አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የህፃናት መብት

ሕፃናት እንደ ማንኛውም ተፈጥሮአዊ ሰው መብት ያላቸው ሲሆን በሥነ-አዕምሮአዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ፣ ማኅበራዊ ግንኙነት እንዲሁም አካላዊ ሁኔታ ምክንያት ተጨማሪ ጥበቃ እንደሚያስፈልጋቸው በዓለም አቀፍና ብሔራዊ ህግ ማዕቀፎች ተደንግጓል፡፡ በዚህ የንቃተ ህግ ፅሁፍ በአጠቃላይ መሰረትዊ የህፃናት መብቶች እና ህፃናትን በተመለከተ የተደነገጉ መርሆችን ለመዳሰስ ተሞክሯ፡፡

1. የህፃን ትርጉም

ለሕፃንነት የሕግ ትርጓሜ መስጠትን አስፈላጊ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል ዋነኛው የመብትና ግዴታ ወሰን (scope of rights and duties) ለማወቅ ስለሚያስችል ነው፡፡ እንዲሁም ሕፃናት ለአደጋ ተጋላጭ ከመሆናቸው አኳያ ልዩ ጥበቃ (special protection due to vulnerability) ስለሚያስፈልጋቸው ህፃናትን በመለየት ይህን ጥበቃ ለማድረግ ነው፡፡
ህፃን ማን ነው ለሚለው ጥያቄ የተለያዩ አገራት ሕጎች የተለያየ ትርጓሜ ሰጥተዋል፡፡ ምንም እንኳ አንድ ወጥ የሆነ የሕፃን ትርጓሜ ባይኖርም ሕፃን የሚለው ቃል ብዙ አገራት ዕድሜን ግምት ውስጥ ያስገባ ትርጉም ይጠቀማሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር በአንዳንድ አገሮች ሕፃን ለሚለው ትርጓሜ ለመስጠት ማኅበራዊ አረዳድን (social construction of age) ግምት ውስጥ የሚያስገቡ ሲሆን ለምሳሌ በጉርምስና ወቅት የሚታዩ አካላዊ ለውጦች እና የድምፅ መጎርነን ከግምት ውስጥ ያስገባሉ፡፡

በዓለም አቀፍ የሕፃናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀፅ 1 የተመለከተው ዕድሜን መሠረት ያደረገ ትርጉም ሲሆን “ሕፃን ማለት ማንኛውም ዕድሜው ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች የሆነ የተፈጥሮ ሰው” እንደሆነ ይገልፃል፡፡ ሆኖም በምን ጉዳይና ምን ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ዝቅ ማድረግ ወይም 18 ዓመት ሳይሞላ ለአካለ መጠን መድረስ እንደሚቻል ባያስቀምጥም አገራት በሚያወጡት ሕግ መሠረት ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች መውረድ የሚቻልበት አጋጣሚም እንዳለ በኮንቬንሽኑ ተገልጧል፡፡ በዚሁ መሰረት ለምሳሌ በኢትዮጵያ ለጋብቻ ሊባል ማለትም ከባድ ምክንያት ሲያጋጥም ተጋቢዎቹ ወይም ከተጋቢዎቹ የአንዳቸው ወላጆች ወይም አሳዳሪ በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት ፍትህ ሚኒስትሩ ከመደበኛ የጋብቻ እድሜ (18 ዓመት) ከሁለት አመት ያልበለጠ ጊዜ በመቀነስ እንዲጋቡ ሊፈቅድ ይችላል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሕፃኑ ከሞግዚት አስተዳደር ነፃ እንደወጣ (emancipated) ይቆጠራል፡፡ ይህ የዕድሜ ጣራ መድረሻ (አሥራ ስምንት ዓመት) ከየት እንደሚጀምር በግለፅ የተደነገገ ነገር ባይኖርም በኮንቬንሽኑ መግቢያ ላይ እንደተገለፀው ከመወለድ በፊትም ማለትም በጽንስ ወቅትም ጥበቃ እንዳለ ግንዛቤ መውሰድ ይቻላል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ የአፍሪካ የሕፃናት መብቶች እና ደህንነት ቻርተር አንቀፅ 2 ሕፃን ለሚለው ትርጓሜ ሲሰጥ “ሕፃን ማለት ማንኛውም ዕድሜው ከአሥራ ስምንት ዓመት በታች የሆነ የተፈጥሮ ሰው ነው” በማለት ደንግጓል፡፡

በኢትዮጵያ ለሕፃን ያለውን ትርጉም ስንመለከት ሀገሪቱ ፌደራላዊ ስርዓት የምትከተል በመሆኑ እና የ1987 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራስያዊ ሪፐብሉክ ሕገ መንግሥት የፌደራል እና የክልል መንግሥታት የየራሳቸውን የቤተሰብ ሕግ እንዲያወጡ ስለሚፈቅድ የተለያየ የሕፃን ትርጓሜ ሊኖር የሚችልበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡ በፌደራል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 215 መሠረት አካለ መጠን ያልደረሰ ሰው ማለት ጾታ ሳይለይ ዕድሜው አሥራ ስምንት ዓመት ያልሞላው ልጅ ነው፡፡

2. የህፃናት መብት መርሆዎች

ዓለም አቀፍ እና አገር አቀፍ ሕጎች የሕፃናት መብቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል በማሰብ የተለያዩ መርሆዎችን አውጥተዋል፡፡ እነዚህ መርሆዎች የሕፃናት መብቶች ለማስከበር እና ማስተግበር ከፍተኛ አስተዋፅዖ አላቸው፡፡ ከእነዚህ መርሆዎች ዋነኛው የሆነው ለሕፃናት ጥቅምና ደህንነት ቅድሚያ መስጠት (Best interest of the child) የሚለው መርህ ነው፡፡ በዚህ ረገድ እ.ኤ.አ በ1959 የወጣው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሕፃናት መብቶች መግለጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕፃናት ጥቅም እና ደህንነት ቅድሚያ መስጠት የሚለውን መርህ አካቶ የወጣ ዓለም አቀፍ ሰነድ ነው፡፡ በመሆኑም ሕፃናት ነክ ውሳኔዎች ሲወሰኑ (ለምሳሌ ወላጆቻቸው የሚለያዩ ከሆነ ከማን ጋር መኖር እንዳለባቸው ሲወሰን) ውሳኔ ሰጭ አካላት ለሕፃናት ጥቅምና ደህንነት ቅድሚያ በመስጠት የሕግ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡ በተያያዘ ሁኔታ የኮንቬንሽኑ አራት ዋና ዋና መርሆዎች በሕፃናት መብቶች ኮንቬንሽን ውስጥ የተዘረዘሩትን ሌሎች መብቶች ለማስፈፀም እና ለመተርጎም የሚያገለግሉ ናቸው ፡፡

እነርሱም፣
• የእኩልነት መብት (The Non-discrimination clause) የኮንቬንሽኑ አንቀፅ 2
• ለህፃናት ጥቅምና ደህንነት ቅድሚያ መስጠት (The Best Interest of the Child) የኮንቬንሽኑ አንቀፅ 3)
• የመሳተፍ መብት (The Right to participation) ኮንቬንሽኑ አንቀፅ 12፣
• በሕይወት የመኖር እና የመልካም አስተዳደግ መብት (The Right to life, survival and development) የኮንቬንሽኑ አንቀፅ 6፣ ናቸው፡፡

3. መሰረታዊ የህፃናት መብቶች በኢትዮጵያ

የሀገራችን ህገ መንግስት ለህፃንነት ትርጉም ያልሰጠ ወይም የእድሜ ገደብ ያላስቀመጠ ቢሆንም የህፃናትን መብት ዝርዝር በአንቀፅ 36 ስር ደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት ማንኛውም ህፃን የሚከተሉት መብቶች አሉት፡-

1. በህይወት የመኖር መብት፣
2. ስምና ዜግነት የማግኘት መብት፣
3. ወላጆቹን ወይም በህግ የማሳደግ መብት ያላቸውን ሰዎች የማወቅና የእነሱንም እንክብካቤ የማግኘት መብት፣
4. ጉልበት ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ፣ በትምህርት፣ በጤናውና በደህንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ስራዎች እንዲሰራ ያለመገደድ ወይም ከመስራት የመጠበቅ፣
5. በትምህርት ቤቶች ወይም በሕፃናት ማሳደጊያ ተቋሞች ውስጥ በአካሉ ከሚፈፀም ወይም ከጭካኔና ኢ-ሰብዓዊ ከሆነ ቅጣት ነፃ የመሆን መብት ናቸው፡፡

በተጨማሪም በህገ መንግስቱ እንደተደነገገው ህፃናትን የሚመለከቱ እርምጃዎች በሚወሰዱበት ጊዜ በመንግስታዊ ወይም በግል በጎ አድራጎት ተቋሞች፣ በፍርድ ቤቶች፣ በአስተዳደር ባለስልጣኖች ወይም በህግ አውጪ አካላት የህፃናት ደህንነት በቀደምትነት መታሰብ አለበት፡፡ ወጣት አጥፊዎች በማረሚያ ወይም በመቋቋሚያ ተቋሞች የሚገኙ በመንግስት እርዳታ የሚያድጉ ወጣቶች በመንግስት ወይም በግል እጓለ ማውታን ተቋሞች (የህፃናት ማሳደጊያዎች) ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች ከአዋቂዎች ተለይተው መያዝ አለባቸው፡፡ እንዲሁም ከጋብቻ ውጪ የተወለዱ ሕፃናት በጋብቻ ከተወላዱ ሕፃናት ጋር እኩል መብት አላቸው፡፡ እንዲሀም መንግስት ለእጓለ ማውታን ልዩ ጥበቃ እንደሚያደርግላቸው እና በጉዲፈቻ የሚያድጉበት ሥርዓት የሚያመቻቹና የሚያስፋፉ፣ ደህንነታቸውንና ትምህርታቸውን የሚያራምዱ ተቋሞች እንዲመሰረቱ እንደሚያበረታታ ይደነግጋል፡፡
በአጠቃላይ ህፃናት የሚከተሉት አለም አቀፍ መሰረታዊ መብች ሊጠበቁላቸው ይገባል፡፡
• የእኩልነት መብት:- በጾታ፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በቋንቋ፣ በኢኮኖሚ አቋም፣ በብሔር ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት ወይም አድሎአዊ በሆነ በማንኛውም ሁኔታ ላይ በመመርኮዝ ልዩነቶች ሊደረጉ አይገባም፡፡
• መብላት እና መጠለያ የማግኘት መብት:- ሁሉም ልጆች ለትክክለኛው እድገታቸው አስፈላጊ የሆነውን ምግብ የማግኘት እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሚኖሩበት ቤት የማግኘትና የመደሰት መብት አላቸው ፡፡
• የትምህርት መብቶች:- ሁሉም ልጆች ችሎታቸውን ለማዳበር እና የራሳቸውን የወደፊት ዕድል ለመፍጠር ትምህርት የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ምክንያቱም ለትክክለኛው ሥነ-ልቦናዊ፣ ስሜታዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገታቸው አስፈላጊ ነው፡፡
• የጤንነት መብት:- ልጆች ጤንነታቸውን ለመንከባከብ እና ለማቆየት እንዲሁም በሽታን ለመከላከል አስፈላጊ የሕክምና ክትትል እና እንክብካቤ ማግኘት አለባቸው፡፡ ወደ ጤናማ አዋቂዎች እንዲያድጉ ጥሩ ፈውስ የማግኘት መብት አላቸው፡፡
• በሕይወት የመኖር መብት፡- ሕፃናት ህይወታቸውን አደጋ ላይ ሊጥሉ ከሚችሉ ነገሮች የመጠበቅ እና የመትረፍ (right of protection and survival) መብት አላቸው፡፡ እንዲሁም በቂ የኑሮ ደረጃ (adequate standard of living) የማግኘት መብት አላቸው፡፡

በአጠቃላይ ህፃናት በተለይ በእድሜያቸው ምክንያት ለተለያዩ አደጋዎች የመጋለጥ እድላቸው ከፍተኛ ስለሆነ መንግስት በሂደት (progressively) የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በፈቀደ መጠን የህፃናትን ደህንነት ለማስጠበቅ የህፃናትን መብት ለማክበር፣ ለመጠበቅ እና ለማሟላት ጥረት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
በንቃተ ሕግ፣ ትምህርትና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት
#አለ_ህግ
#Share #Share #Share #Share
https://t.me/lawsocieties
The application has finished.
they have taken what they want.
Stop applying. Save your time.
#አለ_ህግ
#አለ_ስራ
#አለ_ህግ
#አለ_ችሎት
#አለ_ስራ
#አለ_ዜና
#አለ_ትምህረት
#አለ_ልዩ ልዩ
......................
የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ ክሶች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች 🔴ሁሉም ሕጎች በአንድ🔴 All in one, for All.

አለ_ህግ፣ መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው።
contact us: @LawsocietiesBot or email us: lawsocieties@gmail.com

@lawsocieties

#አለ_ህግ

#Share #Share #Share #Share
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade 42.docx
43.2 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade.pdf
272.5 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade 42.docx
43.2 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade 4.pptx
118 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
Trade remedies.pptx
73.9 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade.pdf
272.5 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade 42.docx
43.2 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
trade 4.pptx
118 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️ (Alemwaza)
Trade remedies.pptx
73.9 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️
813_2013-trade-competition-and-consumers-protection.pdf
26.8 MB
Forwarded from አለሕግAleHig ️
Law Of Traders & Bisness Organizations.pptx
408.1 KB
Forwarded from አለሕግAleHig ️
813_2013-trade-competition-and-consumers-protection.pdf
26.8 MB
እስከ መጋቢት 12/2014 ዓ.ም የማስገቢያ ጊዜው ተራዝሟል
አለሕግAleHig ️
የህግ የበላይነት ብዙ ምሁራን በየፊናቸው በምርምርና ጥናት ባገኙት እውቀት ተመርኩዘው የህግ የበላይነት መርህ ምንነት፤ ይዘትና ፋይዳውን አስመልክቶ አያሌ ንድፈ ሀሳባዊ ትንታኔዎችን አቅርበዋል፡፡ በአገራችን ደግሞ አባቶችና እናቶች በልባቸው ከተጻፈው እውነትና ከልምድ ከቀዱት ቱባ እውቀት በመነሳት የህግ የበላይነትን ጽንስ ሀሳብ በአንድ አባባል እንዲህ ይገልጹታል፡፡ “በፍርድ ከሄደች በቅሎዬ ያለፍርድ የሄደች…
የስልጣን ክፍፍል

የስልጣን ክፍፍል በአገራችን ህገ መንግስታዊ መርህ ሲሆን ህግ አውጭው፤ ህግ ተርጓሚውና ህግ አስፈፃሚው ያላቸውን ስልጣን ከፋፍሎ ያስቀምጣል፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ መርህ በተቃራኒ የአስተዳደር ህግ ከተግባራዊ ምክንያቶች የተነሳ ስራ አስፈፃሚው አካል ሕግ ከማስፈፀም ስልጣኑ በተጨማሪ ህግ የማውጣትና ህግ የመተርጐም ተግባራትን እንዲያከናውን በልዩ ሁኔታ ይፈቅዳል፡፡ እነዚህ ተደራራቢ ስልጣናት የመንግስት አስተዳደርን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ በልዩ ሁኔታ የተሰጡ እንጂ በመርህ ደረጃ ከስልጣን ክፍፍል መሰረተ ሀሳብ ጋር ይጋጫሉ፡፡ ስለሆነም የህገ መንግስቱ የስልጣን ክፍፍል መርህ የአስተዳደር መስሪያ ቤቶች ደንብና መመሪያ የማውጣት እና ዳኝነታዊ ውሳኔ የመስጠት ስልጣን በአፈፃፀም ረገድ በጠባቡ እንዲተረጐም በማድረግ የዚህ ስልጣናቸው ገደብ ሆኖ ያገለግላል፡፡

ይኸው መርህ ፍርድ ቤቶች ሚናቸው እስከየት ድረስ እንደሚዘልቅ ይወስናል፡፡ መደበኛ ፍ/ቤት በህግ ተለይተው በታወቁ የምርመራ ምክንያቶች ስልጣን ካልተሰጠው በስተቀር በስልጣን ውስጥ የተፈፀመ ድርጊት ከማረም መቆጠብ ይኖርበታል፡፡ ፍ/ቤቶች በስልጣን ውስጥ የተፈፀመ ድርጊትን የሚያርሙ ከሆነ በስራ አስፈፃሚው ስልጣን ጣልቃ በመግባት የስልጣን ክፍፍል መርህን ይጥሳሉ፡፡