አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ነሀሴ 2014

. ጡረታ

i. የግል ድርጅት ሰራተኞች ጡረታ ስራ አፈፃፀም መመሪያ ቁ 1_2014


ii.በፕሮቪደንት ፈንድ ወይም በሌላ ስያሜ የሚጠራ ዐቅድ ተጠቃሚ የነበሩ ሰራተኞች በግል ድርጅት ሰራተኞች ጡረታ ዐቅድ ስለሚሸፈኑበት ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁ 2 _ 2014

መመሪያው ወደ ግል ድርጅት ሰራተኞች ጡረታ ዐቅድ የሚደረገውን ሽግግር ከመስከረም 2015 ጀምሮ ግዴታ ለማድረግ ወጥኗል

ለ. NBE External Loan & Suppliers Credit

Issued on September 7 2022 , directive 82 , repealed & replace directive 76 ,2021

Via Tax Solutions Hima Xpress
የማስረጃ ዓይነቶች እና ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸው ፍሬ ነገሮች

መግቢያ

የአንድን ፍሬ-ነገር መኖር ወይም አለመኖር ማረጋገጥ የሚቻለው ማስረጃ በማቅረብ ነው፡፡ ማስረጃ በሰው ምስክሮች፣ በዘገባ፣ በሰነድ፣ ተጨባጭነት ባላቸዉ ሊታዩና ሊዳሰሱ በሚችሉ ነገሮች እና በኤግዚቢት መልክ ሊቀርብ ይቻላል፡፡ አቀራረቡም በሕግ በተደነገገው መሰረት ነው፡፡ በክርክር ሂደት ማስረጃ የማያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ይህ ከፍሬ ነገሩ የተለየ ባህሪ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸዉ ሁኔታዎች ስላሉ ነዉ፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ ስለ ማስረጃ ዓይነቶችና ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸው ጉዳዮች እንመለከታለን፡፡

1. የማስረጃ ዓይነቶች

ማስረጃ የአንድን ፍሬ ነገር መኖር ወይም አለመኖር ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል ከሚቻልባቸው ዘዴዎች እና ማስረዳት ከሚፈለገው ፍሬ ነገር ወይም መደምደሚያ ጋር ማስረጃው የሚኖረውን ግንኙነትን መሠረት በማድረግ በተለያዩ መንገዶች ከፋፍሎ ማየት ይቻላል፡፡

ፍሬ ነገርን ለማስረዳት ከምንጠቀምበት ዘዴ አንጻር፤

ሀ. የሰው ማስረጃ
ሰዎች በአካል ፍርድ ቤት ቀርበዉ ለችሎት መረጃ የሚሰጡበት መንገድ ሲሆን ፍሬ ነገሩን ለፍርድ ቤቱ የሚገልፁት በንግግር ወይም በምልክት ነው፡፡ ይህም የምስክርነት ቃል ይባላል፡፡ የሰው ማስረጃዎች ቀጥተኛ ምስክር፣ የአከባቢ ምስክርና የባለሞያ ምስክር ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

ለ. የሰነድ ማስረጃ
ይህ የማስረጃ ዓይነት በላዩ ላይ የተፃፈበት፣ የተሳለበት ወይም ማናቸዉም ዓይነት ምልክት የተደረገበት ሲሆን ለምሳሌ ውሎች፣ ቼኮች፣ ለፖሊስ ወይም ለፍርድ ቤት የተሰጠ የዕምነት ቃል የተመዘገበበት፣ በጽሁፍ የተገለፀ የላብራቶሪ ወይም የህክምና ምርመራ ውጤት የሰነድ ማስረጃዎች ናቸው፡፡

ሐ. ገላጭ ማስረጃ
ይህ የማስረጃ ዓይነት ፍርድ ቤት እንዲያየውና ግንዘቤ እንዲወስድበት የሚቀርብ ማስረጃ ነው፡፡ ለምሳሌ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረት ወይም ወንጀል ለመፈፀም አገልግሎት ላይ የዋለ መሣሪያ በማስረጃነት ሲቀርብ ገላጭ ማስረጃ ይባላል፡፡

 ማስረዳት ከተፈለገው ፍሬ ነገር አንጻር፤

ቀጥተኛ የሆነ ማስረጃ

ማስረጃ ቀጥተኛ ነዉ የሚባለው አንድን በጭብጥነት የተያዘ ፍሬ ነገር ወይም የተወሰደን መደምደሚያ ትክክለኛነት በቀጥታ ለማረጋገጥ ወይም ለማስተባበል የሚቀርብ ሲሆን ነዉ፡፡ ከዚህ አንፃር ምስክር ቀርቦ በጭብጥ የተያዘው ፍሬነገር መኖሩን ወይም አለመኖሩን ራሱ በስሜት ህዋሳቱ አማካኝነት በማየት፣ በማሽተት፣ በመቅመስ፣ በመስማት ወይም በመዳሰስ ያወቀ መሆኑን የሚመሰክር ሲሆን ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡ በሰነድ ማስረጃ በኩልም በማስረጃነት የቀረበው ሰነድ በጭብጥ የተያዘዉ ፍሬ ነገር መኖርን ወይም የተደረሰበት መደምደሚያ ትክክለኛ መሆኑን ሰነዱ ራሱ በቀጥታ ያረጋግጣል ወይም ያስተባብላል በሚል የቀረበ ከሆነ ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡ ለምሳሌ በቂ ስንቅ ሳይኖረው ቼክ ፈርሞ ሰጥቷል በሚል ገንዘብ እንዲከፍል በተከሳሽ ላይ ለቀረበ ክስ ከሳሽ ቼኩን በማስረጃነት ያቀረበ ቢሆን ተከሳሹ ስለመፈረም አለመፈረሙ እና ስለ ገንዘቡ ልክ ቼኩ በቀጥታ የሚናገር ስለሆነ ቀጥተኛ ማስረጃ ይባላል፡፡

 ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ

ማስረጃ ቀጥተኛ ያልሆነ ነዉ የሚባለው ከሁለት ሁኔታዎች አንፃር ነዉ፡- አንደኛዉ ማስረጃ ያስረዳል የተባለዉን ፍሬ ነገር ምንጭ ማስረጃዉ ራሱ በቀጥታ ያወቀዉ ሳይሆን ከሌላ ያገኘዉ ወይም የተረዳዉ ሲሆን ነዉ፡፡ ምስክር ሌላ ሰዉ የገለፀለት መሆኑን ጠቅሶ የሚመሰክር ሲሆን ቀጥተኛ ሳይሆን የስሚ ስሚ ማስረጃ (Hearsay Evidence) ይባላል፡፡ የስሚስሚ ማስረጃን ቀጥተኛ ያልሆነ የሚያሰኘዉ ማስረጃዉ ፍሬ ነገሩን የሚገልፀዉ ራሱ በቀጥታ እንዳወቀ ሳይሆን ከሌላ ሰዉ የሰማዉ ወይም ከሰነድ ያነበበዉ በመሆኑ ነዉ፡፡ በሰነድ ማስረጃም በኩል የስሚ ስሚ የሚያሰኘዉ ማስረጃ ሆኖ የቀረበዉ ሰነድ ላይ የተገለፀዉ ፍሬ ነገር አዉቃለሁ በሚል በሌላ ሰዉ የተዘጋጀ ሲሆን ነዉ፡፡

2ኛ ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ

ሁለተኛዉ ቀጥተኛ ያልሆነ ማስረጃ ነዉ የሚባልበት ሁኔታ የሚያጋጥመዉ አካባቢያዊ ማስረጃ (Circumstantial Evidence) የቀረበ እንደሆነ ነዉ፡፡ አካባቢያዊ ማስረጃ በጭብጥ ስለተያዘዉ ፍሬ ነገር መኖር አለመኖር በቀጥታ አይነግረንም፡፡ ይልቁንም የተወሰኑ ፍሬ ነገሮችን መኖር ወይም አለመኖር በማረጋገጥ ከዚህ ተነስተን በጭብጥ የተያዘዉን ፍሬ ነገር በተመለከተ አንድ ዓይነት መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ የሚያደርግ ነዉ፡፡
የማስረጃዉ ቀጥተኛ ወይም አካባቢያዊ መሆን አለመሆኑን መለየት በማስረጃ ምዘና ጊዜ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለዉ፡፡

1. ማስረጃ ስለማያስፈልጋቸዉ ፍሬ ነገሮች

ከፍሬ ነገሮቹ የተለየ ባህሪ ወይም የሚያከራክር ነገር ባለመኖሩ ምክንያት ማስረጃ ማቅረብ አስፈላጊ የማይሆንባቸዉ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነሱም፡-
ሀ. ፍርድ ቤት ግንዛቤ ሊወስድባቸዉ የሚችሉ ወይም የሚገቡ ፍሬ ነገሮች፣ ለምሳሌ በአዋጅ ቁጥር 3/1987 መሠረት በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ የወጡ ነገሮችን ፍርድ ቤቶች ሊቀበሏቸዉ እንደሚገባ ተደንግጓል፡፡ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ የተገለፀ ፍሬ ነገር ለማረጋገጥ ሌላ ማስረጃ መቀበል አያስፈልግም፡፡ ጋዜጣዉን በመመልከት ብቻ ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል፡፡
ለ. በፍርድ ቤት በሚደረግ የክርክር ሂደት በተከራካሪ ወገን የታመኑ ፍሬ ነገሮች፣
ሐ. ጠቅላላ እዉነታዎች (Universal Truth)፣
መ. የሕግ ግምቶች (Presumptions) ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ በጋብቻ ውስጥ የተፀነሰ (የተወለደ) ልጅ አባቱ ባልየው እንደሆነ ህጉ ግምት ይወስዳል፡፡

በአጠቃላይ ግራ ቀኝ ተከራካሪ ወገኖች ያስረዱልናል የሚሏቸዉን ማስረጃዎች ወይም ማስረጃ ባይቀርብባቸዉም በሕግ መሠረት የሚወሰኑትን ለይቶ ለማቅረብ የማስረጃ ዓይነቶችን እና ማሰረጃ የማያስፈለጋቸዉን ፍሬነገሮች ማወቁ ተገቢ ነዉ፡፡
በንቃተ ህግ ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
https://t.me/lawsocieties
ባል ሚስቱን የዘረፈበት ልዩ ክስተት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ።

መስከረም 11/2015 ምሽት 3 ሰአት አካባቢ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 11 አስተዳደር የቀጠና 1 ብሎክ 4 የበጎ ፈቃድ እና የሕዝባዊ ሰራዊት ስምሪት ተሰጥቶአቸው አካባቢያቸውን በመጠበቅ ላይ እያሉ አንድ ግለሰብ ከተበዳይ እጅ ሞባይል መንትፎ ሲሮጥ አካባቢው በመጠበቅ ላይ ባለው ህዝባዊ ሰራዊት በቁጥጥር ስር በማዋል ለፖሊስ ያስረክበዋል።

እጅግ የሚያስገርመው ነገር ሞባይል የዘረፈው ባል ሲሆን የተዘረፈችው ሚስት መሆኑ ነው። ቀኝ እጅ ግራ እጁን መነተፈው ማለት ይሄ ነው!!

ለማንኛውም ሀገርም እንዲህ ነው የምትዘረፍ


Via ሶሊያና
https://t.me/lawsocieties
የተሽከርካሪ ቀረጥና ታክስ አወሳሰን

ተሽከርካሪ ወደ ሀገር ሲገባቀረጥና ታክስ የሚታሰበው የተሸከርካሪዉን ሲሲ መሰረት በማድረግ  CIF (የተገዛበት ዋጋ + የትራንስፖርት ወጪ + የኢንሹራንስ ወጪ እና ሌሎች ወጪዎችን ጨምሮ) በሚገኘዉ ጠቅላላ ወጪ ነው፡፡ ተሽከርካሪው ያገለገለ ከሆነ ከተመረተበት አንድ ዓመት ጊዜ ጀምሮ ከFOB ዋጋዉ ላይ በየዓመቱ 10% በመቀነስ በጠቅላላዉ እስከ 3 አመት ወይም 30% ድረስ የእርጅና ቅናሽ ካለዉ በማስላት የጉምሩክና ሌሎች ቀረጦች ጠቅላላ ምጣኔ በማባዛት ቀረጥና ታክሱን ማወቅ ይቻላል፡፡

የተሽከርካሪው የፈረስ ጉልበት ማለትም ሲሲው 1300 ከሆነ 125%ሲሆን 1301ሲሲ እስከ 2500 ሲሲ ደግሞ ከ176.24% እስከ 244.55% ባሉትየጉምሩክና ሌሎች ቀረጦች ጠቅላላ ምጣኔ ይሰላል፡፡ለሰው ማጓጓዣ የሚያገለግሉ ሌሎች ተሸከርካሪዎች ሲሆን ደግሞ በሌላ ስፍራ ያልተጠቀሰ ከሆነ የጉምሩክና ሌሎች ቀረጦች ጠቅላላ ምጣኔ 125.00075% ሲሆን ሹፌሩን ጨምሮ አስር ወይም ከዛ በላይ ሰዎችን ለማጓጓዝ የሚያገለግሉ ተሸከርካሪዎች ከ15 ተጓዦች ያነሰ መቀመጫ ያላቸው ተሸከርካሪዎች 58.25% እንዲሁም 15 እና ከዚያ በላይ ሰው የሚይዝ መቀመጫ ያላቸው የጉምሩክና ሌሎች ቀረጦች ጠቅላላ ምጣኔው 29.50% ነው፡፡

የተሽከርካሪው የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ (duty paying value) በተሽከርካሪው ጠቅላላ ቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ምጣኔ ተባዝቶ የብዜቱ ውጤት ተከፋዩ ቀረጥና ታክስ ይሆናል፡፡ የተሸከርካሪ ቀረጥና ታክስ ለመወሰን አምስት የሰሌት ደረጃዎችን(ማለትም የጉምሩክ ቀረጥ፣ ኤክሳይስ ታክስ፣ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ፣ ሱር ታክስ እና ዊዝሆልዲንግ ታክስ) እንከተላለን፡፡ የቀረጥና ታክስ መጠኑን እንዴት እንደሚታሰብ በምሳሌ እንመልከት፡፡

የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋው ብር 70000፣ የሲሊንደር አቅሙ 1280 የሆነ አዲስ አውቶሞቢል ሲገባ:-

በቅድሚያ የጉምሩክ ቀረጥ የሚሰላ ሲሆን ማስከፈያ ዋጋው በጉምሩክ ቀረጥ ምጣኔ በማባዛት የሚሰላ ነው፡፡ በዚህ መሰረት ተከፋዩ የጉምሩክ ቀረጥ 70,000 X 35% =24,500 ይሆናል፡፡

ቀጥሎ ኤክሳይስ ታክስ የሚሰላ ሲሆን ስሌቱ የአውቶሞቢሉ የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ እና ተከፋዩ የጉምሩክ ቀረጥ በመደመር በኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ ማባዛት ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት ተከፋዩ ኤክሳይስ ታክስ መጠን (70,000 + 24,500) 30%=28,350 ይሆናል፡፡

በሶስተኛ ደረጃ የሚሰላው ተከፋይ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ሲሆን በዚህ ስሌት የአውቶሞቢሉን የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ፣ ተከፋይ የጉምሩክ ቀረጥ እና ኤክሳይዝ ታክስን በመደመር በተጨማሪ ዕሴት ታክስ መጣኔ ይባዛል፡፡ በዚህ መሰረት የሚከፈለው ተጨማሪ ዕሴት ታክስ (70,000 + 24,500 + 28,350) 15% = 18,427.5 ብር ይሆናል፡፡

በአራተኛ ደረጃ የሚሰላው ሱር ታክስ ሲሆን ስሌቱ የአውቶሞቢሉን የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ፣ ተከፋይ የጉምሩክ ቀረጥ፣ ኤክሳይዝ ታክስ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ በመደመር በሱር ታክስ መጣኔ ማባዛት ነው፡፡ በዚህ መሰረት የሚከፈለው ሱር ታክስ (70,000 + 24,500 + 28,350 +18,427.5)10%= 14,127.75 ብር ይሆናል፡፡

በአምስተኛ ደረጃ ተከፋዩን ዊዝሆልዲንግ ታክስ ነው፡፡ ይህ ታክስ የሚሰላው የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋን በዊዝሆልዲንግ ታክስ መጣኔ በማባዛት ነው፡፡ በዚህ መሰረት ተከፋዩ የዊዝሆልዲንግ ታክስ 70,000 X 3%= 2,100 ብር ይሆናል፡፡

በመጨረሻም የስሌት ደረጃ ሁሉም ተከፋይ ቀረጥና ታክስ የሚደመሩ ሲሆን በዚህ መሰረት መንግስት ከዚህ አውቶሞቢል የሚሰበስበው ቀረጥና ታክስ ስሌት

24,500 + 28,350 + 18,427.5 + 14,127.75 + 2,100= 87,505.25 ብር ይሆናል፡፡                                                          #ጉምሩክ ኮሚሽን
መንግሥት ከሠራተኞች ደመወዝ ላይ የሥራ ግብር ቅናሽ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ኢሠማኮ መንግሥት ከሠራተኞች ደመወዝ ላይ የሥራ ግብር ቅናሽ እንዲያደርግ ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤትና ለገንዘብ ሚንስቴር ጥያቄ ማቅረቡን ሪፖርተር አስነብቧል። ጥያቄው ለመንግሥት የቀረበው ሠራተኞች ያለባቸውን ከባድ የኑሮ ውድነት ጫና ግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ የገለጡት የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ፣ ከሠራተኛ ደመወዝ ላይ የሥራ ግብር ምጣኔ መቀነስ በሌሎች አገራት የተለመደ አሠራር መሆኑን ጠቅሰዋል። ግብር የተጣለበት ዝቅተኛው ወርሃዊ የሠራተኛ ደመወዝ 600 ብር መሆኑ ቀርቶ ከፍ ባለ ደመወዝ ላይ እንዲሆን እና ከ10 ሺህ 900 ብር ወርሃዊ ደመወዝ ላይ የሚጣለው 35 በመቶ የግብር ምጣኔም እንዲቀንስ ኢሠመኮ ጠይቋል።
#Black future consultance SC#

▪️🚩Required No - 35
▪️1 - Health officer
▪️2 - Law Expert 👈👈👈👈👈
▪️3 - Nurse
▪️4 - Sales Expert
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://bit.ly/3UERkzK

▪️Deadline: September 30/2022
በአለም አቀፉ ወንጀል ፍርድ ቤት የተከሰሰው ኬንያዊ ጠበቃ ሞቶ ተገኘ

በአለም አቀፉ ወንጀል ፍርድ ቤት (አይሲሲ) በምስክሮች ጣልቃ ገብነት ክስ ቀርቦበት የነበረው ኬንያዊው ጠበቃ ፖል ጊቼሩ ሞቶ ተገኘ።

ፖሊስ እንዳስታወቀው ጠበቃው ፖል ጊቼሩ ሰኞ ምሽት በመዲናዋ ናይሮቢ በሚገኘው ቤቱ ሞቶ መገኘቱን አረጋግጧል።

ጠበቃው በአውሮፓውያኑ 2007 ምርጫ ማግስት ከተፈጠረው ሁከት ጋር በተያያዘ ለምስክሮች ጉቦ በመስጠት ነው ክስ የቀረበበት።

ምስክሮቹ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በአይሲሲ ተከሰው በነበረበት ወቅት ምስክርነት የሚሰጡ ግለሰቦች ምስክርነት የሚሰጡ ግለሰቦች እንደነበሩም ተገልጿል።

በዚህ ሁከት ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ተገድለዋል።ጠበቃው የቀረበበትን ክስ አስተባብሏል።

ጠበቃው የአይሲሲ የእስር ማዘዣ ካወጣበት ከአምስት ዓመት በኋላም በአውሮፓውያኑ 2020 ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል።

አቃብያነ ህግ እንደሚሉት ጠበቃው ፈጸመው በተባለው ተግባር ምክንያት ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በፍርድ ቤቱ የቀረቡባባቸውን ክሶች ውሃ እንዳይቋጥር አድርጎታል ብለዋል።

https://t.me/lawsocieties

Via BBC Amharic
Vacancy Announcement.png
77 KB
የሥራ ማስታወቂያ
ድርጅት፡- ብላክ ፊውቸር አ.ማ
የሥራ መደብ፡- የሕግ ባለሙያ
ተፈላጊ የሥራ ልምድ፡- ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት
ብዛት፡- በድምሩ 10
የሥራ ቦታ፡- አዲስ አበባ
የምዝገባ ጊዜ፡- እስከ መስከረም 20 ቀን 2015 ዓ.ም
የጤና ባለሙያ ነኝ
የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አለኝ
ነገር ግን ሰርተፊኬቱን ከኔ እውቅና እና ፍቃድ ውጪ አንድ ድርጅት የኔን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፍኬት ተጠቅሞ ፍቃድ አውጥቶበት እየሰራበት መሆኑን ደረስኩበት
ድርጅቱ ምን ሲሰራበት እንደነበር አላወቅኩም
ከማንም ጋርም ውል የለኝም
ምን ማድረግ እችላለው?

እኔ የድርጅቱ ሰራተኛ ሳልሆን, ምንም አይነት ውል ሳልዋዋል ሰራተኛቸው እንደሆንኩ አድርጎ ነው እየተተቀመበት ያለው

ድርጅቱ በወንጀል ድርጊት ውስጥ ተሳትፎስ ከነበር የኔ ተጠያቂነት ምን ድረስ ነው?
አቶ_አህመድ_አብዱራህማን_ከ_ኢልይስ_ዲተርጀንት_ኢንዱስትሪ_ኩባንያ_የሰ_መ_ቁ_193292.pdf
805.2 KB
ሰበር ችሎቱ የውጭ ሃገር ሰዎች (ኩባንያ) የንግድ ምልክት ጥበቃ ላይ የህግ ትርጉም ሰጠ

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎ በአመልካች አቶ አህመድ አብዱራህማን እና በተጠሪ ኢልይስ ዲተርጀንት ኢንዱስትሪ ኩባንያ መካከል በሰ/መ/ቁ/ 193292 የንግድ ምልክትን አስመልቶ የቀረበለትን አቤቱታ መርምሮ ሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ/ም በዋለው ችሎት የህግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡

ፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
Vacancy Announcement.png
491.2 KB
Job openings at Selale University

Position 1: Lecturer of Laws
Number: 2


Position 2: Assistant Professor of Laws or Human Rights, or above
Number: 2

Deadline: September 25, 2015 E.C