የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ156 የስራ መደቦች በ0 ዓመት ስራ ፈላጊዎችን በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል።
የተጠቀሰውን የስራ ልምድና የማመልከቻ ነጥብ የምታሟሉ ስራ ፈላጊዎች ለ10 ተከታታይ ቀናት ተመዝገቡ ተብላችኋል!
የምዝገባ ቦታና ዝርዝር የስራ መደቦች እንደሚከተለው ተለቀዋል።
እንዲሁም በቀጣይ ዌብ ሳይት መመልከት ይቻላል።
https://www.pshrdb.gov.et/
ለሚ ኩራ ኮምኒኬሽን
የተጠቀሰውን የስራ ልምድና የማመልከቻ ነጥብ የምታሟሉ ስራ ፈላጊዎች ለ10 ተከታታይ ቀናት ተመዝገቡ ተብላችኋል!
የምዝገባ ቦታና ዝርዝር የስራ መደቦች እንደሚከተለው ተለቀዋል።
እንዲሁም በቀጣይ ዌብ ሳይት መመልከት ይቻላል።
https://www.pshrdb.gov.et/
ለሚ ኩራ ኮምኒኬሽን
Forwarded from Entrust Consult 📗ኢንትረስት
https://t.me/GudayAsfetsami
Message Guday Asfetsami on WhatsApp.
https://wa.me/message/QW6PO22A2KXBN1
https://t.me/GudayAsfetsami
Message Guday Asfetsami on WhatsApp.
https://wa.me/message/QW6PO22A2KXBN1
https://t.me/GudayAsfetsami
February 8-9 & 11-12, 2022
Training for Journalists on Hate Speech and Disinformation Prevention and Suppression Proclamation No. 1185/2020
_____
Feteh organized two rounds of training to be conducted February 8-9 and 11-12 for journalists on the Hate Speech and Disinformation Prevention and Suppression Proclamation No. 1185/2020.
The purpose of this training is to enhance journalists' understanding of the right to freedom of expression and its limitations under the law, while providing detailed understanding of hate speech, disinformation and what is set forth in the law.
#FetehActivityEt
Training for Journalists on Hate Speech and Disinformation Prevention and Suppression Proclamation No. 1185/2020
_____
Feteh organized two rounds of training to be conducted February 8-9 and 11-12 for journalists on the Hate Speech and Disinformation Prevention and Suppression Proclamation No. 1185/2020.
The purpose of this training is to enhance journalists' understanding of the right to freedom of expression and its limitations under the law, while providing detailed understanding of hate speech, disinformation and what is set forth in the law.
#FetehActivityEt
Forwarded from Entrust Consult 📗ኢንትረስት
https://t.me/GudayAsfetsami
Message Guday Asfetsami on WhatsApp.
https://wa.me/message/QW6PO22A2KXBN1
https://t.me/GudayAsfetsami
Message Guday Asfetsami on WhatsApp.
https://wa.me/message/QW6PO22A2KXBN1
https://t.me/GudayAsfetsami
Forwarded from ነገረ ፈጅ Negere Fej 📕
ተለዋጭ ቀጠሮ አሰጣጥ
**
በሌሎች ህጎች የተደነገገዉ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለዋጭ ቀጠሮ ፍላጎት መኖሩ ወይም ጥያቄዉ መቅረቡ ብቻዉን ተለዋጭ ቀጠሮ አያሰጥም፤ ነገር ግን ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት ወይም ለመከልከል የሚከተሉት ሁኔታዎች ከግንዛቤ የሚገቡ ይሆናል፡፡
1. ለተለዋጭ ቀጠሮ ምክንያት ተደርጎ የቀረበዉ ስጋት ወይም አለመመቸት በሌላ ሁኔታ መፍታት የማይቻል መሆኑን በመመዘን፤
2. የተለዋጭ ቀጠሮ ጥያቄ ከመቅረቡ በፊት ለጥያቄዉ ምክንያት የሆነዉን ነገር ለመቅረፍ ወይም ለመፍታት የተደረገ ጥረት ስለመኖሩ በማረጋገጥ፤
3. ተለዋጭ ቀጠሮ የተጠየቀበት ጉዳይ በሂደት ላይ የቆየበትን የጊዜ ርዝማኔ ከግንዛቤ በመዉሰድ፤
4. ከዚህ ቀደም ተለዋጭ ቀጠሮ ያልተጠየቀ ነጊኑ እንዲህም ተጠይቆ የተፈቀደ ወይም ያልተፈቀደ ስለ መሆኑ በመለየት፤
5. በተለዋጭ ቀጠሮ ምክንያት የጉዳዩ መጓተት በሌላዉ ባለጉዳይ ተገቢ በሆነ የጊዜ ገደብ ዉስጥ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት ላይ ተፅእኖ የማይፈጥር መሆኑን ከግምት በማስገባት፤
6. የሚሰጠዉ ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ጉዳዩ በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ ዉስጥ እልባት እንዳያገኝ ለማድረግ ያለዉን አስተዋፅኦ ከግምት በማስገባት፤
7. ከተራ ቁጥር 1-6 የተገለፁት እንደተጠቁ ሆነዉ ሌላ አሳማኝ የሆነ ምክንያት መኖሩን ዳኛ የተረዳ እንደሆነ ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ለመስጠት የሚከለክል አይሆንም፡፡
ምንጭ፡- የፌደራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 008/2013
https://t.me/NegereFej
**
በሌሎች ህጎች የተደነገገዉ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለዋጭ ቀጠሮ ፍላጎት መኖሩ ወይም ጥያቄዉ መቅረቡ ብቻዉን ተለዋጭ ቀጠሮ አያሰጥም፤ ነገር ግን ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት ወይም ለመከልከል የሚከተሉት ሁኔታዎች ከግንዛቤ የሚገቡ ይሆናል፡፡
1. ለተለዋጭ ቀጠሮ ምክንያት ተደርጎ የቀረበዉ ስጋት ወይም አለመመቸት በሌላ ሁኔታ መፍታት የማይቻል መሆኑን በመመዘን፤
2. የተለዋጭ ቀጠሮ ጥያቄ ከመቅረቡ በፊት ለጥያቄዉ ምክንያት የሆነዉን ነገር ለመቅረፍ ወይም ለመፍታት የተደረገ ጥረት ስለመኖሩ በማረጋገጥ፤
3. ተለዋጭ ቀጠሮ የተጠየቀበት ጉዳይ በሂደት ላይ የቆየበትን የጊዜ ርዝማኔ ከግንዛቤ በመዉሰድ፤
4. ከዚህ ቀደም ተለዋጭ ቀጠሮ ያልተጠየቀ ነጊኑ እንዲህም ተጠይቆ የተፈቀደ ወይም ያልተፈቀደ ስለ መሆኑ በመለየት፤
5. በተለዋጭ ቀጠሮ ምክንያት የጉዳዩ መጓተት በሌላዉ ባለጉዳይ ተገቢ በሆነ የጊዜ ገደብ ዉስጥ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት ላይ ተፅእኖ የማይፈጥር መሆኑን ከግምት በማስገባት፤
6. የሚሰጠዉ ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ጉዳዩ በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ ዉስጥ እልባት እንዳያገኝ ለማድረግ ያለዉን አስተዋፅኦ ከግምት በማስገባት፤
7. ከተራ ቁጥር 1-6 የተገለፁት እንደተጠቁ ሆነዉ ሌላ አሳማኝ የሆነ ምክንያት መኖሩን ዳኛ የተረዳ እንደሆነ ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ለመስጠት የሚከለክል አይሆንም፡፡
ምንጭ፡- የፌደራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 008/2013
https://t.me/NegereFej
Telegram
ነገረ ፈጅ Negere Fej 📕
ሕግን አለማወቅ ይቅርታን ሊያስገኝ አይችልም። የፍታብሔር ሕግ ቁጥር 2035(2)
Ignorance of the law is no excuse.
civil code article 2035(2)
ነገረ ፈጅ ከፈለጉ አለን @NegereFeji_Bot ወይም negerefej@gmail.com ይላኩልን።
Ignorance of the law is no excuse.
civil code article 2035(2)
ነገረ ፈጅ ከፈለጉ አለን @NegereFeji_Bot ወይም negerefej@gmail.com ይላኩልን።
በወንጀል ክርክር የመጀመርያ ደረጃ መቃወሚያ አቀራረብና በፍ/ቤቱ የሚሰጥ ብይን/ትእዛዝ
=========================
1. የመጀመርያ መቃወሚያ
ተከሳሹ ማንነቱ ካረጋገጠ በላ ፍ/ቤቱ ክሱን ለተከሳሹ ያነብለታል፡፡ ክሱ ግልፅ ስለመሆኑም ይጠይቀዋል፡፡ ተከሳሹ ክሱ ግልፅ መሆኑን ካረጋገጠ በላ የመጀመሪያ መቃወሚያ ካለው ይጠይቃዋል፡፡ የመጀመርያ መቃወሚያ ያለው መሆኑን ኣለመሆኑን ሳያረጋገጥ ፍ/ቤቱ የእምነት ክህደት ቃል ወደ መቀበል መሄድ የለበትም፡፡
በተከሳሹ ሊቀርብ የሚችል መቃወሚያ በሁለት መልኩ ሊታይ ይችልል፡፡ ኣንዳኛ በቁ.130 (1) እንደተመለከተው ተከሳሹ በክሱ ማመልከቻ ፎርም ወይም ይዘት ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ ነው፡፡ይህ ዓይነቱ መቃወሚያ በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.111 እና 112 የተዘረዘሩትን ነገሮች የሚመለከት ነው፡፡
(1) በቁ. 111 ላይ የተመለከቱት ነገሮች ስናይ፤ ማንኛውም የክስ ማመልከቻ፡-
ቀንና ዓመተ ምህረት የተፃፈበትና የተፈረመበት ፣
የተከሳሹ ስም የያዘ ፣
ተከሳሹ የተከሰሰበት እና የወንጀሉ መሰረታዊ ነገር ያካተተ ፣
ወንጀሉ የተፈፀመበት ጊዜና ስፍራ ያመላከተ ፣
የተበደለው ሰው ስም ወይም ወንጀሉ የተፈፀመበት ንብረት (ተገቢ በሆነ ጊዜ) የሚያመለክት፣
ተከሳሹ ወንጀሉን በመፈፀም ተላልፏል የተባለበት የሕግ ዓንቀፅ የያዘ መሆነ አለበት፡፡
(2) በቁ.112 የተመለከተው ደግሞ ተከሳሹ የተከሰሰበትን ወንጀል ለይቶ ኣውቆ መልስ ለመስጠት እንዲችል እያንዳንዱ ክስ ወንጀሉንና ሆኔታውን በዝርዝር መግለፅ እንዳለበት ነው፡፡
ስለዚህ በቁ.111 ወይም 112 ላይ ከተመለከቱት ሁኔታዎች (ነገሮች) ኣንዳንዶቹ በክሱ ማመልከቻ ላይ ያልተካተቱ ሆኖው ያገኛቸው እንደሆነ ተከሳሹ በመቃወሚያ መልክ ሊያነሳቸው እንዲሚችል ነው፡፡
ሁለተኛውና በተግባርም በተደጋጋሚ ሲነሳ የሚስተዋለው መቃወሚያ በቁ.130 (2) ላይ የተደነገገውን ነው፡፡ በዚህ ንኡስ ዓንቀፅ ስር በመቃወሚያነት ሊነሱ የሚችሉ በርከት ያሉ ምክንያቶች ተዘርዝረው የሚገኙ ሲሆን፤ ኣብዛኛዎቹ የመቃወሚያ ነጥቦች በተከሳሹ ወይም በጠበቃው ብቻ ሊነሱ የሚችሉ ናቸው፡፡ በቁ.130(2) (ሐ) መሰረት የይርጋ ጊዜን ኣስመልክቶ የሚቀርብ ተቃውሞ ግን ተከሳሹ ባያነሳወም ዓቃቤ ሕጉ ሊያነሳው ይችላላ ወይም ፍ/ቤቱ በራሱ ውሳኔ ክሱን መዝጋት ኣለበት (የወ/ሕግ ዓንቀፅ 216 (2)) ፍ/ቤቱ ሌላ ማድረግ ያለበት የተከሳሹ ፍፁም ወይም ከፊል ሃላፊነት ኣጠራጣሪ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ሁሉ ተከሳሹ ተቃውሞ ባያቀርብም ስለዚሁ ነገር ልዩ እውቀት ያለውን የአዋቂ ኣሳብ መጠየቅ ነው፡፡ ቢያስፈልግም በተከሳሹ ጠባይ ፣ ባለፈ ህይወት ታሪኩና በሁኔታዎቹ ላይ ምርመራ እንዲደረግ ትዝዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
በተለይ ተከሳሹ የኣእምሮ በሽታ ያለበት ወይም በሚጥል በሽታ የሚታወክ ለመሆኑ፤ ወይም መስማትና መናገር የሚሳነው ለመሆኑ ወይም ኣእምሮን በሚያደነዝዝ ነገር ወይም በመጠጥ አዘዉታሪነት በሽታ የተለከፈ ለመሆኑ የሚያመለክቱ ሁኔታዎች በተገኙ ጊዜ ፍ/በቱ ለዚሁ ልዩ እውቀት ያለውን ሰው ኣሳብ የመጠቅ ግዴታ ኣለበት ፡፡
(የወ/ሕግ ዓንቀፅ 51)
በመቃወሚያነት መቅረብ የሚችል ምን እንደሆነና መቃወሚያው ማንሳት ያለበት ማን እንደሆነ ካየን ዘንድ የሚቀርብበት ጊዜ መቼ ነው? የኣቀራረቡ ፎርምስ ምን መሆን ኣለበት የሚለውን ማየት ኣስፈላጊነቱ ኣጠያያቂ ኣይደለም፡፡
ተከሳሹ መቃወሚያ ካለው ማቅረብ ያለበት ክሱ ከተነበበለት በላ መሆኑን ከላይ ተገልፆዋል፡፡ ክሱ ከተነበበለት በላ ብቻ ሳይሆን መቃወሚያ ካለው ወድያው ማቅረብ አለበት፡፡ ይህ ኣባባል ታሳቢ የሚያደርገው ተከሳሹ ክሱ ከሚሰማበት ቀን ኣስቀድሞ እንዲደርሰው ስለሚደረግ ኣንብቦ ሊነሳ የሚችል መቃወሚያ ለማቅረብ ተዘጋጅቶ ይመጣል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ ክሱን ወዲያው ካልተቃወመ መቃወሚያውን በላ ማንሳት እንደማይችልም በመርህ ደረጃ በስነ ስርዓት ሕጉ ተደንግጓል (ቁ.130 (3)) ፡፡ ሆኖም ይህ ንኦስ ቁጥር መርህ ብቻ ሳይሆን የመርሁን ልዩ ሁኔታም ደንግጓል፡፡ ይኸዉም፤
“… ፍርድ ቤቱ ሲጠይቀው ተከሳሹ የክሱን ማመልከቻ ወድያው ካልተቃወመ በቀር ቆይቶ እንዲህ ያለውን መቃወሚያ ነገሩ በሚሰማበት በሌላ ጊዜ ሊያነሳ ኣይችልም፡፡ ስለሆነም መቃወም የሚችለው መቃወሚያው የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ በሆነ ጊዜ ብቻ ነው፡፡” የሚል ነው፡፡
እዚህ ላይ መነሳት የሚገባው ጥያቄ “የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ” እና ዘግይተውም ቢሆን ሊቀርቡ የሚችሉ መቃወሚያዎች የተኞቹ ናቸው? የሚል ነው፡፡ ለዚህ ጥያቂ መልስ ሊሆኑ የሚችሉ ሶስት ምሳሌዎች መጥቀስ ይቻላል፡፡
ቁ.130 (2) (ለ) ተከሳሹ በዚሁ ክስ ከዚህ ቀደም ተከሶ ነፃ የወጣ ወይም የጥፋተኝነት ውሳኔ የተሰጠበት መሆኑ ወይም
ቁ.130 (2) (ሐ) ክስ የቀረበበት ወንጀል በይርጋ ሕግ የታገደ ወይም ምሕረት ወይም የኣዋጅ ምሕረት (ይቅርታ) የተደረገለት መሆኑን ወይም
ቁ.130 (2) (ሰ) ለፈፀማቸው ተግባሮች ሃላፊ ያለመሆኑን ባመለከተ ጊዜ ነው፡፡
የመጀመሪያው ምሳሌ ብንመለከት በስነ ስርዓት ሕጉ ብቻ የተቀመጠ ሳይሆን በኢፌዴሪ ሕገ መንግስት ዓንቀፅ 23 ላይም “ማንኛዉም ሰው በወንጀል ሕግና ስነ ስርዓት መሰረት ተከሶ የመጨረሻ በሆነ ውሰኔ ጥፋተኛነቱ በተረጋገጠበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና ኣይከሰስም ወይም ኣይቀጣም” በሚል መልኩ ተገልፆ ይገኛል፡፡ በሁለተኛው ምሳሌ የተጠቀሰ ይቅርታን በተመለከተም ሕገ መንግስተዊ እውቅና ያገኘ ነው (ዓንቀፅ 71 (7)) ፡፡ እንዲሁም የይርጋ ጉዳይ በፍርድ ቤት ሳይቀር መነሳት ያለበት መቃወሚያ በመሆኑና ሃላፊ ያለመሆን ጥያቄም ኣስገዳጅ ድንጋጌ ሆኖ በወንጀል ሕግ የሰፈረ በመሆኑ ክሱ እንደተነበበ ወድያው ባይቀርቡም የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግዱ በመሆናቸው በማንኛውም ጊዜ ሊነሱ የሚችሉ መቃወሚያዎች ናቸው፡፡
የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ መቃወሚያ ሲገኝ ጊዜ ዘግይቶም ቢሆን ሊነሳ ይችላል ብሎ ሕጉ ሲያስቀምጥ ይህን ተከትሎ የሚነሳ ጥያቄ በስር ፍርድ ቤት ሳይነሳ ቀርቶ በይግባኝ ፍርድ ቤት ይግባኙ በሚታይበት ጊዜ ቢነሳስ ተቀባይነት ኣለው ወይ የሚል ይሆናል፡፡ እንግዲህ ይህ ልዩ ሁኔታ ከኣጠቃላይ የሕገ መንግስቱ መርሆዎችና ከቅጣት ዓላማ ኣንፃር መታየት ስላለበት በይግባኝ ፍርድ ቤት በሚሰማበት ወቅት የተነሳ መቃወሚያ ቢሆንም እንኳ ተቀባይነት ሊያገኝ ይገባል፡፡ የመዝገብ ቁጥሩ ማስታወስ ባልችልም በ1967 ዓ.ም አንድ ሰው የግድያ ወንጀል ፈፅሟል በሚል በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን ማእከላዊ /ከፍተኛ/ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት ጥፋተኛ ሆኖ ስለተገኘ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ይፈረድበታል፡፡ ፍርዱን በመቃወም ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባይ ያቀረበ ሲሆን የጠ/ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎትም መዝገቡ ከመረመረ በላ ክሱ በይርጋ ጊዜ የታገደ ሆኖ ስላገኘው በዞኑ ፍ/ቤት የተሰጠን የጥፋተኛነትና የቅጣት ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ይግባይኝ ባይን በነፃ እንዲለቀቅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
=========================
1. የመጀመርያ መቃወሚያ
ተከሳሹ ማንነቱ ካረጋገጠ በላ ፍ/ቤቱ ክሱን ለተከሳሹ ያነብለታል፡፡ ክሱ ግልፅ ስለመሆኑም ይጠይቀዋል፡፡ ተከሳሹ ክሱ ግልፅ መሆኑን ካረጋገጠ በላ የመጀመሪያ መቃወሚያ ካለው ይጠይቃዋል፡፡ የመጀመርያ መቃወሚያ ያለው መሆኑን ኣለመሆኑን ሳያረጋገጥ ፍ/ቤቱ የእምነት ክህደት ቃል ወደ መቀበል መሄድ የለበትም፡፡
በተከሳሹ ሊቀርብ የሚችል መቃወሚያ በሁለት መልኩ ሊታይ ይችልል፡፡ ኣንዳኛ በቁ.130 (1) እንደተመለከተው ተከሳሹ በክሱ ማመልከቻ ፎርም ወይም ይዘት ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ ነው፡፡ይህ ዓይነቱ መቃወሚያ በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.111 እና 112 የተዘረዘሩትን ነገሮች የሚመለከት ነው፡፡
(1) በቁ. 111 ላይ የተመለከቱት ነገሮች ስናይ፤ ማንኛውም የክስ ማመልከቻ፡-
ቀንና ዓመተ ምህረት የተፃፈበትና የተፈረመበት ፣
የተከሳሹ ስም የያዘ ፣
ተከሳሹ የተከሰሰበት እና የወንጀሉ መሰረታዊ ነገር ያካተተ ፣
ወንጀሉ የተፈፀመበት ጊዜና ስፍራ ያመላከተ ፣
የተበደለው ሰው ስም ወይም ወንጀሉ የተፈፀመበት ንብረት (ተገቢ በሆነ ጊዜ) የሚያመለክት፣
ተከሳሹ ወንጀሉን በመፈፀም ተላልፏል የተባለበት የሕግ ዓንቀፅ የያዘ መሆነ አለበት፡፡
(2) በቁ.112 የተመለከተው ደግሞ ተከሳሹ የተከሰሰበትን ወንጀል ለይቶ ኣውቆ መልስ ለመስጠት እንዲችል እያንዳንዱ ክስ ወንጀሉንና ሆኔታውን በዝርዝር መግለፅ እንዳለበት ነው፡፡
ስለዚህ በቁ.111 ወይም 112 ላይ ከተመለከቱት ሁኔታዎች (ነገሮች) ኣንዳንዶቹ በክሱ ማመልከቻ ላይ ያልተካተቱ ሆኖው ያገኛቸው እንደሆነ ተከሳሹ በመቃወሚያ መልክ ሊያነሳቸው እንዲሚችል ነው፡፡
ሁለተኛውና በተግባርም በተደጋጋሚ ሲነሳ የሚስተዋለው መቃወሚያ በቁ.130 (2) ላይ የተደነገገውን ነው፡፡ በዚህ ንኡስ ዓንቀፅ ስር በመቃወሚያነት ሊነሱ የሚችሉ በርከት ያሉ ምክንያቶች ተዘርዝረው የሚገኙ ሲሆን፤ ኣብዛኛዎቹ የመቃወሚያ ነጥቦች በተከሳሹ ወይም በጠበቃው ብቻ ሊነሱ የሚችሉ ናቸው፡፡ በቁ.130(2) (ሐ) መሰረት የይርጋ ጊዜን ኣስመልክቶ የሚቀርብ ተቃውሞ ግን ተከሳሹ ባያነሳወም ዓቃቤ ሕጉ ሊያነሳው ይችላላ ወይም ፍ/ቤቱ በራሱ ውሳኔ ክሱን መዝጋት ኣለበት (የወ/ሕግ ዓንቀፅ 216 (2)) ፍ/ቤቱ ሌላ ማድረግ ያለበት የተከሳሹ ፍፁም ወይም ከፊል ሃላፊነት ኣጠራጣሪ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ሁሉ ተከሳሹ ተቃውሞ ባያቀርብም ስለዚሁ ነገር ልዩ እውቀት ያለውን የአዋቂ ኣሳብ መጠየቅ ነው፡፡ ቢያስፈልግም በተከሳሹ ጠባይ ፣ ባለፈ ህይወት ታሪኩና በሁኔታዎቹ ላይ ምርመራ እንዲደረግ ትዝዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
በተለይ ተከሳሹ የኣእምሮ በሽታ ያለበት ወይም በሚጥል በሽታ የሚታወክ ለመሆኑ፤ ወይም መስማትና መናገር የሚሳነው ለመሆኑ ወይም ኣእምሮን በሚያደነዝዝ ነገር ወይም በመጠጥ አዘዉታሪነት በሽታ የተለከፈ ለመሆኑ የሚያመለክቱ ሁኔታዎች በተገኙ ጊዜ ፍ/በቱ ለዚሁ ልዩ እውቀት ያለውን ሰው ኣሳብ የመጠቅ ግዴታ ኣለበት ፡፡
(የወ/ሕግ ዓንቀፅ 51)
በመቃወሚያነት መቅረብ የሚችል ምን እንደሆነና መቃወሚያው ማንሳት ያለበት ማን እንደሆነ ካየን ዘንድ የሚቀርብበት ጊዜ መቼ ነው? የኣቀራረቡ ፎርምስ ምን መሆን ኣለበት የሚለውን ማየት ኣስፈላጊነቱ ኣጠያያቂ ኣይደለም፡፡
ተከሳሹ መቃወሚያ ካለው ማቅረብ ያለበት ክሱ ከተነበበለት በላ መሆኑን ከላይ ተገልፆዋል፡፡ ክሱ ከተነበበለት በላ ብቻ ሳይሆን መቃወሚያ ካለው ወድያው ማቅረብ አለበት፡፡ ይህ ኣባባል ታሳቢ የሚያደርገው ተከሳሹ ክሱ ከሚሰማበት ቀን ኣስቀድሞ እንዲደርሰው ስለሚደረግ ኣንብቦ ሊነሳ የሚችል መቃወሚያ ለማቅረብ ተዘጋጅቶ ይመጣል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ ክሱን ወዲያው ካልተቃወመ መቃወሚያውን በላ ማንሳት እንደማይችልም በመርህ ደረጃ በስነ ስርዓት ሕጉ ተደንግጓል (ቁ.130 (3)) ፡፡ ሆኖም ይህ ንኦስ ቁጥር መርህ ብቻ ሳይሆን የመርሁን ልዩ ሁኔታም ደንግጓል፡፡ ይኸዉም፤
“… ፍርድ ቤቱ ሲጠይቀው ተከሳሹ የክሱን ማመልከቻ ወድያው ካልተቃወመ በቀር ቆይቶ እንዲህ ያለውን መቃወሚያ ነገሩ በሚሰማበት በሌላ ጊዜ ሊያነሳ ኣይችልም፡፡ ስለሆነም መቃወም የሚችለው መቃወሚያው የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ በሆነ ጊዜ ብቻ ነው፡፡” የሚል ነው፡፡
እዚህ ላይ መነሳት የሚገባው ጥያቄ “የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ” እና ዘግይተውም ቢሆን ሊቀርቡ የሚችሉ መቃወሚያዎች የተኞቹ ናቸው? የሚል ነው፡፡ ለዚህ ጥያቂ መልስ ሊሆኑ የሚችሉ ሶስት ምሳሌዎች መጥቀስ ይቻላል፡፡
ቁ.130 (2) (ለ) ተከሳሹ በዚሁ ክስ ከዚህ ቀደም ተከሶ ነፃ የወጣ ወይም የጥፋተኝነት ውሳኔ የተሰጠበት መሆኑ ወይም
ቁ.130 (2) (ሐ) ክስ የቀረበበት ወንጀል በይርጋ ሕግ የታገደ ወይም ምሕረት ወይም የኣዋጅ ምሕረት (ይቅርታ) የተደረገለት መሆኑን ወይም
ቁ.130 (2) (ሰ) ለፈፀማቸው ተግባሮች ሃላፊ ያለመሆኑን ባመለከተ ጊዜ ነው፡፡
የመጀመሪያው ምሳሌ ብንመለከት በስነ ስርዓት ሕጉ ብቻ የተቀመጠ ሳይሆን በኢፌዴሪ ሕገ መንግስት ዓንቀፅ 23 ላይም “ማንኛዉም ሰው በወንጀል ሕግና ስነ ስርዓት መሰረት ተከሶ የመጨረሻ በሆነ ውሰኔ ጥፋተኛነቱ በተረጋገጠበት ወይም በነፃ በተለቀቀበት ወንጀል እንደገና ኣይከሰስም ወይም ኣይቀጣም” በሚል መልኩ ተገልፆ ይገኛል፡፡ በሁለተኛው ምሳሌ የተጠቀሰ ይቅርታን በተመለከተም ሕገ መንግስተዊ እውቅና ያገኘ ነው (ዓንቀፅ 71 (7)) ፡፡ እንዲሁም የይርጋ ጉዳይ በፍርድ ቤት ሳይቀር መነሳት ያለበት መቃወሚያ በመሆኑና ሃላፊ ያለመሆን ጥያቄም ኣስገዳጅ ድንጋጌ ሆኖ በወንጀል ሕግ የሰፈረ በመሆኑ ክሱ እንደተነበበ ወድያው ባይቀርቡም የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግዱ በመሆናቸው በማንኛውም ጊዜ ሊነሱ የሚችሉ መቃወሚያዎች ናቸው፡፡
የሚፀና ፍርድ ከመስጠት የሚያግድ መቃወሚያ ሲገኝ ጊዜ ዘግይቶም ቢሆን ሊነሳ ይችላል ብሎ ሕጉ ሲያስቀምጥ ይህን ተከትሎ የሚነሳ ጥያቄ በስር ፍርድ ቤት ሳይነሳ ቀርቶ በይግባኝ ፍርድ ቤት ይግባኙ በሚታይበት ጊዜ ቢነሳስ ተቀባይነት ኣለው ወይ የሚል ይሆናል፡፡ እንግዲህ ይህ ልዩ ሁኔታ ከኣጠቃላይ የሕገ መንግስቱ መርሆዎችና ከቅጣት ዓላማ ኣንፃር መታየት ስላለበት በይግባኝ ፍርድ ቤት በሚሰማበት ወቅት የተነሳ መቃወሚያ ቢሆንም እንኳ ተቀባይነት ሊያገኝ ይገባል፡፡ የመዝገብ ቁጥሩ ማስታወስ ባልችልም በ1967 ዓ.ም አንድ ሰው የግድያ ወንጀል ፈፅሟል በሚል በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን ማእከላዊ /ከፍተኛ/ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦበት ጥፋተኛ ሆኖ ስለተገኘ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ይፈረድበታል፡፡ ፍርዱን በመቃወም ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባይ ያቀረበ ሲሆን የጠ/ ፍርድ ቤት ወንጀል ችሎትም መዝገቡ ከመረመረ በላ ክሱ በይርጋ ጊዜ የታገደ ሆኖ ስላገኘው በዞኑ ፍ/ቤት የተሰጠን የጥፋተኛነትና የቅጣት ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ይግባይኝ ባይን በነፃ እንዲለቀቅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
ለ) የኣቀራረቡ ፎርም ሲታይ ደግሞ በቁ.130 (1) ወይም (2) መሰረት የሚቀርበው መቃወሚያም ሆነ ዓቃቤ ሕጉ ለመቃወሚያው የሚሰጠው መልስ ሁሉ በቃል መቅረብ እንዳለበት ከቁ.131 (1) መረዳት ይቻላል፡፡ ተደጋጋሚ ስልጠናዎች እየተሰጡ ኣሁን ኣሁን እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም በተግባር ሲሰራበት የነበረና ኣሁንም ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል ብሎ በኣስተማማኝ መናገር የማይቻለው፤ መቃወሚያ ለማቅረብ ጊዜ መስጠት ፣ መቃወሚያው በፅሑፍ ማቅረብ ፣ ዓ/ሕግ የመቃወሚያው ግልባጭ እንዲደርሰው ማድረግ ፣ ዓ/ሕግ በሚሰጠው ቀነ ቀጠሮ መልሱ በፅሑፍ ያቀርባል ፣ ተከሳሹ በበኩሉ የመልስ መልስ በፅሑፍ ለማቅረብ ጊዜ ይሰጠዋል ፣ በመጨረሻ ፍ/ቤቱ የተከሳሽ መቃወሚያና የዓ/ሕግ መልስ ከሕጉ ጋር ኣገናዝቦ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይሰጣል፤ ምናልባት ምርመራው ያላለቀ ከሆነ ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠት እንደተጠበቀ ሆኖ ፍ/ቤቱ ብይን ይሰጣል፡፡ ይህ የተንዛዛ ኣካሄድ ሕጉ ከሚያዘው ውጭ መሆኑን ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል፡፡
ሐ) ከመቃወሚያ ጋር ተያይዞ ሌላ መታየት ያለበት ነጥብ በመቃወሚያነት መቅረብ ያለበት በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ከተዘተዘሩት ምክንያቶች ሲገኝ ብቻ ነው ወይስ ከዚያ ውጭ የሆኑ ምክንያቶች ሲገኙም ማቅረብ ይፈቀደል የሚለው ነው፡፡ በዚህ ዙርያ ሁለት ኣስተሳሰቦች ይራመዳሉ፡፡ በአንድ በኩል በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ባይሸፈንም የክሱ መሰማት ሂደት እንዳይቀጥል የሚያደርጉ ሌሎቸ ምክንያቶች በተገኙ ጊዜም ተከሳሽ እንዲያነሳ ሊፈቀድለት ይገባል የሚሉ ኣሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቁ.130 ሌላ የመቃወሚያ ነጥብ በማይጨምር ሁኔታ (exclusively) ዘርዝሮ ያስቀመጠ በመሆኑ ከዚያ ውጭ የሚቀር ተቃውሞ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባም የሚል ሓሳብ የሚያራምዱ አሉ ብቻ ሳይሆን ኣብዛኛው ጊዜ በተግባር የሚሰራበትም ይህ ኣቋም ነው ፡፡ እንደ የሞጁሉ ኣዘጋጅ እምነትም በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 130 ስር የማይሸፈን የተቃውሞ ነጥብ በሚነሳበት ጊዜ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባውም፤ ምክንያቱም በዛ ስር ያልተጠቀሰ ነጥብ በማያካትት እና በተሟላ ሁኔታ (exclusively and exhaustively) የተቀረፀ ነው፡፡
2. መቃወሚያውን ስለመመርመርና ስለመወሰን
በቁ. 13. (2) መሰረት የሚቀርበውን ማንኛውንም መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ በመዝገቡ ከፃፈ በላ ዓ/ሕጉ መልስ እንዳለው ይጠይቃል፡፡ የቀረበውን መቃወሚያ ሕግን በመጥቀስ ለመወሰን የሚቻል ከሆነ ወይም ዓ/ሕጉ መቃወሚያውን ካልተቃወመ ፍ/ቤቱ ወድያው ይወስናል (ቁ. 131 (1)) ፡፡ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለማጣራት ማስረጃ መቅረቡ ኣስፈላጊ ሆኖ ካገኘውና ማስረጃ ሳይቀርብ ወድያው ውሳኔ (ብይን) መስጠት የማይቻል በሆነ ጊዜ ኣስፈላጊው ማስረጃ እንዲቀርብ ማዘዝ ይችላል (ቁ. 131 (3)) ፡፡ የተፈለገው ማስረጃ አስቀርቦ ከመረመረ በላ ፍ/ቤቱ ወዲያው ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ቁጥር 131 (4) ይደነግጋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመቃወሚያው ላይ የሚሰጠው ውሳኔ /ብይን/ እንደየ መቃወሚያው ዓይነት ሊለያይ ይችላል፡፡ ይኸዉም፡-
ሀ) የቀረበው መቃወሚያ የሕግ ድጋፍ የሌለው ከሆነ ወይም በማስጃ ካልተደገፈ መቃወሚያውን ውድቅ ያደርጋል ፣
ለ) በቁ. 130/ 2/ለ/፣ /ሐ/፣ ወይም/ሰ/ መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱን ዘግቶ ተከሳሹን ያሰናብታል ፣
ሐ) በቁ.130/2/ሀ/ መሰረት የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ጉዳዩ በተጀመረበት ፍ/ቤት እንዲቀጥል በማዘዝ መዝገቡን ይዘጋል ፣
መ) በቁ. 130(2) (መ) መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱ ተነጥሎ እንዲታይ ያዝዛል ፣
ሠ) በቁ. 130 /2/ሠ/ የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ኣስፈላጊው ፈቃድ እስኪሰጥ መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል ፣
ረ) በቁ. 130/2/ረ/ የቀረበ ከሆነ ደግሞ ኣስቀድሞ መፈፀም ያለበት ስርዓት እስኪፈፀም መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል፡፡
ከዚህ በላይ በፊደል “ለ” የተጠቀሰውን እንዳለ ሆኖ ተከሳሹ ሙሉ በሙሉ ሃላፊ ባለመሆኑ ክሱ በተዘጋ ጊዜ የተከሳሹ ሁኔታ በፀጥታ ወይም በህዝብ ሰላማዊ ኑሮ ላይ ሁከት ወይም ኣደጋ የሚያደርስ መስሎ ከታየው ተከሳሹ ተገቢ በሆነ ስፍራ ወይም ሕክምና በሚያገኝበት ቦታ ተወስኖ እንዲቀመጥ ፍ/ቤቱ ያዝዛል ( የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 208 እና የወ/ሕግ ዓንቀፅ 130 እስከ 132 ) ፡፡
via #Legal_Service
©Tsegaye Demeke
ሐ) ከመቃወሚያ ጋር ተያይዞ ሌላ መታየት ያለበት ነጥብ በመቃወሚያነት መቅረብ ያለበት በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ከተዘተዘሩት ምክንያቶች ሲገኝ ብቻ ነው ወይስ ከዚያ ውጭ የሆኑ ምክንያቶች ሲገኙም ማቅረብ ይፈቀደል የሚለው ነው፡፡ በዚህ ዙርያ ሁለት ኣስተሳሰቦች ይራመዳሉ፡፡ በአንድ በኩል በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ባይሸፈንም የክሱ መሰማት ሂደት እንዳይቀጥል የሚያደርጉ ሌሎቸ ምክንያቶች በተገኙ ጊዜም ተከሳሽ እንዲያነሳ ሊፈቀድለት ይገባል የሚሉ ኣሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቁ.130 ሌላ የመቃወሚያ ነጥብ በማይጨምር ሁኔታ (exclusively) ዘርዝሮ ያስቀመጠ በመሆኑ ከዚያ ውጭ የሚቀር ተቃውሞ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባም የሚል ሓሳብ የሚያራምዱ አሉ ብቻ ሳይሆን ኣብዛኛው ጊዜ በተግባር የሚሰራበትም ይህ ኣቋም ነው ፡፡ እንደ የሞጁሉ ኣዘጋጅ እምነትም በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 130 ስር የማይሸፈን የተቃውሞ ነጥብ በሚነሳበት ጊዜ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባውም፤ ምክንያቱም በዛ ስር ያልተጠቀሰ ነጥብ በማያካትት እና በተሟላ ሁኔታ (exclusively and exhaustively) የተቀረፀ ነው፡፡
2. መቃወሚያውን ስለመመርመርና ስለመወሰን
በቁ. 13. (2) መሰረት የሚቀርበውን ማንኛውንም መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ በመዝገቡ ከፃፈ በላ ዓ/ሕጉ መልስ እንዳለው ይጠይቃል፡፡ የቀረበውን መቃወሚያ ሕግን በመጥቀስ ለመወሰን የሚቻል ከሆነ ወይም ዓ/ሕጉ መቃወሚያውን ካልተቃወመ ፍ/ቤቱ ወድያው ይወስናል (ቁ. 131 (1)) ፡፡ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለማጣራት ማስረጃ መቅረቡ ኣስፈላጊ ሆኖ ካገኘውና ማስረጃ ሳይቀርብ ወድያው ውሳኔ (ብይን) መስጠት የማይቻል በሆነ ጊዜ ኣስፈላጊው ማስረጃ እንዲቀርብ ማዘዝ ይችላል (ቁ. 131 (3)) ፡፡ የተፈለገው ማስረጃ አስቀርቦ ከመረመረ በላ ፍ/ቤቱ ወዲያው ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ቁጥር 131 (4) ይደነግጋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመቃወሚያው ላይ የሚሰጠው ውሳኔ /ብይን/ እንደየ መቃወሚያው ዓይነት ሊለያይ ይችላል፡፡ ይኸዉም፡-
ሀ) የቀረበው መቃወሚያ የሕግ ድጋፍ የሌለው ከሆነ ወይም በማስጃ ካልተደገፈ መቃወሚያውን ውድቅ ያደርጋል ፣
ለ) በቁ. 130/ 2/ለ/፣ /ሐ/፣ ወይም/ሰ/ መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱን ዘግቶ ተከሳሹን ያሰናብታል ፣
ሐ) በቁ.130/2/ሀ/ መሰረት የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ጉዳዩ በተጀመረበት ፍ/ቤት እንዲቀጥል በማዘዝ መዝገቡን ይዘጋል ፣
መ) በቁ. 130(2) (መ) መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱ ተነጥሎ እንዲታይ ያዝዛል ፣
ሠ) በቁ. 130 /2/ሠ/ የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ኣስፈላጊው ፈቃድ እስኪሰጥ መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል ፣
ረ) በቁ. 130/2/ረ/ የቀረበ ከሆነ ደግሞ ኣስቀድሞ መፈፀም ያለበት ስርዓት እስኪፈፀም መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል፡፡
ከዚህ በላይ በፊደል “ለ” የተጠቀሰውን እንዳለ ሆኖ ተከሳሹ ሙሉ በሙሉ ሃላፊ ባለመሆኑ ክሱ በተዘጋ ጊዜ የተከሳሹ ሁኔታ በፀጥታ ወይም በህዝብ ሰላማዊ ኑሮ ላይ ሁከት ወይም ኣደጋ የሚያደርስ መስሎ ከታየው ተከሳሹ ተገቢ በሆነ ስፍራ ወይም ሕክምና በሚያገኝበት ቦታ ተወስኖ እንዲቀመጥ ፍ/ቤቱ ያዝዛል ( የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 208 እና የወ/ሕግ ዓንቀፅ 130 እስከ 132 ) ፡፡
via #Legal_Service
©Tsegaye Demeke
ውል ማለት ምን ማለት ነው ? የዉል አመሠራረት ሲባልስ በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል?
***
ሰላም እንዴትናችሁ ውድ የፌስቡክ ገጻችን ተከታታዮች ለዛሬ ውል ሲባል ምን ማለት ነው? የዉል አመሠራረት ሲባልስ በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አንድ የጹሁፍ ጥንቅር ወደ እናንተ ልናደርስ ወደድን መልካም ንባብ ተመኘን፡፡
የሰዉ ልጆች በዚች ምድር ላይ ሲኖሩ የተለያዩ ህጋዊ ውጤት ያላቸዉን ድርጊቶች ያከናዉናሉ፡፡ ለአብነትም ቤት ይከራያሉ ያከራያሉ፣ ጋብቻ ይፈፅማሉ፣ ንብረት ይሸጣሉ ይገዛሉ፣ ወዘተ፡፡ ህጋዊ ዉጤትም ከሚያስከትሉ ተግባራት አንዱ ውል ነዉ፡፡ ውል ሰዎች በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሕይወታቸዉ ዉስጥ ከሚያከናውኗቸው የግንኙነት መገለጫዎች አንዱ ሲሆን ከፍትሐብሔር ግዴታ አንዱ ዘርፍ ነው፡፡
ሰዎች በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴያቸዉ ዉስጥ የተለያዩ ውሎችን ይፈፅማሉ፡፡ ወደ ሱቅ ሂደዉ ሸቀጥ ሲገዙ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ ታክሲ ሲጠቀሙ፣ ለንግድም ሆነ ለመኖሪያ ቤት ሲከራዩ፣ ወዘተ፡፡ እኒህ የውል ግዴታ ዉስጥ የሚገቡት የማህበረሰቡ አካል የሆኑ ሰዎች ናቸዉ፡፡ በሌላ አባባል ውል የሚኖረዉ የውል ግዴታ ውስጥ የሚገቡ (የሚዋዋሉ) ሰዎች ሲኖሩ ነዉ፡፡ ሰዎች ስንል በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ህጋዊ ሰዉነት የተሰጣቸው ድርጅቶች ናቸዉ፡፡ ውድ አንባቢያን ለመግቢያ ያክል ይህን ካልን አሁን ደግሞ የውልን ትርጓሜ እናያለን
ውል ማለት ምን ማለት ነው
ውል ምን ማለት ነዉ? የሚለዉን ስንመለከት የዘርፉ ሙሁራን እና የፍትሐብሔር ህጋችን የተቀራረበ ትርጉም ሰጥተውት እናገኛለኝ፡፡ በእዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ ላይ “ዉል ማለት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸዉ አንድን ድርጊት ለማድረግ ወይንም ላለማድርግ በመስማማት ግዴታ የሚፈጥሩበት መንገድ ነዉ” ሲል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ ፕሮፌስር ጥላሁን ተሾመ የኢትዮጳያ የዉል ህግ መሰረተ ሀሳቦች በሚለዉ መፅሃፋቸዉ ዉስጥ “ዉል አንድን ግዴታ ወይም ከዚሁ ግዴታ የተያያዙ ሌሎች በርከት ያሉ ግዴታዎችን የሚያቋቁም ተግባርን የሚያመለክት አነጋገር ነዉ፡፡ በዚህ ግዴታ ባለገንዘብ የሆነዉ ወገን አንድ ነገር እንዲፈጸምለት የመጠየቅ መብት የሚኖረዉ ሲሆን ባለዕዳዉ ደግሞ አንድን ነገር የመፈጸም ግዴታ ይጠበቅበታል” በማለት አብራርተዉ ገልፀዉታል፡፡ እንዲሁም በፍትሐብሔር ህጋችን መፅሃፍ አምስት ስለ ግዴታዎች በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡
የዉል አመሠራረት
ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ስምምነት ነዉ፡፡ ነገር ግን ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ ለአፈፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡ ይህም ማለት ተዋዋይ ወገኖች የተስማሙበትን ነገር እንደ ስምምነታቸዉ ባይፈፅሙ ያልፈፀሙትን ነገር በህግ ተገደዉ እንዲፈፅሙ ይደረጋሉ፡፡ ይህም የሚያሳየን ዉል በተስማሚዎቹ አካላት መካከል እንደ ህግ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ነዉ፡፡
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ስለ ዉል አመሰራረት በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን ሁኔታዎች አስቀምጧል፡፡ እነሱም፡
1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑን፡፡ ይህም ማለት በህግ ፊት የሚፀና ዉል ለማድረግ ተዋዋዮች በህግ ችሎታ ያላቸዉ መሆን አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ላይ ስለ ችሎታ በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 192 ላይ በመርህ ደረጃ ማንኛዉም ሰዉ በህግ ችሎታ እንደሌለዉ ካልተገለፀ በቀር ማንኛዉንም ህጋዊ ድረጊት ለማድረግ ችሎታ እንዳለዉ እንደሚቆጠር ተደንግጓል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀፅ 193 ላይ እንደተደነገገዉ እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡ ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ህጋዊ ተግባር ነዉ ስለሆነም እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ዉል መዋዋል አይችልም፡፡
2ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ መሆኑ፡፡ ይህም ማለት ተወያይ ወገኖች ዉል ዉስጥ የሚገቡት ያለማንም ጫና አድራጊነት በራሳቸዉ ፍቃድ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡ አንድ የዉል ግዴታ የተቋቋመ መሆኑ የሚረጋገጠዉ የተዋዋዮቹ ፈቃድ በህግ አግባብ መገለፁ ሲታወቅ ነዉ፡፡ ተዋዋዮቹ በመሀከላቸዉ በህግ ፊት የሚፀና ግዴታ ለማቋቋምና ይህም ግዴታ በሚያስከትለዉ ዉጤት ለመገዛት ስምምነት ያላቸዉ መሆኑ ይፋ ሲያደርጉ ፈቃዳቸዉን ገለፁ እንላለን፡፡ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀፅ 1679 ላይ ይህን አባባላችን በሚያጠናክር መልኩ “ዉል ተዋዋዮች በገቡባቸዉ ግዴታዎችና እነዚህም አስገዳጅ እንዲሆኑ የተስሚ መብትን በሚገልፀዉ የፈቃድ መስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ” በማለት ተደንግጓል፡፡
3ኛ. ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት (ዉል ዉስጥ የሚገቡበት) ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆኑ፡፡ የዉሉ ፍሬ ነገር በሰዉ ልጅ አቅም መፈጸም የሚችል እና ህጋዊና ሞራላዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ በሰዉ ልጅ አቅም መፈፀም የሚቻል ተግባር ማለት የሰዉ ልጅ በተፈጥሮዉ ማከናዉን የሚችለዉ ማለት ነዉ፡፡ ለአብነት የዉሉ ፍሬ ነገር እንደ እርግብ መብረር ቢሆን በሰዉ ልጅ ተፈጥሮ የማይቻል ተግባር ነዉ፡፡ ሌለዉ የዉሉ ፍሬ ነገር በህግ ያልተከለከለ ወይም ህገ-ወጥ እና በህብረተሰቡ ባህልና ወግ ተቀባይነት ያለዉ ነገር ላይ (በሌላ አባባል ከህብረተሰቡ ሞራል ጋር ያልተቃረነ ያልሆነ) መሆን አለበት፡፡ ለአብነት ፍሬ ነገሩ ሰዉ ለመግደል ቢሆን በህግ የተከለከለ ነዉ፡፡
4ኛ. የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ በህግ (ፎርም) ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጡ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም የማያስፈልግ መሆኑ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678(3) ላይ እንደተደነገገዉ በግልፅ በህግ ይህን የዉል ፎርም ተከተሉ ተብሎ ካልተደነገገ በቀር ተዋዋይ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት አይነት ማድረግ ይችላሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚሁ ህግ አንቀፅ 1719(1) ላይ ተዋዋይ ወገኖች የመዋዋል ነፃነት እንዳላቸዉ ሁሉ የሚዋዋሉበትን ዉል አቀራረፅ የመወሰን ነፃነትም እንዳለቸዉ በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በተለየ ሁኔታ በህግ ዉሉ በዚህ መልክ ይቀመጥ ካልተባለ በስተቀር ተዋዋዮቹ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት ፎርም ማድረግ ይችላሉ፡፡
ውድ አንባቢያን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁን በዚሁ አበቃን በቀጣይ የቤት ኪራይ ውል ሲባል ምን ማለት ነው በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አርዕስት አንድ ጥንቅር ከትበን ወደ እናንተ እናደርሳለን እስክንገናኝ መልካም ጊዜ ተመኝን ሰላም፡፡
https://t.me/lawsocieties
***
ሰላም እንዴትናችሁ ውድ የፌስቡክ ገጻችን ተከታታዮች ለዛሬ ውል ሲባል ምን ማለት ነው? የዉል አመሠራረት ሲባልስ በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አንድ የጹሁፍ ጥንቅር ወደ እናንተ ልናደርስ ወደድን መልካም ንባብ ተመኘን፡፡
የሰዉ ልጆች በዚች ምድር ላይ ሲኖሩ የተለያዩ ህጋዊ ውጤት ያላቸዉን ድርጊቶች ያከናዉናሉ፡፡ ለአብነትም ቤት ይከራያሉ ያከራያሉ፣ ጋብቻ ይፈፅማሉ፣ ንብረት ይሸጣሉ ይገዛሉ፣ ወዘተ፡፡ ህጋዊ ዉጤትም ከሚያስከትሉ ተግባራት አንዱ ውል ነዉ፡፡ ውል ሰዎች በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሕይወታቸዉ ዉስጥ ከሚያከናውኗቸው የግንኙነት መገለጫዎች አንዱ ሲሆን ከፍትሐብሔር ግዴታ አንዱ ዘርፍ ነው፡፡
ሰዎች በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴያቸዉ ዉስጥ የተለያዩ ውሎችን ይፈፅማሉ፡፡ ወደ ሱቅ ሂደዉ ሸቀጥ ሲገዙ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ ታክሲ ሲጠቀሙ፣ ለንግድም ሆነ ለመኖሪያ ቤት ሲከራዩ፣ ወዘተ፡፡ እኒህ የውል ግዴታ ዉስጥ የሚገቡት የማህበረሰቡ አካል የሆኑ ሰዎች ናቸዉ፡፡ በሌላ አባባል ውል የሚኖረዉ የውል ግዴታ ውስጥ የሚገቡ (የሚዋዋሉ) ሰዎች ሲኖሩ ነዉ፡፡ ሰዎች ስንል በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ህጋዊ ሰዉነት የተሰጣቸው ድርጅቶች ናቸዉ፡፡ ውድ አንባቢያን ለመግቢያ ያክል ይህን ካልን አሁን ደግሞ የውልን ትርጓሜ እናያለን
ውል ማለት ምን ማለት ነው
ውል ምን ማለት ነዉ? የሚለዉን ስንመለከት የዘርፉ ሙሁራን እና የፍትሐብሔር ህጋችን የተቀራረበ ትርጉም ሰጥተውት እናገኛለኝ፡፡ በእዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ ላይ “ዉል ማለት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸዉ አንድን ድርጊት ለማድረግ ወይንም ላለማድርግ በመስማማት ግዴታ የሚፈጥሩበት መንገድ ነዉ” ሲል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ ፕሮፌስር ጥላሁን ተሾመ የኢትዮጳያ የዉል ህግ መሰረተ ሀሳቦች በሚለዉ መፅሃፋቸዉ ዉስጥ “ዉል አንድን ግዴታ ወይም ከዚሁ ግዴታ የተያያዙ ሌሎች በርከት ያሉ ግዴታዎችን የሚያቋቁም ተግባርን የሚያመለክት አነጋገር ነዉ፡፡ በዚህ ግዴታ ባለገንዘብ የሆነዉ ወገን አንድ ነገር እንዲፈጸምለት የመጠየቅ መብት የሚኖረዉ ሲሆን ባለዕዳዉ ደግሞ አንድን ነገር የመፈጸም ግዴታ ይጠበቅበታል” በማለት አብራርተዉ ገልፀዉታል፡፡ እንዲሁም በፍትሐብሔር ህጋችን መፅሃፍ አምስት ስለ ግዴታዎች በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡
የዉል አመሠራረት
ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ስምምነት ነዉ፡፡ ነገር ግን ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ ለአፈፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡ ይህም ማለት ተዋዋይ ወገኖች የተስማሙበትን ነገር እንደ ስምምነታቸዉ ባይፈፅሙ ያልፈፀሙትን ነገር በህግ ተገደዉ እንዲፈፅሙ ይደረጋሉ፡፡ ይህም የሚያሳየን ዉል በተስማሚዎቹ አካላት መካከል እንደ ህግ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ነዉ፡፡
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ስለ ዉል አመሰራረት በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን ሁኔታዎች አስቀምጧል፡፡ እነሱም፡
1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑን፡፡ ይህም ማለት በህግ ፊት የሚፀና ዉል ለማድረግ ተዋዋዮች በህግ ችሎታ ያላቸዉ መሆን አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ላይ ስለ ችሎታ በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 192 ላይ በመርህ ደረጃ ማንኛዉም ሰዉ በህግ ችሎታ እንደሌለዉ ካልተገለፀ በቀር ማንኛዉንም ህጋዊ ድረጊት ለማድረግ ችሎታ እንዳለዉ እንደሚቆጠር ተደንግጓል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀፅ 193 ላይ እንደተደነገገዉ እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡ ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ህጋዊ ተግባር ነዉ ስለሆነም እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ዉል መዋዋል አይችልም፡፡
2ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ መሆኑ፡፡ ይህም ማለት ተወያይ ወገኖች ዉል ዉስጥ የሚገቡት ያለማንም ጫና አድራጊነት በራሳቸዉ ፍቃድ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡ አንድ የዉል ግዴታ የተቋቋመ መሆኑ የሚረጋገጠዉ የተዋዋዮቹ ፈቃድ በህግ አግባብ መገለፁ ሲታወቅ ነዉ፡፡ ተዋዋዮቹ በመሀከላቸዉ በህግ ፊት የሚፀና ግዴታ ለማቋቋምና ይህም ግዴታ በሚያስከትለዉ ዉጤት ለመገዛት ስምምነት ያላቸዉ መሆኑ ይፋ ሲያደርጉ ፈቃዳቸዉን ገለፁ እንላለን፡፡ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀፅ 1679 ላይ ይህን አባባላችን በሚያጠናክር መልኩ “ዉል ተዋዋዮች በገቡባቸዉ ግዴታዎችና እነዚህም አስገዳጅ እንዲሆኑ የተስሚ መብትን በሚገልፀዉ የፈቃድ መስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ” በማለት ተደንግጓል፡፡
3ኛ. ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት (ዉል ዉስጥ የሚገቡበት) ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆኑ፡፡ የዉሉ ፍሬ ነገር በሰዉ ልጅ አቅም መፈጸም የሚችል እና ህጋዊና ሞራላዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ በሰዉ ልጅ አቅም መፈፀም የሚቻል ተግባር ማለት የሰዉ ልጅ በተፈጥሮዉ ማከናዉን የሚችለዉ ማለት ነዉ፡፡ ለአብነት የዉሉ ፍሬ ነገር እንደ እርግብ መብረር ቢሆን በሰዉ ልጅ ተፈጥሮ የማይቻል ተግባር ነዉ፡፡ ሌለዉ የዉሉ ፍሬ ነገር በህግ ያልተከለከለ ወይም ህገ-ወጥ እና በህብረተሰቡ ባህልና ወግ ተቀባይነት ያለዉ ነገር ላይ (በሌላ አባባል ከህብረተሰቡ ሞራል ጋር ያልተቃረነ ያልሆነ) መሆን አለበት፡፡ ለአብነት ፍሬ ነገሩ ሰዉ ለመግደል ቢሆን በህግ የተከለከለ ነዉ፡፡
4ኛ. የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ በህግ (ፎርም) ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጡ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም የማያስፈልግ መሆኑ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678(3) ላይ እንደተደነገገዉ በግልፅ በህግ ይህን የዉል ፎርም ተከተሉ ተብሎ ካልተደነገገ በቀር ተዋዋይ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት አይነት ማድረግ ይችላሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚሁ ህግ አንቀፅ 1719(1) ላይ ተዋዋይ ወገኖች የመዋዋል ነፃነት እንዳላቸዉ ሁሉ የሚዋዋሉበትን ዉል አቀራረፅ የመወሰን ነፃነትም እንዳለቸዉ በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በተለየ ሁኔታ በህግ ዉሉ በዚህ መልክ ይቀመጥ ካልተባለ በስተቀር ተዋዋዮቹ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት ፎርም ማድረግ ይችላሉ፡፡
ውድ አንባቢያን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁን በዚሁ አበቃን በቀጣይ የቤት ኪራይ ውል ሲባል ምን ማለት ነው በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አርዕስት አንድ ጥንቅር ከትበን ወደ እናንተ እናደርሳለን እስክንገናኝ መልካም ጊዜ ተመኝን ሰላም፡፡
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/