አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ሌሎች ቴክኒኮች፡- በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ቅድመዝግጅት ካለ ጥያቄዎችን በጽሁፍ አዘጋጅቶ የመቅረብ ነገር ሊኖር ይችላል:: ነገር ግን እንዲህ አይነቱ አቀራረብ መልካም አይደለም:: ጥያቄዎቹ በጽሁፍ ከተዘጋጁ ወይ እያነበቡ ለመጠየቅ ነዉ አለያም ሸምድዶ ከሃሳብ እያስታወሱ ለመጠየቅ ነዉ:: ሁለቱም ተመሳሳይ ናቸዉ:: ወረቀት ላይ የምናተኩር ከሆነ ወይም በአዕምሯችን ስለምናስታዉሰዉ ነገር የምናስብ ከሆነ ምስክሩን ዓይንለዓይን አንገናኝም ማለት ነዉ:: በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ ከምስክሩ ጋር የዓይንላይን ግንኙነት መኖር ምስክሩን ለመቆጣጠር ይረዳል:: ከዚህም ሌላ ያልተጠበቁ ለክሱ የሚጠቅሙ አጋጣሚዎችን ለመጠቀም በጥያቄና መልሱ ሂደት ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል:: ጥያቄን ከወረቀት ላይ ወይም ከአዕምሮ ዉስጥ ማንበብ ይህን አትኩሮት ስለሚነፍግ በዚህም ረገድ ዐቃቤህግ ብሎም ክሱ ተጎጂ ይሆናሉ:: በተለይ ጥያቄዉ በርከት ያለ ከሆነ አንዱ ጥያቄ ተመልሶ ሌላ ለመጠየቅ በዝርዝሩ ዉስጥ የሚቀጥለዉ ጥያቄ ቦታ እንዳይጠፋ በማሰብ አትኩሮትን ወደዚሁ ጽሁፍ ለማድረግ መገደድ ይኖራል::
ከዚህ የተሻለዉ አማራጭ ጥያቄዉን በዝርዝር አለመጻፍ ነዉ:: ዝግጅቱ የግድ በጽሁፍ መሆን ካለበት የጥያቄዎቹን ሃሳቦች የያዙ ርዕሶችን ዝርዝር (አዉትላይን) አዘጋጅቶ መቅረብ ይመረጣል:: ርዕሶቹን ብቻ ከወረቀቱ ላይ በመመልከት ጥያቄዎቹን ከራስ ማመንጨት ይገባል::

አትኩሮትን ወደጥያቄና መልሱ ሂደት ማድረግ ተገቢ ስለመሆኑ ከፍ ብሎ ተጠቅሷል:: ከዚህ በተያያዘ ለመሰቀለኛ ጥያቄ የሚሰጡ መልሶችን ዐቃቤህግ ማድመጥ ይኖርበታል:: ለክሱ ገንቢ የሆኑ አጋጣሚዎችን ለመጠቀም የሚረዳ ከመሆኑም በላይ ምስክሩ ጥያቄዉን እየሸሸ የሚመልስ ከሆነ ይህን አስተዉሎ ጥያቄዉ እንዲመለስ ለማስገደድ (ምስክሩን ለመቆጣጠር) የሚያስችል ነዉ:: ከዚህ ከማድመጥ የሚያሰናክለዉ አንዱ ከላይ እንደተመለከትነዉ ጥያቄን በዝርዝር ጽፎ ቀርቦ በንባብ መጠየቅ ሲሆን ሌላኛዉ ደግሞ ምስክርነቱን በዝርዝር መጻፍ ነዉ:: ሰለዚህ እነዚህን የአሰራር ዘዴዎች ወይም ባህሪዎች ዐቃቤህግ ሊያስወግድ ይገባል::
አንዳንድ ጊዜ የተቃራኒ ወገን ምስክር ሳያስበዉ ወይም ከዐቃቤህግ የአጠያየቅ ብቃት የተነሳ ለክሱ ጠቃሚ ምስክርነት ሊስጥ ይችላል:: በሌሎች አጋጣሚዎች ደግሞ ክሱን የሚጎዳ ነገር ሊመሰክር ይችላል:: በዚህ ጊዜ ዐቃቤህግ እንደተሰጠዉ ምስክርነት ጠቃሚነት ወይም ጎጂነት ስሜቱ የሚለዋወጥ ከሆነ ምስክሩ በሰጠዉ ምስክርነት እያደረሰ ያለዉን ዉጤት በሚገባ እንዲገነዘብ ስለሚያደርገዉ የተከሳሹን ክርክር የሚጎዳዉን ምስክርነት ያስተካክላል የዐቃቤህግን ክስ የጎዳበትን ምስክርነት በማጠናከር የበላይነቱን ይዞ የክርክሩን ሂደት የመቆጣጠሩን ሚና ከዐቃቤህግ ይነጥቃል::
የተከሳሽ ምስክር ለዐቃቤህግ ክስ ገንቢ የሆነ ምስክርነት ከሚሰጥባቸዉ አጋጣሚዎች አንዱ መዋሸት ነዉ:: መዋሸቱን የምናዉቅ ከሆነ ከምስክርነቱ በተቃራኒ የሆነዉን ዕዉነተኛዉን ታሪክ የሚያሳይ ማስረጃ አለን ማለት ነዉ:: ስለዚህ ምስክሩ ሲዋሽ ካገኘነዉ በዚሁ ዉሸቱ እንዲቀጥልበት የሚያደርጉ ጥያቄዎችን ማንሳት እንጂ መዋሸቱን ያወቅንበት መሆኑን የሚገልጽ ምንም ነገር ማድረግ የለብንም:: ምክንያቱም ይህን ከገለጽን የዋሸበትን ሁኔታ ያስተካክላል ስለዚህ ዐቃቤህግ ምስክሩ የማይታመን ወይም የሚዋሽ መሆኑን የሚያስረዳበትን አጋጣሚ ያጣል ማለት ነዉ::
በብዙ አጋጣሚዎች አላዋቂ መስሎ ላለመታየት በሚደረግ ጥረት ክርክርን መጉዳት ሊከተል ይችላል:: ስለዚህ በማያዉቁት ጉዳይ ጥያቄ ከመጠየቅ አለመቦዘን ተገቢ ነዉ:: ለምሳሌ በባለሙያ ምስክርነት ጊዜ ለባለሙያዉ ወይም ስለጉዳዩ ዕዉቀት ላላቸዉ ሰዎች ተራ የሆነ ነገር ሁሉ ለዐቃቤህግ ግልጽ ላይሆን ይችላል:: ስለዚህ አላዋቂ ላለመምሰል የባለሙያ ምስክርነት በሚነገርበት ጊዜ ነገሩ እንደገባዉ ሰዉ ዝም ብሎ ማዳመጥ ጉዳቱን ማወቅ የሚቻለዉ ነገሩ ካለቀ በኋላ ሰለሚሆን ጥንቃቄ ይፈልጋል:: በዚህ ረገድ ግልጽ ያልሆነን ነገር ማብራሪያ እንዲሰጥበት መጠየቅ ሊያሳፍር አይገባም ምንም ያህል ተራ ነገር ቢሆን ወይም ቢመስል::
ቀደም ሲል ለማየት እንደተሞከረዉ መስቀለኛ ጥያቄ አደጋ ያለዉ ሂደት ነዉ እንደተገኘ የሚገባበት አይደለም:: ጥንቃቄ ያሻዋል:: ተመራጭ ሆኖ ወይም አማራጭ የሌለዉ ሆኖ ጥያቄዉ መካሄድ ያለበት ከሆነ የተመጠነ ሊሆን ይገባዋል:: በዚህ ጊዜ ምስክሩን ለመቆጣጠር መቻል ያስፈልጋል:: ለዚህም የማያጨቃጭቁ ጥያቄዎችን ማንሳት አንዱ ከምስክሩ ጋር ያለመፋጠጥ ሁኔታ መፍጠሪያ መንገድ ሲሆን ሌላዉ የጥያቄዉን ሂደት ዓላማ መደበቅ መቻል ነዉ:: ይህ ማለት ግን ምስክሩን ማፋጠጥ ወይም ማስጨነቅ በማንኛዉም አጋጣሚ ተገቢ አይደለም ማለት አይደለም:: ተቃራኒ ምስክር እንደመሆኑ የምንፈልገዉን ነገር በቀላሉ ሊሰጠን አይችልም ወይም አይፈቅድም:: ስለዚህ አንዳንድ ጊዜ ፍጥጫ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል:: ትልቁ ጥያቄ ግን መቼ የሚለዉ ነዉ:: ይህን ነገር መቼ ማድረግና አለማድረግ እንዳለብን የምናዉቅባቸዉን አንዳንድ ሁኔታዎች መለየት ያስፍልጋል::
ምስክርን ማስጨነቅ ወይም ማፋጠጥ ተገቢ የሚሆንበት ጊዜ ምልክቶች - የምስክሩ መረጋጋት አለመቻል ከጠበቃዉ ርዳታን መጠበቅ መናደድ ወይም ማድበስበስ መጀመር የጠበቃዉ ማደናገሪያ ወይም አቅጣጫ ማስቀየሪያ ተቃዉሞዎች መበራከት - እነዚህና መሰል ሁኔታዎች ምስክሩ ለማፋጠጥ የተጋለጠ መሆኑን ጠቋሚ ናቸዉ:: በዚህ ጊዜ ምስክሩ የደበቀዉን ለማዉጣት ወይም ነገሮችን ማሳሳት ወይም ማዘባረቅ ጀምሮ ከሆነ የበለጠ ነገር የሚያበላሽበት ሁኔታ ዉስጥ መሆኑን መረዳትና ማፋጠጡን ማጠንከር ያስፈልጋል::
በዚህ ሁኔታ የተጀመረ ማፋጠጥ ቢኖርም ምስክሩ እየጠነከረ ከመጣና በቀላሉ የሚፈታ ሰዉ ካልሆነ ማፈግፈግ - መተዉ ተመራጭ ነዉ::
ምስክሩን ማፋጠጥ ተገቢ የማይሆንባቸዉ አጋጣሚዎች ሲኖሩ በቀጥታ ማጥቃትን ማስቀረት ተገቢ ነዉ:: ይህ ተገቢ የሚሆንባቸዉ ሁኔታዎች ባብዛኛዉ ሃዘኔታን ወይም አክብሮትን የሚያገኙ ሰዎች ምስክር የሆኑባቸዉ አጋጣሚዎች ናቸዉ:: እነዚህም - ህጻናት አዛዉንት የሃይማኖት ሰዎች ወይም አባቶች ወዘተ ናቸዉ:: በነዚህ አጋጣሚዎች በቂና አስተማማኝ ማስረጃ ካልኖረ በቀር እንደዚህ አይነት ሰዎችን ማፋጠጥና ማስጨነቅ በዳኞችና ሂደቱን በሚከታለዉ ህኅብረተሰብ ፊት የሚያስጸይፍ ሊሆን ስለሚችል ዉጤቱ አፍራሽ ይሆናልና ይህ አይነቱን አቀራረብ መተዉ ተገቢ ነዉ::

ምስክርን ስለማስተባበል፡- ከመስቀለኛ ጥያቄ ሂደት ጋር የማይነጣጠለዉ ይህ ምስክርን የማስተባበል ነገር በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 145 የተፈቀደ ነዉ:: ይህ ህግ ተከሳሽ የዐቃቤህግን ምስክር የሚያስተባብልበትን ሥነሥርዓት ብቻ የሚደነግግ ይመስላል:: ሆኖም በፖሊስ ጣቢያ የተሰጠ ምስክርነት ጽሁፍ ለምስክርነት ማስተባበያ ይሆን ዘንድ ከመፈቀዱ በፊት ለፍርድቤት የሚቀርበዉ በተከሳሽ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን በዐቃቤህግም ጭምር ነዉ:: ከዚህ በኋላ ፍርድቤት ጽሁፉን ለማስተባበያነት እንዲሰጠዉ የሚያደርገዉ ለተከሳሹ ነዉ::
ያም ሆነ ይህ በተለመደዉ አሰራር መሰረት ዐቃቤህግ የራሱን ምስክር በተመለከተ ቃሉን እየለወጠ መሆኑን ለማስረዳት በፖሊስ ጣቢያ የሰጠዉን ቃል ጽሁፍ ለምስክሩ አሳይቶ ፊርማዉን እንዲያረጋግጥ ካደረገ በኋላ ለፍርድቤት በማቅረብ ሲያስወስን ይታያል:: በተመሳሳይ ሁኔታ የተከሳሹ ምስክር በፖሊስ ምርመራ ጊዜ የሰጠዉን ቃል ጽሁፍ ለማስተባበያነት እንዲታይለት ቢጠይቅ ምን ስህተት አለዉ? የተከሳሽ ምስክር በፖሊስ ጣቢያ የምስክርነት ቃል ሊያስመዘግብ ይችላል? የተከሳሽ ምስክር በወንጀል ምርመራ ጊዜ በጉዳዩ ላይ ቃሉን በምስክርነት ከሰጠ በኋላ ዐቃቤህግ ማስረጃ አድርጎ ሳይቆጥረዉ ቢቀርና ተከሳሽ ምስክሩ ቢያደርገዉ ለፖሊስ ምስክርነቱን የሰጠ ምስክር ሊባል አይችልም?
በኢትዮጵያ ህግ መሰረት የሚደረገዉ ማስተባበል ቀድሞ በተሰጠ ቃል ላይ የተመረኮዘ ነዉ:: ሆኖም የማስትባበል ስራ ቀደም ሲል በምስክሩ በተደረገ ሌላ ተግባርም ሊከናወን ይችላል:: እንዲሁም የምስክሩን ባህሪ (ምናልባትም የመዋሸት) እና በጉዳዩ ዉጤት ምስክሩ የሚኖረዉን ጥቅም በማሳየት ምስክሩን ማስተባበል ይቻላል::

ከወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 145 ዉጪ ያሉ ምስክር ማስተባበያ ዘዴዎች፡- የቀድሞ የምስክር ቃልንም በተመለከተ ህጉ በፖሊስ ጣቢያ የተመዘገበን ቃል ብቻ ይገልጻል:: ቀደም ሲል በፍርድቤት በማንኛዉም ጉዳይ የተመዘገበ ቃልስ ምስክሩን ለማስተባበል አይዉልም? የቀዳሚ ምርመራ ፍርድቤት የመዘገበዉ ምስክርነት ለዚህ አገልግሎት ማዋል አይቻልም? በክስ መስማት ጊዜ በፍርድቤት ከሚደረግ የቃል ምዝገባ ሌላ ቃልን ለመመዝገብ ብቻ በሚሰራ ፍርድቤት ቃል ሊመዘገብ አይችልም (የወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 35)? ምስክሩ ባለዉ የሥራ ኃላፊነት መሰረት የጻፋቸዉ ጽሁፎች ወይም ደብዳቤዎች ምስክሩን ለማስተባበል አያገለግሉም?
በነዚህ በሁሉም ሆነ በፖሊስ ጣቢያ ቃል ምስክርን ለማስተባበል አስቀድሞ ይህን ቃል ወይም መጻጻፍ እና ይዘቱን ማወቅ እንደሚያስፈልግ አያጠያይቅም:: ለዚህ ደግሞ ከዚህ በፊት እንደተገለጸዉ ዝግጅት ማድረግ የማይታለፍ ይሆናል::
Via #Tsegaye Demeke - Lawyer
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Commercial Code/አዲሱ ንግድ ህግ
____
Feteh’s subcontractor ARTS TV produced a “Legal Reform in 5” spotlight program to introduce the revised Commercial Code Proclamation No. 1243/2021.

Mr. Fikadu Petros, a member of the Commercial Code Drafting Team, explains the changes made in relation to the types of business organizations that can be legally established and bankruptcy.

#USAIDETHIOPIA #FetehActivityEt

https://youtu.be/llH0rw5yYQE

#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
🎰 የማንዋል ደረሰኝ የሚጠቀም የታክስ ከፋይ
ኃላፊነት
ማንኛውም የማንዋል ደረሰኝ እንዲጠቀም የተፈቀደለት የታክስ ከፋይ የሚከተሉት ኃላፊነቶች ይኖሩበታል፡፡
• በባለሥልጣኑ ፈቃድ (ዕውቅና) ያልተሰጣቸውን ደረሰኞች አለመጠቀም፤
• ለአንድ ግብይት ጥቅም ላይ የዋለን ደረሰኝ ለሌላ ግብይት አለመጠቀም፤
• በበራሪና ቀሪ ቅጠሎች ላይ የተለያየ መረጃ አለመመዝገብ፤
• ግብይቱ ከተከናወነበት ሽያጭ ዋጋ የተለየ የገንዘብ መጠን በደረሰኙ ላይ አለማስፈር፤
• የደረሰኝ ህትመት ከተፈቀደለት ግብር ከፋይ ውጪ ለሌላ ታክስ ከፋይ ጥቅም ላይ እንዲውል አለማድረግ፤
• ያለደረሰኝ ሽያጭ አለማከናወን፤
• ደረሰኝ ለሚጠይቁ ግዥ ፈፃሚዎች ሽያጭ አለመከልከል፤
• ተመሳሳይ ቁጥር ያለው ደረሰኝ በማሳተም ጥቅም ላይ አለማዋል፤
• እንዲሰረዝ ውሳኔ በተሰጠበት ደረሰኝ አለመጠቀም፤
• ደረሰኝ ሲታተም ዝርዝር መረጃዎችን አሟልቶ የያዙ ደረሰኞችን አሳትሞ መጠቀም፤
• በራሪና ቀሪ ቅጠሎች ያለው ደረሰኝ ማሳተም፣ ደረሰኞችን በጥንቃቄ መያዝ እና ግብይት የተፈጸመባቸውን ደረሰኞች በታክስ አዋጁ እስከተገለፀ ጊዜ ድረስ ይዞ ማቆየት፣ ለሒሳብ ምርመራ ወይም ለግብር አወሳሰን እንዲቀርብ በሚጠየቅበት ጊዜ ማቅረብ፤
• የደረሰኝ አጠቃቀም መከታተያ ሌጀር ለሁሉም በግልጽ በሚታይበት ቦታ መስቀል እና ትክክለኛ መረጃ እንዲይዝ ማድረግ፤
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
1238_2013 የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ.pdf
2 MB
ይህ አዋጅ "የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ቁጥር ፩ሺ፪፻፴፰/፪ሺ፲፫" ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Online Media Directive_Ethiopia.pdf
292.8 KB
የበይነ-መረብ መገናኛ ብዙሃን መመሪያ
ቁጥር 902/2014

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን
ግንቦት 2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የዓለማችን ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ መሪ ማን ነው?

የሲንጋፖሩ ጠቅላይ ሚኒስትር በዓመት 2 ሚሊዮን ዶላር የሚከፈላቸው መሪ ናቸው።

https://am.al-ain.com/article/the-salary-list-of-world-leaders
የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰሞኑን በፓርላማ ባደረጉት ንግግር "1ኛ ደረጃ ሌቦች ዳኞች ናቸው" በሚል በገለፁት ጉዳይ ይቅርታ እንዲጠይቁ አሳሰበ።
Investment Flows to Africa Reached a Record $83 billion in 2021

Foreign direct investment (FDI) to African countries hit a record $83 billion in 2021, according to UNCTAD’s World Investment Report 2022 published on 9 June.
#EthiopianBusinessDaily
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
በአንድ ተማሪ ላይ የድብደባ ወንጀል የፈፀሙ የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!

ጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር ሆቴል በሚባል አካባቢ ሰኔ 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ በክፍል ውስጥ ርንቺት ተኩሶ ከት/ቤት ውስጥ አምልጦ የሄደ አንድ ተማሪን አራት የፖሊስ አባላት ተከታትለው በመያዝ የድብደባ ወንጀል ፈጽመውበታል፡፡

ህገ- ወጥ ድርጊቱ በማህበራዊ ሚዲያ ከተለቀቀ በኋላ ፖሊስ ባደረገው ማጣራት ድል በር 2ኛ ደረጃ በሚባል ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ነው በሚል ፕሮግራም ላይ በክፍል ውስጥ በተደረገ ዝግጅት አንድ ተማሪ ርችት እንደተኮሰ እና በት/ት ቤት ውስጥ ርችት መተኮሱ ሌሎች ተማሪዎችን እንደረበሻቸው ለፖሊስ መረጃ ይደርሰዋል፡፡

በእለቱ ድርጊቱን ፈፅሟል የተባለው ተማሪ ከት/ቤቱ ቅጥር ግቢ እንደወጣ የተነገራቸው 4 የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት ክትትል በማድረግ ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር የሚባል ሆቴል አካባቢ ተማሪውን ይዘውት ተገቢ ያልሆነ ድብደባ ፈፅመውበታል፡፡

የአ/አበባ ፖሊስ እንዳስታወቀው ፖሊስ መረጃው ካደርሰው በኋላ ተጠርጣሪ የፖሊስ አባላቱን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ ይገኛል፡፡

በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የህግ አስከባሪነት መነሻው ህግን ማክበር መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ የዜጎችን ህጋዊ መብት በሚፃረሩ የፖሊስ አባላት ላይ የሚወሰደውን ዕርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልና በማንኛውም ሁኔታ ህገወጥ ተግባራት ሲፈፀሙ ህ/ሰቡ በያገባኛል ስሜት የሚሰጠውን መረጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ ኢትዮመረጃ
የአማራ ክልልአቃቤ ህግ ማህበር ጠቅላይ ሚኒስትሩለህዝብ እንደራሴዎች 2ኛ ደረጃ ሌባ ዐቃቤ ህግ ነው ብለው የተናገሩትን ብያኔያዊ መግለጫ ማስተካከያ የማይሰጡበት ከሆነ ተገቢ ያልሆነውን ብያኔ ተከትሎ የሚመጣውን የአስፈፃሚ አካላት ጫና ማህበሩ እንደሚታገል ተገለፀ!
-----
@የአማራ ክልል ዓቃብያነ ሕግ ማሕበር