አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የአማራ ክልልአቃቤ ህግ ማህበር ጠቅላይ ሚኒስትሩለህዝብ እንደራሴዎች 2ኛ ደረጃ ሌባ ዐቃቤ ህግ ነው ብለው የተናገሩትን ብያኔያዊ መግለጫ ማስተካከያ የማይሰጡበት ከሆነ ተገቢ ያልሆነውን ብያኔ ተከትሎ የሚመጣውን የአስፈፃሚ አካላት ጫና ማህበሩ እንደሚታገል ተገለፀ!
-----
@የአማራ ክልል ዓቃብያነ ሕግ ማሕበር
የነዳጅ_ውጤቶች_የሥርጭት፣_የርክክብና_የሽያጭ_አፈፃፀም_መመሪያ_904_2014.pdf
324.5 KB
⛽️ የነዳጅ ውጤቶች የሥርጭት፣ የርክክብና የሽያጭ አፈፃፀም መመሪያ ቁ. 904/2014

የፌዴራል መንግሥት አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁ. 1263/2014 አንቀጽ 19(4) መሠረት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡ ይህ መመሪያ ከወደብ እስከ ነዳኝ ማደያዎች ድረስ ባለው የሥርጭት፣ የርክክብና የሽያጭ ሂደት ላይ ተሳታፊ በሆኑና የቁጥጥር ሚና ባላቸው አካላት ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ ከሰኔ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡
መልካም የእረፍት ቀን ለሁሉም የአለ_ህግ ቤተሰቦች🙏

stay updated about all legal issues🔴

Share, invite and add...❗️👇👇👇

https://t.me/lawsocieties
#Ruwanda!

#የሩዋንዳው ፕሬዘዳንት ፖል ካጋሜ ከዚህ በፊት ብዙ መስኪዶችን አዘግተው ነበር አሁን ደግሞ ከ6000 በላይ የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያኖች እንዲዘጉ ማድረጋቸው ተሰማ።
#ፕሬዝዳንቱ ቸርች ለመክፈት ማንኛውም የቤተክርስቲያኑ መሪ የስነመለኮት ዲግሪ ሊኖረው ይገባል ያሉ ሲሆን
#እኔ ከዚህ በኋላ ቤተክርስቲያን የንግድ ተቋም ሲሆን ቆሜ አላይም ብለዋል።

#ሩዋንዳን በምታክል ትንሽ ሀገር ላይ በቂ ሆስፒታልና
ት/ቤቶች ሳይኖሩ ሀሰተኛ ቤተክርስትያናትና ፓስተሮች በዝተዋል ያሉት ፖል ካጋሜ ይህንን የሚቆጣጠርም አዲስ ሕግ እንዲወጣ አድርገዋል ተብሏል።
@ ምንጭ: 35 News GH

https://t.me/lawsocieties
የ 37 ዩኒቨርሲቲ የ Exit Exam የፈተና ጣቢያቸው እና የተፈታኞች ስም ዝርዝር
የሁሉም የህግ ተቄማት የ Exit Exam ምዝገባ እና የፈተና ጣቢያ ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ በዚህ ሊንክ ስምዎን መኖሩን ያረጋግጡ https://t.me/AleHig
2014 law exit exam center and registration number
37 ዩኒቨርሲቲ የ Exit Exam የፈተና ጣቢያቸው እና የተፈታኞች ስም ዝርዝር፣
የሁሉም የህግ ተቋማት የ Exit Exam ምዝገባ እና የፈተና ጣቢያ ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ፣


ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በተመዘገቡበት ዩኒቨርሲቲ በመግባት ስምዎን መኖሩን ያረጋግጡ።
2014 law exit exam center and registration number


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31167

አልፋ ዩኒቨርስቲ https://t.me/AleHig/31170

አምቦ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31172

አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31175

አርሲ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31177

አሶሳ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31179

ባህርዳር ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31181

ቡሌሆራ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31183

ደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ https://t.me/AleHig/31185

ደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31187

ደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31189

ደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31191

ዲላ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31193

ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31195

ኢትዮጲስ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31197

ጋምቤላ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31199

ጎንደር ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31200

ሀራማያ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31202

ጅጅጋ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31204

ጅማ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31206

ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31389

ማዳወላቡ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31208

መቱ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31210

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31212

MoE Tigray ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31214

ኒው ጀነሬሽን ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31216

ኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31218

ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31221

ሰመራ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31224

ሴንትሜሪ ዩኒቨርስቲ https://t.me/AleHig/31226

ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31230

ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31232

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ https://t.me/AleHig/31234

ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31236

ወለጋ ዩኒቨርስቲ https://t.me/AleHig/31238

ወሎ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31240

አፍሪካ ቤዛ ዩኒቨርስቲ
https://t.me/AleHig/31245


https://t.me/lawsocieties
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
Names of books that brought to Exam hall

2021/2022 ACADEMIC YEAR


PART I: PRIVATE LAWS

THIS IS A CLOSED BOOK EXAM EXCEPT PERTINENT ETHIOPIAN LAWS.

Part Ii: public Laws

Laws that can be brought to the exam room are
The UN Charter,
The Vienna Convention on the Law of Treaties,
The FDRE Constitution,
The Criminal Code,
The Income Tax Proclamation,
The VAT Proclamation,
The Environmental Pollution Control Proclamation, And
The EIA Proclamation.

Part III: Procedural Laws

A closed book exam for all materials except clean copies of
the Civil Procedure Code,
the Criminal Procedure Code
the Criminal Code,
the Federal Courts Establishment Proclamation, and
Corruption Crime Proclamations (substantive and procedural)
Which cannot be lent to nor borrowed from other students.

Part IV: Miscellaneous Law Courses

It is a closed book examination.

Via @Lawsocieties Ale_Hig አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties
አንድ የመንግሥት ሠራተኛን በኃላፊ በተፃፈ ደብዳቤ ብቻ ከሥራ ማሰናበት ሕገ መንግሥታዊ ነውን?

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 37(1) መሰረት ማንኛውም ሰው በፍርድ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ለሌላ በሕግ የዳኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት ሕገ መንግሥታዊ መብት ያለው ስለመሆኑ ተደንግጓል። በተጨማሪም በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 42 ስር ለሠራተኞች የተደነገጉ በርካታ መብቶች አሉ። በተለይም ከዚህ የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ አርዕስት መረዳት አንደሚቻለው ሠራተኞች በሕገ መንግሥቱ የተጠበቀላቸው የሥራ ዋስትና መብት ያላቸው መሆኑን መረዳት ይቻላል። በሕገ መንግሥቱ ለሠራተኞች የተጠበቀው የሥራ ዋስትና መብት ከሚከበርበት መንገድ ውስጥ አንዱ ሠራተኞች በሕግ አግባብ ከተቀመጠው ሂደት እና አሠራር ውጪ ከሥራቸው መባረር የሌለባቸው መሆኑ ነው። ሠራተኞች በሥራ ቦታ ለሚያጠፉት ጥፋት በሕግ አግባብ በተቀመጠው የዲስፕሊን ሂደት የመዳኘት መብት አላቸው። ይህ መብት ከላይ በተጠቀሰው የሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 37(1) መሰረት የሚተገበር ነው።
በዚህ ድንጋጌ መሰረት በተለይም የመንግሥት ሠራተኞች በዲስፕሊን ጥፋት ከሥራ የሚሰናበቱት ጉዳያቸውን ለማየት እና ፍርድ ወይም ውሳኔ ለመስጠት በሕግ ስልጣን ባለው አካል ብቻ ነው። በሕግ በግልፅ ከተደነገገው አግባብ ውጪ አንድ የመንግሥት ሠራተኛ ተገቢውን ክርክር ሳያደርግ፤ ያለውን ማስረጃ በማቅረብ እራሱን ሳይከላከል አንዲሁም ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ላለው አካል ይግባኝ አቅርቦ ሳይከራካር ከሥራ ሊሰናበት አይችልም።.......ይቀጥላል 👇👇👇👇👇
የቀጠለ.......👆👆👆👆👆👆👆👆👆
አንድ ሠራተኛ ጥፋት ሲያጠፋ ተገቢው ክስ ቀርቦበት በቀረበበት ክስ ላይ ሠራተኛው መልስ ሰጥቶ የመከራከር፣ ማስረጃ የማቅረብ እና የመከላከል መብቱ ሊከበርለት ይገባል።
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 9(1) መሰረት ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሠራር፣ አንዲሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ሕገ መንግሥቱን የሚቃረን ሆኖ ሲገኝ ተፈፃሚነት አንዳይኖረው በሕገ መንግሥት ትርጉም ስርዓት ውድቅ ይደረጋል።
የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 84 እና 9(1) ጣምራ ንባብ መሰረት ማንቸውንም ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮችን የማጣራት ስልጣን አለው። በሚያደርገው ማጣራትም ማናቸውንም ሕግ፣ ልማዳዊ አሠራር፣ የባለስልጣን ወይም የመንግሥት አካል ውሳኔ የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌ የሚጥስ ሆኖ ከተገኘ ተፈፃሚነት እንዳይኖረው የውሳኔ ሃሳቡን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያቀርባል። ምክር ቤቱም የጉባዔውን የውሳኔ ሃሳብ ተቀብሎ ካፀደቀው ውሳኔው የመጨረሻ ይሆናል።
በዚሁ መሰረት ቀጥለን የምናየው ጉዳይ አስፈፃሚ የመንግሥት አካል የሆነው የአዲስ አበባ ከተማ የክ/ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት የአንድን መምህር የዲስፕሊን ጉዳይ አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ ኢ-ሕገ መንግሥታዊነትን ነው።
አመልካች በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኝ የአንድ ትምህርት ቤት መምህር ናቸው። እኝህ በአዲስ አበባ ከተማ በመምህርነት የሚያገለግሉ አመልካች በትምህርት ቤቱ ያሉ መምህራንን በማስተባበር የሥራ ማቆም አድማ አንዲደረግ አድርገዋል እንዲሁም የመማር ማስተማሩን ሥራ አስተጓጉለዋል በሚል በክ/ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ ደብዳቤ ከሥራ እንዲሰናበቱ ተደርጓል። አመልካች ይህን የክ/ከተማውን ፅ/ቤት ውሳኔ ለማሻር የይግባኝ ቅሬታ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት ሬጅስትራር ቢያቀርቡም ፍርድ ቤቱ አቤቱታቸውን አልተቀበላቸውም። ቀጥሎም አመልካች አቤቱታቸውን ለሌሎች የተለያዩ የመንግሥት አካላት ቢያቀርቡም የሚቀበላቸው እና መፍትሄ የሚሰጣቸው አካል አላገኙም።
በመጨረሻም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግሥት ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮችን ለማጣራት ስልጣን ለተሰጠው የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ በአስተዳደር አካሉ ውሳኔ ላይ የሕገ መንግሥት ትርጉም አንዲሰጣቸው አመልክተዋል።
ጉባዔውም ጉዳዩን ለማጣራት ያመች ዘንድ አመልካች በወቅቱ ለአዲስ አበባ ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት ሬጅስትራር የይግባኝ ማመልካቻ ማቅረብ አለማቅረባቸውን እና አንድ ጉዳይ በዲስፕሊን ኮሚቴ ሳይታይ በሥራ ኃላፊ ደብዳቤ ብቻ የተሰናበተ ከሆነ ለሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማቅረብ እና መዝገብ ማስከፍት ይችላል ወይ የሚለውን አጣርቷል። ፍርድ ቤቱ በሰጠው ምላሽ በወቅቱ የነበረው ሬጅስትራር የለቀቀ በመሆኑ በጉዳዩ ላይ ምላሽ መስጠት የማይቻል መሆኑን ጠቅሷል። በሌላ በኩል አንድ ጉዳይ በዲስፕሊን ኮሚቴ ሳይታይ በሥራ ኃላፊ በተፃፈ ደብዳቤ ከሥራ ቢሰናበት በዚሁ ደብዳቤ መነሻነት የይግባኝ መዝገብ መክፈት የሚቻል መሆኑን በመግለፅ መልስ ሰጥቷል።
አመልካች የስንብት ደብዳቤ በተሰጣቸው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የይግባኝ ማመልከቻ ለአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት አቅርበው የነበረ መሆኑን ለጉባዔው ካቀረቡት ማስረጃ መረዳት ይቻላል። በመሆኑም የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት የአመልካችን ጉዳይ ተቀብሎ ማስተናገድ ሲገባው “አንቀበልም’’ ማለቱ አመልካች በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 37(1) የተረጋገጠላቸውን ፍትህ የማግኘት መብታቸው መጣሱን ያረጋግጣል።
የአመልካች ዓይነት የይግባኝ አቤቱታን የመቀበል፣ የመመርመር እና ፍርድ ወይም ውሳኔ የመስጠት ሕጋዊ ግዴታ የተጣለው በአዲስ አበባ ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት ላይ ነው። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ በሕግ በተሰጠው የዳኝነት ስልጣን መሰረት የአመልካችን አቤቱታ በመቀበል ተገቢውን ማጣራት እና ክርክር በማድረግ ውሳኔ ወይም ፍርድ መስጠት ነበረበት። የአዲስ አበባ ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት ይህን ኃላፊነቱን ባለመወጣት እና የአመልካችን አቤቱታ ተቀብለው ባለማስተናገዳቸው አመልካች ማግኘት የነበረባቸውን ፍትህ ሊያገኙ አልቻሉም።
ጉባዔው ጉዳዩን ካጣራ በኋላ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት የአመልካችን ጉዳይ ተቀብሎ ማስተናገድ ሲገባው አንቀበልም ማለቱ በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 37(1) ስር የተደነገገውን ማንኛውም ሰው በፍርድ ሊወሰን የሚገባውን ጉዳይ ለፍርድ ቤት ወይም ለሌላ በሕግ የዳኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል የማቅረብና ውሳኔ ወይም ፍርድ የማግኘት መብቱን የሚጥስ ነው በማለት፣ አመልካች በፅ/ቤቱ ኃላፊ ደብዳቤ ብቻ የተላለፈባቸው የሥራ ስንብት ውሳኔ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው በማለት የሕገ መንግሥት ትርጉም እንደሚያስፈልገው የውሳኔ ሃሳቡን አሳልፏል።
ስለሆነም አመልካች ጉዳያቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ፍርድ ቤት የማቅረብ መብት አላቸው በማለት ጉባዔው የውሳኔ ሃሳቡን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተላልፏል። ምክር ቤቱም የአጣሪ ጉባዔውን የውሳኔ ሃሳብ በመቀበል በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ሰጥቷል።
በያደታ ግዛው
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
#የአላባ ጥቅም ውል

የአላባ መብት ማለት የሚጠቀሙበትን ነገር ከመጠበቅ ግዴታ ጋር ከዚሁ ነገር ላይ በሚገኙት ነገሮች (ፍሬዎች) ወይም መብቶች ለመጠቀምና ለመገልገል የሚሰጥ መብት ነው፡፡

ይህም መብት የሚንቀሳቀሱና በማንቀሳቀሱ ንብረቶች መብቶች ወይም በአንድ ጠቅላላ ንብረት ላይ ሊሆን የሚችል ነው:: በማለት በፍትሐ ብሔር ህግ አንቀጽ 1309 (1) እና (2) ላይ ተቀምጧል፡፡

በመሆኑም ተገልጋዮች የአላባ ጥቅም ውልን ለመዋዋል ወደመስሪያ ቤታችን ሲመጡ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡

. በህግ አግባብ የተዘጋጀ የውል ሰነድ፣

. ተዋዋይ ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ስልጣን ያላቸው መሆኑን ማረጋገጫ ሰነድ፣

. የንብረት ባለቤትነት ማስረጃ፣

. በማንኛውም መልኩ ንብረቱ ከእዳና እገዳ ነጻ መሆኑን ማረጋገጥ፣

የአላባ ውሉ የሚደረገው በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ከሆነ የሁለት ምስክሮቻዉና የታደሰ መታወቂያ፣

. የአላባ ሰጪ እና ተቀባይ የታደሰ መታወቂያ፣

. የአላባ ሰጪው ያገባ ወይም ያላገባ ከሆነ ማስረጃ እና የትዳር አጋር የፈቃድ ስምምነት /ውክልና፣

. የንግድ ማህበር ከሆነ የመመስረቻ ጽሁፍ፣ የንግድ ዋና ምዝገባ እና እንደአስፈላጊነቱ ቃለ-ጉባኤ፡፡
via DARA
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ በግል ስልካቸው ላይ ከተከሳሽ ቤተሰብ በተላከላቸው መልክት ምክንያት እራሳቸውን ከዳኝነት አነሱ።

ዳኛው በፌደራል የዳኝነት አስተዳደር አዋጅ ቁ.1233/2013 መሰረት ነጻና ገለልተኝነታቸውን ለማረጋገጥ ሲሉ ነው ከሚመለከቱት መዝገብ ዳኝነታቸውን በራሳቸው ፍቃድ ያነሱት።

ለፍርድ ከተቀጠረ የሙስና ወንጀል መዝገብ እራሳቸውን ከዳኝነት ያነሱት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የ1ኛ ሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ ናቸው።

የችሎቱ ዳኛ ከሁለት ወር በፊት በሙስና ወንጀል ክስ የቀረበባቸውን የቀድሞ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች 1ኛ ተከሳሽ አዱኛ ነጋሳ ፣ 2ኛ ተከሳሽ አክሊሉ ዘሪሁንን ፣ 3ኛ ረቂቅ ዜናዊ ፣ 4ኛ ተከሳሽ ረቡማ በለጠ እንዲሁም ከዚህ በፊት በዋስ ወጥተው በውጪ ጉዳያቸውን የሚከታተሉት 5 ኛ ተከሳሽ ቶፊቅ ሙላት ፣ 6ኛ ተከሳሽ የከፍተኛው ፍ/ቤት ሬጅስትራር ስሜነህ አለሙና እና 7ኛ ቸከሳሽ የቦሌ
ክ/ከ ወረዳ 6 የኗሪዎች መረጃና ማስረጃ አገልግሎት ባለሙያ ከድር ዱንዲን መዝገብ ሲመለከቱ መቆየታቸው ይታወሳል።

ተከሳሾቹ በህዳር 28 ቀን 2014 ዓ/ም በዓቃቤ ህግ በቀረበባቸው ክስ ላይ የአቶ ዳዊት ገ/እግዛብሔር የሆነ በስራ ግንኙነት ሳይከፈል የቀረ የ276 ሚሊዮን ብር እና 9 ከመቶ ወለድ ክፍያ ብር በጥቅም በመመሳጠር በጥቅምት 10 ቀን በ2009 ዓ/ም ቱፋ ጣፋ በሚባል በሀሰተኛ ስም በተከፈተ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ በሚመለከቱት 11ኛ የአፈጻጻም ችሎት ክርክር ሳይደረግ ያልተገባ ውሳኔ በመስጠት ከ4ኛ ተከሳሽ ረቡማ በለጠ የ3ሚሊዮን ብር ጉቦ እና የ2 ሚሊዮን ብር ቼክ በመቀበል በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ የሚገኝ የዳዊት ገ/እግዛብሔር ሒሳብ የነበረ 276 ሚሊዮን ብር ወደ ቡና ባንክ ገቢ እንዲሆን ያልተገባ ትዛዝ ሰጥተዋል ተብለው በዓቃቤ ህግ በየተሳትፎ ደረጃ ተጠቅሶ በሙስና ክስ መከሰሳቸው ይታወሳል።

ተከሳሾቹ ክሱ ከደረሳቸው በኋላ ክሱን አለመፈጸማቸውን ገልጸው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን ለችሎቱ አስመዝግበዋል።

ከሳሽ ዓቃቤ ህግም የሰው ምስክር ችሎት አቅርቦ በየደረጃው አሰምቷል።

የችሎቱ ዳኞች የተሰማውን የምስክር ቃል ተገልብጦ መርምረው ፍርድ ለመስጠት ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተው ነበር።

ሆኖም ሰብሳቢ ዳኛው የግል ስልካቸው ላይ በሚያውቋቸው የ4ኛ ተከሳሽ ዘመድ ረቡማ ለተባለ ለ4ኛ ተከሳሽ ድጋፍ እንዲያደርጉ መልክት መላኩንና ቤተሰብ ላይ ጫና እንደተደረገባቸው በችሎት ይፋ አድርገዋል።

ዳኞች የዳኝነት ስራቸውን ከማንኛውም ውስጣዊና ውጪያዊ ተፅኖ ነጻ ሆነው በገለልተኝነትና በተጠያቂነት መንፈስ ማከናወን ያለባቸው መሆኑ መደንገጉን ሰብሳቢ ዳኛው ጠቅሰዋል።

በዚህ በፌደራል የዳኞች አስተዳደር አዋጅ ቁ. 1233/2013 ድንጋጌ መሰረት በግል ስልኬ የተላከው መልክት ነጻ ሆኜ ትክክለኛ ፍትህ መስጠት ስለማያስችለኝ እራሴን ከመዝገቡ አስቻለው ሲሉ ከመዝገቡ ዳኝነት መነሳታቸውን በችሎት ይፋ አድርገዋል።

15/10/2014

ሕግ አገልግሎት/Legal Service እንደዘገበዉ
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀል፣ የሕግ ማዕቀፋ እና አተገባበሩ

ይህ ጽሑፍ ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀል በኢትዮጵያ ያስዳስሰናል።

ጸሐፊው፦ ገብረእግዚአብሔር ወልደገብርኤል

https://www.abyssinialaw.com/blog-posts/item/2031-fraudulent-misrepresentation-under-corruption-laws-in-ethiopia
በፍርድ ቤት 'የራስ አነሳሽነት' የሚሰጥ ብይን/ትዕዛዝ/ውሳኔ እና የመሰማት መብት
#አብርሃም ዮሐንስ

በወንጀል ጉዳይ በተለይ ደሞ በፍትሐብሔር ክርክር ወቅት ፍርድ ቤት በራሱ አነሳሽነት ብይን/ትዕዛዝ/ውሳኔ የመስጠት ሰፊ ስልጣን አለው። ጥቂት ምሳሌ መጥቀስ ቢያስፈልግ አቤቱታ እንዲሻሻል: ተጨማሪ ማስረጃ እንዲቀርብ ትዕዛዝ መስጠት፤ የስረ-ነገር ስልጣኑ ላይ ብይን መስጠት እንዲሁም የመብት መቅረት በጊዜ ገደብ ሲወሰን በመብቱ አለመኖር ላይ ውሳኔ መስጠት /ለምሳሌ አሰሪው የሚከራከርበት የስንብት ምክንያት ድርጊቱ መፈፀሙን አሰሪው ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ ሲታሰብ አንድ ወር ካለፈው/ የአሰሪው የማሰናበት መብት ቀሪ ይሆናል። ይህ ከይርጋ የተለየ እንደመሆኑ በፍርድ ቤቱ በራሱ ሊነሳ ይችላል። ከጊዜ ገደብ ጋር በተያያዘ የሰ/መ/ቁ 17361 ቅፅ 10 ይመለከቷል/

የራስ አነሳሸነት ለፍርድ ቤቱ አስገዳጅ ነው ወይስ 'የእንደፈቀደ' /discretionary/ ስልጣን የሚለው ጥያቄ መሰረታዊና አከራካሪ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ሌላ ይበልጥ መሰረታዊ ጉዳይ ጥያቄ ሆኖ ሲነሳ አይታይም።

በራስ አነሳሽነት የሚሰጥ ብይን/ትዕዛዝ/ውሳኔ መሰረታዊና እና ህገ-መንግስታዊ ከሆነው የመሰማት መብት አንጻር አሉታዊ እንደምታው በሚገባ አልተፈተሸም።

በምሳሌነት የስረ-ነገር ስልጣንን እንመልከት።
በተግባር እንደሚታየው ብሎም በስነ-ስርዓት ህጉ እና በሰበር ትርጉም ጭምር ድጋፍ ያገኘው አቋም አንድ ፍርድ ቤት የሰረ-ስልጣን ከሌለው በተከራካሪ ወገኖች ባይነሳም በራሱ አነሳሽነት መዝገቡን መዝጋት ይኖርበታል።
ግን በራስ አነሳሽነት ሲባል ምን ማለት ነው? በራስ አነሳሽነት የሚያስገነዝበው ፍርድ ቤቱ ነጥቡን መጀመሪያ በክርክር ወቅት ማንሳት አለበት ማለት ነው። የሚያነሳው ደግሞ ለተከራካሪ ወገኖች ነው። በዚሁ መሰረት ተከራካሪ ወገኖች በተነሳው ነጥብ ላይ ያላቸውን የህግ ክርክር ብሎም ማስረጃ ማቅረብ ወይም ማሰማት አስፈላጊ ከሆነ ማስረጃቸውን ሊያሰሙ ይገባል። የመሰማት መብት በግራ ቀኙ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ፍርድ የሚያነሳውንም ነጥብ ይጨምራል።

በራስ አነሳሽነት ማለት ተከራካሪ ወገኖች ሳያውቁትና ሳይሰሙ በድንገት እና በድብቅ የሚሰጥ ብይን/ትዕዛዝ/ውሳኔ ማለት አይደለም። ፍርድ ቤት የስረ-ነገር ስልጣኑን የሚወስነው በግምት ሳይሆን በተረጋገጡ አግባብነት ያላቸው ፍሬ ነገሮችና በህጉ ትርጓሜ ላይ በመመስረት ነው። በፍሬ ነገር /ማስረጃ/ እና የህግ ትርጉም በሚመለከት ጉዳይ ተከራካሪ ወገኖች የመሰማት መብት አላቸው።

ነገሩን እንደሚከተለው እንመልከተው።
የስረ-ነገር ስልጣን መቃወሚያ በተከራካሪ ከተነሳ ተቃራኒው ወገን የመሰማት መብት ካለው ፍርድ ቤት ስላነሳው ብቻ ይህን መብቱን የሚያጣበት አንዳችም የህግ መሰረት የለም።
በተጨማሪም ተካራካሪዎችን ያላሳተፈ 'የራስ አነሳሽነት' ለስህተት የመጋለጡ ዕድል በጣም ሰፊ ነው።

እንበልና በመኪና አደጋ የተነሳ ከውል ውጭ ሀላፊነት ክስ ሲቀርብ ተከሳሽ በመልሱ ላይ የጠቀሰው አድራሻ ተከራካሪዎች የተለያየ ክልል ነዋሪዎች መሆናቸውን ይጠቁማል። ሆኖም ተከሳሽ የጠቀሰው ቤተሰቡ የሚኖርበትን አድራሻ እንጂ መደበኛ የንግድ ስራውን የሚያከናውነውና አብዛኛውን ጊዜ የሚኖረው አደጋው በደረሰበት ክልል ነው። ተከሳሽ የስረ-ነገር ስልጣን አላነሳም። ከሳሽም በዚህ ነጥብ ላይ ማስተባበያ አላቀርበም። ካሁን አሁን ፍርድ ቤት በራሱ አነሳሽነት የስረ-ነገር ስልጣኑን በዚህ ላይ ተመስርቶ ብይን ሊሰጥ ይችላል በሚል ስሌት ማስተባበያ እንዲያቀርብም አይጠበቅበትም። ፍርድ ቤት በራሱ የሚያነሳቸው ነጥቦች በርካታ እንደመሆናቸው የትኛውም የህግ ባለሞያ ሁሉንም ከወዲሁ ሊያውቃቸው ሆነ ሊገምታቸው አይችልም።

ፍርድ ቤት በራስ አነሳሽነት የስረ-ነገር ስልጣኑን የመወሰን ሀሳብ ካለው ማድረግ ያለበት ተከራካሪ ወገኖች የተለያየ ክልል ነዋሪዎች መሆናቸውን እንደ ምክንያት ይዞ በራሱ ጊዜ መዝገቡ መዝጋት አይደለም። መጀመሪያ ከስልጣን ጋር በተያያዘ ፍርድ ቤቱ የስረ-ነገር ስልጣኑን ለመወሰን የተከራካሪ ወገኖች አድራሻ መጣራት እንዳለበት ለተከራካሪ ወገኖች በመንገር በዚህ ረገድ የህግ ክርክር ካላቸው በተጨማሪም ክርከራቸውን የሚደግፍ ማስረጃ ካላቸው እንዲያቀርቡ ዕድል መስጠት አለበት። ይህ ሲሆን ነው ተከሳሽ የንግድ ስራውና አብዛኛውን ጊዜ የሚኖረው አደጋው በደረሰበት ክልል መሆኑን ከሳሽ ማስተባበያ ማቅረብ የሚችለው። በተጨማሪም አንድ ሰው የንግድ እና የቤተሰብ መኖሪያ ስፍራው የተለያየ ከሆነ ለስረ-ነገር ስልጣን አወሳሰን የየትኛው ክልል ነዋሪ ነው? የሚለው የህግ ጭብጥ ግራ ቀኙ ሊከራከሩበት ይገባል።

በአጠቃላይ 'በራስ አነሳሽነት' ማለት ፍርድ ቤት በራሱ ጊዜ የሚያነሳው ሆኖም ባነሳው ነጥብ ላይ ግራ ቀኙ የመሰማት መብታቸው ተጠብቆ ከተከራከሩ በኋላ የሚሰጥ ብይን/ትዕዛዝ/ውሳኔ ማለት እንጂ ፍርድ ቤት ግራ ቀኙ ሳያውቁት ፍሬ ነገሩን በራሱ ገምቶ፣ የህጉን ትርጉም ለብቻው አውጥቶ አውርዶ መጨረሻ ላይ ድንገት የሚሰጠው ብይን/ትዕዛዝ/ውሳኔ ማለት አይደለም።
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties