አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Commercial Code/አዲሱ ንግድ ህግ
____
Feteh’s subcontractor ARTS TV produced a “Legal Reform in 5” spotlight program to introduce the revised Commercial Code Proclamation No. 1243/2021.

Mr. Fikadu Petros, a member of the Commercial Code Drafting Team, explains the changes made in relation to the types of business organizations that can be legally established and bankruptcy.

#USAIDETHIOPIA #FetehActivityEt

https://youtu.be/llH0rw5yYQE

#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
🎰 የማንዋል ደረሰኝ የሚጠቀም የታክስ ከፋይ
ኃላፊነት
ማንኛውም የማንዋል ደረሰኝ እንዲጠቀም የተፈቀደለት የታክስ ከፋይ የሚከተሉት ኃላፊነቶች ይኖሩበታል፡፡
• በባለሥልጣኑ ፈቃድ (ዕውቅና) ያልተሰጣቸውን ደረሰኞች አለመጠቀም፤
• ለአንድ ግብይት ጥቅም ላይ የዋለን ደረሰኝ ለሌላ ግብይት አለመጠቀም፤
• በበራሪና ቀሪ ቅጠሎች ላይ የተለያየ መረጃ አለመመዝገብ፤
• ግብይቱ ከተከናወነበት ሽያጭ ዋጋ የተለየ የገንዘብ መጠን በደረሰኙ ላይ አለማስፈር፤
• የደረሰኝ ህትመት ከተፈቀደለት ግብር ከፋይ ውጪ ለሌላ ታክስ ከፋይ ጥቅም ላይ እንዲውል አለማድረግ፤
• ያለደረሰኝ ሽያጭ አለማከናወን፤
• ደረሰኝ ለሚጠይቁ ግዥ ፈፃሚዎች ሽያጭ አለመከልከል፤
• ተመሳሳይ ቁጥር ያለው ደረሰኝ በማሳተም ጥቅም ላይ አለማዋል፤
• እንዲሰረዝ ውሳኔ በተሰጠበት ደረሰኝ አለመጠቀም፤
• ደረሰኝ ሲታተም ዝርዝር መረጃዎችን አሟልቶ የያዙ ደረሰኞችን አሳትሞ መጠቀም፤
• በራሪና ቀሪ ቅጠሎች ያለው ደረሰኝ ማሳተም፣ ደረሰኞችን በጥንቃቄ መያዝ እና ግብይት የተፈጸመባቸውን ደረሰኞች በታክስ አዋጁ እስከተገለፀ ጊዜ ድረስ ይዞ ማቆየት፣ ለሒሳብ ምርመራ ወይም ለግብር አወሳሰን እንዲቀርብ በሚጠየቅበት ጊዜ ማቅረብ፤
• የደረሰኝ አጠቃቀም መከታተያ ሌጀር ለሁሉም በግልጽ በሚታይበት ቦታ መስቀል እና ትክክለኛ መረጃ እንዲይዝ ማድረግ፤
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
1238_2013 የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ.pdf
2 MB
ይህ አዋጅ "የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ቁጥር ፩ሺ፪፻፴፰/፪ሺ፲፫" ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Online Media Directive_Ethiopia.pdf
292.8 KB
የበይነ-መረብ መገናኛ ብዙሃን መመሪያ
ቁጥር 902/2014

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን
ግንቦት 2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የዓለማችን ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ መሪ ማን ነው?

የሲንጋፖሩ ጠቅላይ ሚኒስትር በዓመት 2 ሚሊዮን ዶላር የሚከፈላቸው መሪ ናቸው።

https://am.al-ain.com/article/the-salary-list-of-world-leaders
የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰሞኑን በፓርላማ ባደረጉት ንግግር "1ኛ ደረጃ ሌቦች ዳኞች ናቸው" በሚል በገለፁት ጉዳይ ይቅርታ እንዲጠይቁ አሳሰበ።
Investment Flows to Africa Reached a Record $83 billion in 2021

Foreign direct investment (FDI) to African countries hit a record $83 billion in 2021, according to UNCTAD’s World Investment Report 2022 published on 9 June.
#EthiopianBusinessDaily
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
በአንድ ተማሪ ላይ የድብደባ ወንጀል የፈፀሙ የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!

ጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር ሆቴል በሚባል አካባቢ ሰኔ 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ በክፍል ውስጥ ርንቺት ተኩሶ ከት/ቤት ውስጥ አምልጦ የሄደ አንድ ተማሪን አራት የፖሊስ አባላት ተከታትለው በመያዝ የድብደባ ወንጀል ፈጽመውበታል፡፡

ህገ- ወጥ ድርጊቱ በማህበራዊ ሚዲያ ከተለቀቀ በኋላ ፖሊስ ባደረገው ማጣራት ድል በር 2ኛ ደረጃ በሚባል ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ነው በሚል ፕሮግራም ላይ በክፍል ውስጥ በተደረገ ዝግጅት አንድ ተማሪ ርችት እንደተኮሰ እና በት/ት ቤት ውስጥ ርችት መተኮሱ ሌሎች ተማሪዎችን እንደረበሻቸው ለፖሊስ መረጃ ይደርሰዋል፡፡

በእለቱ ድርጊቱን ፈፅሟል የተባለው ተማሪ ከት/ቤቱ ቅጥር ግቢ እንደወጣ የተነገራቸው 4 የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት ክትትል በማድረግ ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር የሚባል ሆቴል አካባቢ ተማሪውን ይዘውት ተገቢ ያልሆነ ድብደባ ፈፅመውበታል፡፡

የአ/አበባ ፖሊስ እንዳስታወቀው ፖሊስ መረጃው ካደርሰው በኋላ ተጠርጣሪ የፖሊስ አባላቱን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ ይገኛል፡፡

በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የህግ አስከባሪነት መነሻው ህግን ማክበር መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ የዜጎችን ህጋዊ መብት በሚፃረሩ የፖሊስ አባላት ላይ የሚወሰደውን ዕርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልና በማንኛውም ሁኔታ ህገወጥ ተግባራት ሲፈፀሙ ህ/ሰቡ በያገባኛል ስሜት የሚሰጠውን መረጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ ኢትዮመረጃ
የአማራ ክልልአቃቤ ህግ ማህበር ጠቅላይ ሚኒስትሩለህዝብ እንደራሴዎች 2ኛ ደረጃ ሌባ ዐቃቤ ህግ ነው ብለው የተናገሩትን ብያኔያዊ መግለጫ ማስተካከያ የማይሰጡበት ከሆነ ተገቢ ያልሆነውን ብያኔ ተከትሎ የሚመጣውን የአስፈፃሚ አካላት ጫና ማህበሩ እንደሚታገል ተገለፀ!
-----
@የአማራ ክልል ዓቃብያነ ሕግ ማሕበር