አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የኢትዮጵያ የህግ ምንጮች እና ተዋረድ

መግቢያ

ህጎች የተለያዩ መመዘኛዎችን መሰረት በማድረግ ሊከፋፈሉ ይችላሉ፡፡ በዚህ መሰረት “የሲቪል ሎው (civil law)” እና “የኮመን ሎው (common law)”፣ “ፐብሊክ ሎው (public law)” እና “የግል ህግ (private law)”፣ “የወንጀል ህግ” እና “የፍትሀብሄር ህግ”፣ “የስነ ስርዓት ህግ (procedural law)” እና “መሰረታዊ ህግ (substantive law) እና የመሳሰሉትን መስፈርቶች በመጠቀም ህጎችን ማከፋፈል ይቻላል፡፡ የሀገራት ህጎች በሁለት ዋና ዋና የህግ ስርዓቶች ማለትም የኮመን ሎው እና የሲቪል ሎው በሚል ይታወቃሉ፡፡ የሲቨል ሎው የህግ ስርዓት ተከታይ አገራት ፍትሀብሄርን የሚመለከት ዐብይ ህግ በአንድ ጥራዝ (codified) ታውጀው እና የወንጀል የሚመለከት ዐብይ ህግ በአንድ ጥራዝ (code) ታውጀው ይገኛሉ፡፡ እነዚህም በአገራችን አጠራር የፍትሀብሄር ህግ እና የወንጀል ህግ ተብለው ይታወቃሉ፡፡ ስለሆነም ይህን ስርዓት የሚከተሉ ሀገሮች ዋና የህግ ምንጭ በህግ አውጪ አካል ታውጀው የሚጠረዙ ህጎች ናቸው ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩል የኮመን ሎው ስርዓትን የሚከተሉ ሀገሮች ዋና የህግ ምንጫቸው በህግ አውጪ አካል የሚወጡ ህጎች ሳይሆኑ በፍርድ ቤቶች በተመሳሳይ ጉዳይ ቀደም ብለው የተሰጡ አስገዳጅ ውሳኔዎች (precedent) ናቸው፡፡ እንዲሁም ያልተፃፉ ህጎችን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡

በሀገራችንም የተለያዩ የህግ ምንጮች ያሉ ሲሆን የህጎች ተዋረድ ወይም የህግ የበላይነት ደረጃ (hierarchy of laws) በህግ ስርዓት ውስጥ ጉልህ ቦታ ካላቸው ጉዳዮች አንዱ ነው፡፡ በዚህ የንቃተ ህገ ፅሁፍ የኢትዮጵያ የህግ ምንጮችን እና የህጎቹን ተዋረድ ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

1. የኢትዮጵያ ህግ ምንጮች (sources of Ethiopian laws)
በአገራችን ህጎች በፌደራል እና በክልል ደረጃ ወጥተው ስራ ላይ ይውላሉ፡፡ እነዚህም ህጎች በፌደራል እና በክልሎች የተለያዩ ምንጮች አሏቸው፡፡

1.1. የፌደራል የህግ ምንጮች
i. ህገ መንግስት (constitution)
የኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 9 ህገ መንግስት የሀገሪቱ የበላይ ሕግ እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡ ማንኛውም ህግ ለምሳሌ አዋጅ፣ ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከሕገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ይህ ማለት ህገ መንግስት የማንኛውም ህጎች መነሻ እና ምንጭ እንዲሁም ህጋዊነታቸውን (validation) የሚያገኙበት መሰረት ነው፡፡
ii. አለም አቀፍ ስምምነቶች (international treaties)
ሀገራት አለም አቀፍ ስምምነት ሲፈርሙ ስምምነቱን እንደ አንድ አለም አቀፍ ህግ እንተቀበሉ ማስረጃ ነው፡፡ የህገ መንግስቱ አንቀፅ 9 (4) እንደሚደነግገው ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የሀገሪቱ ህግ አካል ናቸው፡፡ እነዚህ ስምምነቶች ስራ ላይ ለመዋል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቅ እና በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትመው መውጣት አለባቸው፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የአገሪቱ ህግ አካል ሆነው ተግባራዊ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡
iii. ኮዶች (codes)
በሀገራችን በ1960ዎቹ አምስት ኮዶች ተዘጋጅተው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ እነዚህም የፍትሀ ብሄር ህግ፣ የንግድ ህግ፣ የባህር ህግ በ1960፣ የወንጀል ስነ ስርዓት ህግ በ1961 እና የፍትሀ ብሄር ስነ ስርዓት ህግ በ1965 ናቸው፡፡ እነዚህም ህጎች በነጋሪት ጋዜጣ በአዋጅ መልክ ታውጀው ስራ ላይ ውለዋል፡፡ ከዚህም በኃላ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ፣ የወንጀል ህግ እና አዲሱ የንግድ ህግ በኮድ መልክ ስራ ላይ የዋሉ የአገራችን የህግ ምንጮች ናቸው፡፡
iv. አዋጅ፣ ደንብ እና መመሪያ (proclamations, regulations & directives)
አዋጆች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ደንቦች በሚኒስትሮች ምክር ቤት እና መመሪያዎች ደግሞ በፌደራል ሚኒስትሮች መስሪያ ቤቶች ወይም በሚስትሮች ምክር ቤት መመሪያ እንዲያወጡ በደንብ ውክልና በተሰጣቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ይወጣሉ፡፡ በተጨማሪም የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማወጅ ስልጣን በህገ መንግስቱ ተሰጥቶታል፡፡ እነዚህም የህግ ክፍሎች ወይም አይነቶች የአገራችን የህግ ምንጭ በመሆን የሚያገለግሉ ሲሆኑ በስራ ላይ የሚውሉበትን ሁኔታ በተመለከተ በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ ይህም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይም በሚነስትሮች ምክር ቤት ከታወጁበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ የሚውሉ ወይም በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ የሚውሉ ናቸው፡፡
v. አስገዳጅ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች (precedent)
ይህ የህግ ምንጭ አይነት ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ በተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ አስገዳጅ ወይም ህግ የሚሆንበት ስርዓት ነው፡፡ በአገራችን ፍርድ ቤቶች የሚሰጧቸው ውሳኔዎች በተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ እንደ ህግ እንደሚያገለግሉ እና አስገዳጅ እንደሆነ የሚገልፀው የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ነው፡፡ በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 10/2 ስር እንደተደነገገው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የህግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ ባለ የፌደራል እና የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት ይኖረዋል ይላል፡፡ ይህ ማለት እነዚህ ውሳኔዎች የህግ ምንጭ ሆነው ስራ ላይ ይውላሉ ማለት ነው፡፡
vi. ልማዳዊ ህጎች (customary laws)
ልማዳዊ ህጎች በኢትዮጵያ ህጎች ውስጥ በተለያየ ጊዜ እንደምንጭ ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ ለምሳሌ የፍትሀ ብሄር ህጉን ያረቀቁት ፕሮፌሰር ሬኒ ዳቪድ በረቂቁ ውስጥ የኦርቶዶክስን ልማዳዊ ህግ ‘ፍትሀ ነገስትን‘ እንደምንጭ እንደተጠቀሙበት ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም በህገ መንግስቱ አንቀፅ 34/5 ስር እንደተደነገገው የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሀይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጎች መሰረት መዳኘት እንደሚችሉ ያስቀምጣል፡፡ በመሆኑም ባህላዊ ወይም ልማዳዊ ህጎች እንደ አንድ የህግ ምንጭ ያገለግላሉ ማለት ነው፡፡

1.2. የክልል ህግ ምንጮች
i. የክልል ህገ መንግስት(state constitutions)
በኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 52/2 ስር እንደተደነገገው ክልሎች የራሳቸው ህጎች ማውጣት ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ክልሎች የራሳቸው ህገ መንግስት ከፌደራል ህገ መንግስት ጋር በሚጣጣም መልኩ አውጥተዋል እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ የክልል ህገ መንግስት በክልሎቹ ውስጥ የበላይ ህግ ነው፡፡
ii. የክልል አዋጆች (state proclamations)
የፌደራል ህገ መንግስት ክልሎች ለአስተዳደር በሚያመች መልኩ የክልሎቹን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት በማስገባት አዋጅ ማወጅ እንደሚችሉ ያስቀምጣል፡፡ በዚህ መሰረት ለምሳሌ ትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ እና የደ/ብ/ብ/ህ ክልል የራሳቸው የቤተሰብ ህግ አውጀዋል፡፡
iii. የክልል ደንቦች እና መመሪያዎች (state regulations & directives)
የፌደራል ህገ መንግስት የክልል አስፈፃሚ ምክር ቤቶች በክልል ወሰን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ እንደሚችሉ እንዲሁም ደንብ እና መመሪያዎችን ማውጣት እንደሚችሉ ስልጣን ሰጥቷቸዋል፡፡
2. የህጎች ተዋረድ (hierarchy of laws)
የህጎች ተዋረድ (hierarchy of laws) የህጎች የበላይነት ደረጃን ወይም የትኛው ህግ ከየትኛው ህግ የበላይ ህግ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ በአገራችን በህገ መንግስቱ አንቀፅ 9/1 ስር እንደተደነገገው ማንኛውም ህግ፣ ልማዳዊ ድርጊት እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት እንደማይኖረው ይደነግጋል፡፡ ይህ ማለት በሀገሪቱ ውስጥ የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ህገ መንግስቱ ነው ማለት ነው፡፡

የፌደራል ህገ መንግስት በፌደራልም ይሁን በክልል ደረጃ የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነው፡፡ በመቀጠል የአገሪቱ የበላይ የህግ አውጪ አካል ማለትም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚያወጣቸው ህጎች ማለትም አዋጆች ይከተላሉ፡፡ የአለም አቀፍ ስምምነቶችን የህግ ተዋረድ በተመለከተ ወጥ የሆነ መግባባት ባይኖርም በህገ መንግስቱ ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የአገረቱ ህግ አካል ይሆናሉ ስለሚል ከአዋጅ ጋር ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ይቀመጣሉ የሚል ሀሳብ አለ፡፡ በህግ ተዋረድ በመቀጠል የሚመጡት በሚኒስትሮች ምክር ቤት የሚወጡት ደንቦች እና በሚኒስትር መስሪያ ቤቶች የሚወጡት መመሪያዎች በቅደም ተከተል ናቸው፡፡

በሌላ በኩል በተመሳሳይ ተዋረድ (hierarchy) ላይ ባሉ ህጎች መካከል መቃረን ሲኖር ተፈፃሚ የሚሆነው በጊዜ ዘግይቶ የወጣው ህግ (latest prevails) ነው፡፡ ይህ ማለት ዘግይቶ የወጣው ቀድሞ ከወጣው ይልቅ ተፈፃሚ ይሆናል ማለት ነው፡፡ እንዲሁም ልዩ ህግ (special law) ከጠቅላላ ህግ ይልቅ ቅድሚያ ተቀባይነት (special law prevails over general law) ይኖረዋል ማለት ነው፡፡
ተቋርጦ የነበረው የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት በወረዳዎች መስጠት ጀምሯል
.
አገልግሎቱን ለማግኘትም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ከሚኖሩበት ወረዳ መታወቂያውን ለማግኘት ወደሚያመሩበት ወረዳ የመሸኛ ማሰረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡
.
በአዲስ አበባ ከተማ ተቋርጦ የሰነበተው አዲስ የነዋሪነት መታወቂያን የመስጠት አገልግሎት ከወረዳ ወረዳ በሚደረግ የመሸኛ አሰጣጥ ብቻ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚቻል ኢትዮ ኤፍ ኤም ከኤጀንሲው ሰምቷል፡፡
.
በአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገና እና መረጃ ኤጀንሲ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት አቶ መላክ መኮንን ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቁት በያዝነው ሳምንት ተቋርጦ የነበረው የመታወቂያ ምትክ እና እድሳት አገልግሎት በሁሉም ወረዳዎች አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ፡፡
.
ከዚሁ በተጨማሪ ተቋርጦ የሰነበተውና ከወረዳ ወረዳ በመሸኛ አማካኝነት ሲሰጥ የነበረው አዲስ የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት በዛሬው እለት መጀመሩን ነግረውናል፡፡
.
ይሁን እንጂ ከክልል ከተሞች የሚመጡ መሸኛዎችን በመቀበል የሚሰጠው አዲስ የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት ገና እንዳልተጀመረ የነገሩን አቶ መላክ አገልግሎቱን ከሳምንት በኋላ ለማስጀመር እየተሰራበት መሆኑን ነግረውናል፡፡
.
የውልሰው ገዝሙ
EthioFM
Forwarded from Yim.... Mi
if you have any information about 14th amhara national justice professionals trading and legal research institute exam result please inform us
LHR has organized a one and half days specialized training on Equality and Non-discrimination in Ethiopia for practising lawyers at Azzeman Hotel. This training is intended to build the capacity f lawyers in this area with a view to encourage lawyers to take cases of equality to courts and other adjudication bodies.

Day-2
On the second day, participants resume the discussion they had on the previous day on conceptual equality, International and regional instruments on equality and non-discrimination. Today the participants are having an in-depth discussion on the right to equality under the Ethiopian Federal and State constitution, Practical cases on equality brought to the House of Federation and Courts and the way forward.

#Ethiopia #HumanRight #HumanRightforLawyers #LawyersforHumanRights #LHR

https://t.me/lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
🟩 @lawsocieties
🟨 @lawsocieties
🟥 @lawsocieties
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል መሆን አለባት? የወጪ ጥቅም ትንተና
https://t.me/lawsocieties
በ፡ ይትባረክ
ከ2003 ጀምሮ ኢትዮጵያ ወደ WTO የመቀላቀል ሂደት ጀምራለች። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጥንካሬ ቢኖረውም ጠንከር ያለ ሂደቱ ረዘም ላለ ጊዜ ቆይቷል። እ.ኤ.አ. ከ2018 ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ስሜትን ለመሳብ እና ወደ WTO መውጣት የተቃረበ ይመስላል፣ ይህ ውሳኔ በእውነት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ህዝቦቿ “አሸናፊ” ይሆናል ወይ ብለን መጠየቅ አለብን። ወደ WTO መውጣት ለኢትዮጵያ ትርፋማ መሆን አለመሆኑን ለማወቅ ሶስት ዋና ዋና ነጥቦች አሉ፡- 1) የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አሁን ያለንበት ደረጃ፣ 2) የአለም ንግድ ድርጅት አባልነት ተጨባጭ ጠቀሜታዎች፣ 3) እና የአለም ንግድ ድርጅት አባልነት የሚያመጣውን ተጨባጭ ዋጋ .

አሁን ያለችው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ድብልቅና የሽግግር ኢኮኖሚ ሰፊ የህዝብ ሴክተር ያለው ነው።. ይህ ማለት የኢትዮጵያ መንግስት በተወሰኑ ኢንዱስትሪዎች ላይ የተወሰነ ቁጥጥር ያደርጋል፣ በዋናነት የባንክ፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እና የትራንስፖርት ዘርፍ እና በማዕከላዊ የታቀደ ኢኮኖሚ አለው። መንግሥት በአሁኑ ወቅት ወደ ነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ለመሸጋገር ብዙ የመንግሥት ንግዶችን ወደ ግል በማዛወር ላይ ነው ። ኢትዮጵያ በአለም ፈጣን ኢኮኖሚ እያስመዘገበች ያለች ሀገር ስትሆን ጠንካራ የሀገር ውስጥ ገበያ ያላት ከአፍሪካ በህዝብ ብዛት ሁለተኛዋ በመሆኗ ነው። ከሕዝብ ዕድገቷ ጋር ለመራመድ ኢትዮጵያ በየዓመቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሥራ ዕድል መፍጠር አለባት።

የዓለም ንግድ ድርጅትን መቀላቀል ከብዙ ጥቅሞች ጋር አብሮ ይመጣል፣ ከነዚህም አንዱ ለተጠቃሚዎች ዝቅተኛ ዋጋ ነው። ታሪፎችን ማስወገድ ሸማቾች እንዲገዙ ያስችላቸዋልርካሽ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች . ታሪፍ ከውጭ የሚገቡ ዕቃዎችን ዋጋ ይጨምራል። በዚህ ምክንያት የሀገር ውስጥ ቢዝነሶች ከውጭ አምራቾች ጋር ለመወዳደር ዋጋቸውን ለመቀነስ አይገደዱም, እና የሀገር ውስጥ ሸማቾች ለሸቀጦች ከፍተኛ ዋጋ እየከፈሉ ይገኛሉ. በኢኮኖሚያዊ ንድፈ ሀሳብ በውጭ ኩባንያዎች ላይ ታሪፍ መጣል አነስተኛ ውጤታማ የአገር ውስጥ ኩባንያዎች ከንግድ ሥራ ውጭ በሚሆኑበት ጊዜ እንዲኖሩ ያስችላቸዋል። ይህ ለአገር ውስጥ ሸማቾች እና ለውጭ አምራቾች መጥፎ ቢሆንም ለአገር ውስጥ አምራቾች እና ለአገር ውስጥ መንግሥት ጥሩ ነው። WTO ብዙ ጊዜ ከሸማች የወደፊት ታሪፍ ቅናሽ ያለውን ጥቅም እና አጠቃላይ የአለም የንግድ ደረጃን እንዴት እንደሚያሳድግ ይጠቅሳል። በእርግጥ የዓለም ንግድ ድርጅት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የዓለም ንግድ ድርጅት ከ25 በመቶ በላይ ጨምሯል።.

ነፃ ንግድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነትን ያበረታታል። ነፃ ንግድ ከጠባቂ ንግድ ፖሊሲዎች የተሻለ ነው ተብሎ የሚነገረው ለሸማቾች ብዙ ምርጫዎችን እና የኑሮ ደረጃቸውን ለማሻሻል ጥሩ እድሎችን ስለሚሰጥ ነው። ውድድርበአለም አቀፍ ደረጃም ኩባንያዎች አዳዲስ ምርቶችን እንዲፈጥሩ እና ወደ ገበያ የሚያመጡትን ምርቶች እንዲፈጥሩ ያስገድዳቸዋል, ይህም የገበያ ድርሻን ለማስጠበቅ የዋጋ ቅናሽ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው ነው. እዚህ ላይ የሚቀርበው መከራከሪያ ኢትዮጵያ ነፃ ውድድርን በመቀበል አንፃራዊ የምርት ተጠቃሚነት ያላት ዘርፎችን በመለየት በእነሱ ላይ መሻሻል ትችላለች የሚል ነው። የነጻ ውድድርም በአንዳንድ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ፈጠራን ሊያበረታታ ይችላል፣ ይህም የኢትዮጵያ መንግስት ጠቃሚ ነው ብሎ የሚመለከተው። ይህ ፈጠራ ኢንደስትሪውን በአለምአቀፍ ደረጃ እንዲወዳደር ያስገድደዋል ወይም ለመኖር ሲል የተወሰነ ቦታ እንዲቀርጽ ያስገድደዋል። አንድ ኢንዱስትሪ ተወዳዳሪ ሆኖ መቀጠል ካልቻለ እና ለአለም አቀፍ ውድድር ሲከፈት ካልተሳካ እንደ መልካም እድገት ይቆጠራል ምክንያቱም ውጤታማ ያልሆነው ኢንዱስትሪ በመንግስት እየተደገፈ ነበር ማለት ነው።

ሌላው የነፃ ንግድን ማስተዋወቅ ፋይዳ የንፅፅር ጠቀሜታ ኢኮኖሚያዊ ህግን ያካትታል ፣ይህም ነፃ ንግድ ኢኮኖሚያዊ ደህንነትን ለመጨመር ያስችላል ፣ምክንያቱም ሀገራት ዝቅተኛ የእድል ወጪን በሚያገኙበት ቦታ ሸቀጦችን በማምረት ረገድ ልዩ ችሎታ አላቸው ። እንደ ኢትዮጵያ ያለ አገር ከሙዝ ይልቅ በአንፃራዊነት የተሻለ ቡና በማምረት ላይ ከሆነ፣ ለቡና ምርት ብዙ ሀብት ማውጣቱ፣ ሙዝ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶች ክፍያ ለመክፈል የተወሰነ ቡና መላክ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ የዓለማችን ምርጡ ሙዝ አምራች ብትሆንም ይህ እውነት ሆኖ ይቆያል ምክንያቱም ንግድ ሳታካሂድ ከምትችለው የሁለቱም ምርቶች የበለጠ ስለሚኖራት ነው። ይህ ሥርዓት እንዲሠራ አገር ከምንም ነገር የተሻለ መሆን የለበትምከንግድ ተጠቃሚ ለመሆን. አንድ ሀገር በአንፃራዊነት የተሻለ በሚሰራው ስራ ላይ ብቻ ማተኮር አለበት። የዚህ ዓይነቱ ስፔሻላይዜሽን ውጤት አገሮች በአገር ውስጥ ሊቻል ከሚችለው በላይ ከፍ ያለ አጠቃላይ ምርት እና የፍጆታ ደረጃ ማግኘት መቻላቸው ነው።

በመጨረሻም፣ ነፃ ንግድ ድርጅቶች በምጣኔ ሀብት ምክንያት ልዩ እንዲሆኑ እና ከፍተኛ መጠን ያላቸውን እቃዎች እንዲያመርቱ ያበረታታል ። ይህ በዋነኝነት የሚመለከተው እንደ መኪና እና አውሮፕላን ማምረቻ በመሳሰሉት ከፍተኛ ቋሚ ወጭዎች ለሚሰቃዩ ኢንዱስትሪዎች ነው ። በልቡ የልኬት ኢኮኖሚ ማለት ከፍ ባለ የውጤት ደረጃ አነስተኛ ጉልበት እና አነስተኛ ሀብቶችን በአንድ ምርት ክፍል ይፈልጋል ማለት ነው።በትንሽ መጠን ከሚያስፈልገው በላይ. ይህም አገሮች ከኢኮኖሚ ምጣኔ ጋር በተያያዙ ዝቅተኛ ወጭዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስፔሻላይዝድ እንዲያደርጉ እና ሥራቸውን እንዲያሳድጉ ያበረታታል። ይህም የዓለምን የምርት ቅልጥፍናን በማሻሻል ዓለም አቀፍ ንግድን ይጠቅማል ። ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቷን ወደ ትላልቅ እና ምርታማ የማኑፋክቸሪንግ እና የኢንዱስትሪ ፋሲሊቲዎች በማተኮር ከምጣኔ ሀብት ተጠቃሚ መሆን ትችላለች። ይህ አሁን ካለው የመንግስት የልማት እቅድ ጋር የተጣጣመ ሲሆን ከፍተኛ የምርት መጠን እንዲኖር ያስችላል፣ የኢትዮጵያን የተመረተ ምርት የበለጠ ርካሽ ለማድረግ ያስችላል። ይህ በአንድ ዩኒት ምርት ዋጋ መቀነሱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ያደርጋታል እናም የውጭ ኢንቨስትመንት እና የንግድ እድሎችን ለመሳብ ያስችላል።

WTO እንደ ገለልተኛ ዳኛ ሆኖ ያገለግላልበአባል ሀገራት መካከል የሚነሱ የንግድ አለመግባባቶችን ለመፍታት. ባለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ በዓለም ንግድ ድርጅት ፊት የቀረቡ የንግድ አለመግባባቶች እየጨመሩ መጥተዋል፣ ይህም የዓለም ንግድ ድርጅት መሰል አለመግባባቶችን ለመፍታት እንደ መድረክ እምነት እንዳለው ያሳያል። እንደውም የዓለም ንግድ ድርጅት አለመግባባቶችን የማስፈታት ተግባር በጣም ስኬታማ ነበር።ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚሄድ በጣም ውስብስብ ጉዳዮች በፊቱ እየቀረቡ በሲስተሙ ላይ ጫና ይፈጥራሉ። ኤል.ዲ.ሲዎች በንድፈ ሀሳብ ከክርክር አፈታት ስርዓቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ ምክንያቱም ውሳኔዎቹ የሚወሰኑት በኢኮኖሚ ሃይል ሳይሆን በተቀመጡ ህጎች ላይ ነው። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በመቀላቀል ተጠቃሚ ሆናለች ምክንያቱም እንደ LDC በአጠቃላይ የንግድ ውዝግቦች በሚነሱበት ጊዜ የዓለም ንግድ ድርጅት በሚያወጣው ደንብ ትጠበቃለች። የዓለም ንግድ ድርጅት አለመግባባቶችን ለመፍታት ባለሥልጣኖችን ማነጋገር መቻሏ ኢትዮጵያ ጉዳዮቿን በትልልቅ እና በበለጸጉ አገሮች ላይ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንድትታይ ያስችላታል።
የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዛሬው እለት የካቲት 19 ቀን2014ዓ-ም ለአብክመ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኝነት ያወጣው ፈተና ይህን ይመስላል ተወያዩበት!
ኑዛዜን ለመቃወም የተቀመጠ ጊዜ ገደብ
****************************
ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን የጊዜ ገደብ በተመለከተ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በቁጥር 973 ላይ የተመለከተው ተፈጻሚ ሚሆነው ኑዛዜ ፈራሽ ነው የሚለውን ክስ ኑዛዜው ሲነገር በነበሩ ሰዎች የቀረበ እንደሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973/1/ ላይ እንደተገለጸው “ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ወይም የተወከሉ ሰዎች ኑዛዜው አይጸናም ወይም አንዱ በኑዛዜው የተነገረው ቃል አይጸናም በማለት ክስ ለማቅረብ ያላቸውን ሀሳብ መግለጫ ወይም ስለ ክፍያው በሂሳብ አጣሪው የቀረበውን የድልድል አመዳደብ ሀሳብ ለመቃወም ኑዛዜው ከተነበበት አንስቶ በሚቆጠር የአስራ አምስት ቀን ጊዜ አላቸው”፡፡
በሌላ መልኩ ደግሞ ኑዛዜው ሲነበብ ያልነበሩ ሰዎች መቃወሚያቸውን መቼ ሊቀርቡ ይችላሉ ለሚለው በፍ/ሕ/ቁ 974/1/ እና 2 ላይ የተገለጸ ሲሆን በዚህም መሰረት “ በኑዛዜ ንባብ ሥነ-ሥርዓት ላልነበሩ ወይም በኑዛዜው ንባብ ሥነ-ሥርዓት በወኪልነት ላልሰሙ ሰዎች እንዲሁም ኑዛዜው በሌሉበት የተነበበ እንደሆነ ከዚህ በላይ የተገለጸው የጊዜ ገደብ ለመቁጠር መነሻ የሚሆነው ሥለ ክፍያው ድልድልና አመዳደብ ሀሳቡን ከተነገራቸው ቀን አንስቶ ነው”፡፡
በፍ/በ/ህ/ቁ 973/2/ ላይ በተገለጸው መሰረት ኑዛዜ ከፈሰሰበት ጊዜ ከአምስት ዓመት በኋላ ወይም ኑዛዜ የሌለ እንደሆነ ሟች ከሞተ ከአምስት ዓመት በኋላ ስለ ኑዛዜው መጽናትና ስለክፍያው አመዳደብ አጣሪው ያቀረበውን የድልድል ሀሳብ በማናቸውም አስተያየት ቢሆን መቃወሚያ ሊቀርብበት አይችልም፡፡
ከዚህ በላይ ከተገለጹት የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በተያያዘ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 82585 በቅጽ 15 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ የሰጠ ሲሆን በትርጓሜውም “በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ድንጋጌዎች አቤቱታ አቅርቢው ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ ወይም የተወከለ የመሆን አለመሆን መስፈርት መሰረት በማድረግ ይርጋው መቁጠር የሚጀምርበትን ጊዜ እና ፍጹም የሆነ የይርጋ ጊዜ በቁጥር 974/2/ ከመደንገጋቸው በስተቀር ሁለቱም ድንጋጌዎች ኑዛዜው ፈራሽ ነው የሚል ክስ የሚቀርብበትን ስርዓት የሚደነግጉ በመሆቸው ተያያዥነት አላቸው በማለት ኑዛዜ መኖሩን ማወቅ እና የኑዛዜውን ሙሉ ይዘት ማወቅ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው ሲል በፍ/ብ/ህ/ቁ 973/1/ የተመለከተው የ15 ቀን ጊዜ ገደብ የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ሳይሆን የመግለጫ ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በመሆኑም ስለ ኑዛዜ መኖር እንጂ ስለድልድሉ የማያውቅ ወራሽ መግለጫ የማቅረብ ግዴታ ስለማይኖርበት ጊዜው መቁጠር የሚጀምረው በኑዛዜው የተደረገውን ድልድል ካወቁበት ቀን ጀምሮ ነው” በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
በሟች የተደረገ ኑዛዜ ከውርስ የነቀለኝ በመሆኑ ሊፍርስ ይገባል በማለት ኑዛዜው ሲነበብ በነበረ አመልካች የሚቀርብ የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 መሰረት በተገለጠው የጊዜ ገደብ ነው ወይስ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 በተገለጸው ጊዜ ውስጥ ነው? የሚለው አከራካሪ ጉዳይ በመሆኑ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 152134 በቅጽ 23 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ በውሳኔውም መሰረት በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ስለ ኑዛዜ መነበብ እንዲሁም ኑዛዜ ሲነበብ የነበሩ ሰዎች ኑዛዜው እንዲፈርስ አቤቱታ የሚያቀርቡበትን ሥርዓትና ጊዜውን በሚመለከት የሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል /ነቅሎናል/ በማለት ኑዛዜው እንዲፈርስ የሚቀርብን ወይም የቀረበ አቤቱታን የሚመለከት አይይለም፡፡ በመሆኑም ኑዛዜው ከውርስ የመንቀል ውጤት ያለው በመሆኑ እንዲፈርስ በሚል የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄ ሊታይ የሚገባው በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነውእንጂ በአንቀጽ 973 መሰረት አይደለም በማለት አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው የሕግ ትርጓሜ መሰረት ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ነው የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ አንድ ኑዛዜ ፈራሽ ነው በሚል ስለሚቀርብ መግለጫ እና እንዲሁም መግለጫው እና ክሱ ሊቀርብ ስለሚገባው የጊዜ ገደብ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 እና 974 ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 973 ተፈጻሚነት የሚኖረው ኑዛዜ ሲነበብ በነበሩ ወይም በተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ሲሆን በአንቀጽ 974 ድንጋጌ ደግሞ ተፈጻሚነቱ በኑዛዜ ሥነ-ሥርዓት ባልነበሩ ወይም ባልተወከሉ ሰዎች ጉዳይ ነው፡፡ ኑዛዜ ሲነበብ የነበረ አመልካች ኑዛዜው ከውርስ ነቅሎኛል በማለት የሚያቀርበው የክስ አቤቱታ ሊቀርብ ሚገባው በፍ/ህ/ቁ 973 መሰረት ሳይሆን በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1123 መሰረት ነው፡፡