደንበኞቻቸው መብትና ጥቅም እንዲጠበቅ የማድረግ ድርብ ኃላፊነት ሲኖርባቸው እነዚህን ኃላፊነቶች በተጣጣመ መልኩ ነው ማከናወን ያለባቸው፡፡ ከዚህ አኳያ ለሰብአዊ መብቶችና መሰረታዊ ነፃነቶች መከበር በትጋት መቆምና መስራት ይኖርባቸዋል፡፡
M) #በዚህ ረገድ የደንበኛቸውን ጥቅም ማስጠበቅና ለፍትህ መከበርም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ መካከል የሚታየውን ክፍተት ለማጣጣመና ሚዛናዊ ለማድረግ መጣር አለባቸው፡፡ ጠበቆች ሙያቸው የግለሰቦች መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች እንደከበሩና እንዲጐለብቱ የማድረግ ልዩ ኃላፊነት ወይም ግዴታ እንደጣለባቸው በመገንዘብ ይህንን ከፍተኛ የሙያ ግዴታ ለመወጣት ከፍተኛ ስነምግባር መላበስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለፍትህ ሥርዓቱ መጐልበትና ለሰብዓዊ መብቶች መከበርም ዘወትር የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት መሥራት እንደሚገባቸውና በዚህ ሂደት ውስጥም ለሙያቸው ስነምግባር መገዛት እንደሚጠበቅባቸው ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/