አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በንግድ ሕጉ

(በላይሁን ይርጋ)

1. መግቢያ
በአዋጅ ቁጥር 1243/2013 መሰረት የፀደቀው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንግድ ሕግ መሰረታዊ ለውጥ ካመጣባቸው የህጉ ክፍል መካከል መፀሀፍ ሁለት የንግድ ማህበርን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች ይገኙበታል፡፡ በበፊቱ የንግድ ሕግ ውስጥ ከተካተቱት ስድስት የንግድ ማህበራት አይነቶች መካከል ተራ የሽርክና ማኅብር በመባል የሚታወቀው እና ከአንጽፅ 227 እስከ 270 ባሉት ድንጋጌዎች ሥር የተመለከተው የንግድ ማኅበር የሚቋቋምበት ዋና ዓላማ የንግድ ሥራ ለመሥራት አለመሆኑ በግልፅ የተደነገገ ሲሆን በተግባርም በሥራ ላይ ውሎ የማይገኝ በመሆኑ ከሕጉ እንዲወጣ የተደረገ ሲሆን በምትኩ ሁለት አዳዲስ የንግድ ማኅበር ዓይነቶችን አካቶ በጠቅላላ ሰባት የንግድ ማህበር አይነቶችን ይዞ መጥቷል፡፡

በሕጉ እንደ አዲስ ከተካተቱት ሁለት የንግድ ማህበር አይነቶች መካከል አንዱ ኃላፊነቱ የተወሰነ የሽርክና ማኅበር /Limited Liability Partnership LLP/ በመባል የሚታወቀው አንዱ ሲሆን ይህ ዓይነቱ የሽርክና ማኅበር ሁለት ወይም ከዛ በላይ የሆኑ ሰዎች የሙያ ለሙያ ደጋፊ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት የሚያቋቁሙት የማኅበር አይነት ነው ። ሌላው በተቀረው ዓለም እየተለመደ የመጣው አዲስ አደረጃጀት ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት (One Man Company) ሲሆን በዚች አነስተኛ ፅሁፍ ስለዚሀ ማህበር ባህርያትና መሰል ጉዳዮች ዘርዘር አድርገነ ለማየት እንሞክራለን።
..............
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በንግድ ሕጉ
...........#ከላይ #የቀጠለ........

2. የባለ አንድ አባል ኃለፊነቱ የተወሰነ የንግድ ማህበር አስፈላጊነት
በአገራችን የንግድ ሕግ መሠረት የንግድ ማህበር ወይም ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስፈልገው ዝቅተኛ የአባላት ቁጥር ቢያንስ ሁለት መሆን ይኖርበታል ፡፡ ነገር ግን ይህ መስፈርት የንግድ ማኅበራት ከሚቋቋሙበት ዓላማ፤ አሁን አገሪቱ ከምትከተለው ነጻ የገበያ ሥርዓትና በወቅቱ ተቀባይት እያገኘ ከመጣው ዓለም አቀፍ የንግድ አሠራር ልምድ ጋር በሚከተሉት ምክንያቶች የሚጣጣም አይደለም፡፡ የመጀመሪያው ባለሀብቶች በንግድ ማኅበር ተደራጅተው እንዲሠሩ የተደረገበት ዋናው ዓላማ ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሀኒቱ በሚለው ብሂል የንግድ ሥራው የሚያስፈልገውን አዋጭ የንግድ ሐሳብና ካፒታል በጋራ አመንጭተው ወደ ንግድ ሥራ ቢገቡ ውጤታማ ይሆናሉ በሚል እሳቤ ነው፡፡ የንግድ ሕጉ በወጣበት በ1952 ዓ.ም በሀገሪቱ ያሉ ባለሀብቶች ያላቸው የካፒታል መጠን ብቻቸውን ማህበር ለመመስረት የሚያስችላቸው አይደለም የሚል አስተሳሰብ ስለነበረና በተጨባጭም በወቅቱ የነበረው የካሽ ገንዘብ እንቅስቃሴ አነስተኛ ስለነበረ ህጉ ይህ ታሳቢ አድርጎ እንደወጣ መረዳት ይቻላል፡፡ በመሆኑም ይህ አስተሳብ ሕጉ በወጣበት ዘመን ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በቂ የንግድ ሐሳብና ካፒታል ያላቸው ባለሀብቶች ከፍላጎታቸው ውጭ ከሌሎች ጋር የግድ እንዲጣመሩ ማስገደዱ ባለሀብቶች በነጻነት በመረጡት የንግድ መስክ ተሠማርተው ራሳቸውንም ሆነ አገራቸውን እንዳይጠቅሙ እንቅፋት ይፈጥራል፡፡

አሁን በተግባር እየታየ እንዳለው የሕጉን አነስተኛ የአባላት ቁጥር ግዴታ ለማሟላት እና ሌላ ሰው በሚያቋቁመው የንግድ ኩባንያ ውስጥ ላለማስገባት ሲሉ ምንም የንግድ ሐሳብም ሆነ የገንዘብ አስተዋጽኦ ያላደረጉ የቤተሰብ አባላትንና ሌሎች የቅርብ ሰዎቻቸውን አባል አያደረጉ ማህበር ይመሰርታሉ፡፡ ይህም በአንድ በኩል ምንም አስተዋጽኦ የሌላቸውን ሰዎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ሰዎች የተመሠረቱ ኃላፊነታቸው የተወሰነ የግል ኩባንያዎች አባላት ቁጥር በተለያየ ምክንያት ለምሳሌ ያህል በባለትዳሮች፣ በቤተ ዘመዳሞችና በጓኛሞች ወዘተ መካከል አለመግባባት ሲፈጠር አንዱ አባል ከማኅበሩ የሚወጣበት ሁኔታ ሲከሰት ኩባንያው ውጤታማ ቢሆንም በህጉ በአንድ አባል መቀጠል ስለማይቻል እንዲፈርስ ይደረጋል ፡፡ ግለሰብ ባለሀብቶች ከፍላጎታቸው ውጭ ከሌሎች ሰዎች ጋር የንግድ ማኅበር እንዲያቋቁሙ መገደዳቸው የሚያስከትለው ሌላው ችግር የንግድ ማኅበር ከሌላ ሰው ጋር ላለማቋቋም ሲሉ ወደ ግል ንግድ እንዲያተኩሩ አድርጓል፡፡ ለዚህም ማስረጃ የሚሆነው በአገራችን ከኩባንያዎች ቁጥር ይልቅ የግለሰብ ንግድ ከፍተኛውን ቁጥርና የገበያ ድርሻ ይዞ ይገኛል ፡፡ ይህ አሠራር የተለያዩ ችግሮችን ማስከተሉ ይነገራል፡፡ አንደኛ ለንግድ ሥራ የሚመድቡትን ሀብት ከግል ንብረታቸው ነጥለው በኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ለማስተዳደር የሚኖራቸውን ዕድል የሚዘጋ ነው፡፡ ሁለተኛው በኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ አቋቁመው ከኩባንያው በላይ የሚመጣ ዕዳን ወደ ግል ሀብታቸው እንዳይተላለፍ የሚገድበውን ዕድል ያሳጣል፣ በዚህም የተነሣ በዕዳ እንዳይጠየቁ ንብረታቸውን የሚያሸሹበት ሁኔታ ስለሚፈጥር ሕገ ወጥነትንን ያበረታታል፡፡

ሌላው ችግር በግላቸው ኩባንያ መሥርተው ከጊዜ በኋላ የኩባንያውን ዕድገትና ውጤት እያዩ ሌሎች ግለሰቦችን በመሳብ ተጨማሪ ካፒታል እንዳያሰባስቡና የንግዱን ሥራ ለማስፋፋት ጥረት እንዳያደርጉ እንቅፋት ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህም በአገራችን የንግድ ኩባንያዎች እንዳይስፋፉ ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከመንግሥት ቁጥጥር አኳያም ሲታይ ከኃላፊነታቸው የተወሰኑ የግል ኩባንያዎች በተለየ ሁኔታ የግለሰብ ንግድ የተደራጀ አመራርና የኦዲት እንዲሁም ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ ስላልተጣለባቸው አሠራራቸው ሕግን የተከተለ ለመሆኑ መንግሥት ለማረጋገጥ የሚያስችልበት ሁኔታ በጣም የጠበበ ነው፡፡

አንድ ሰው ብቻውን ኩባንያ እንዲያቋቋም መፍቀዱ የተለያዩ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ በአንድ ሰው ብቻ ኩባንያ እንዲያቋቋም መፈቀዱ ወደፊት የሚቋቋሙትን ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ተቋቁመው በተለያዩ ምንያቶች የአባላቱ ቁጥር ወደ አንድ ዝቅ በማለቱ ብቻ በሕጉ አንቀጽ 511 መሠረት እንዲፈርሱ የሚደረጉትን ከመፍረስ ይታደጋቸዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ባለሀብቶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ለማቋቋም የሕጉን ግዴታ ለማሟላት ሲሉ ብቻ ከማይፈልጉት ባለሀብት ጋር የሚጣመሩበትን ዕድል ይቀንሳል፡፡ ሦስተኛ ባላሀብቶች ከግለሰብ ንግድ ይልቅ ኩባንያ እንዲያቋቁሙ ስለሚያደርግ የኩባንያዎች ዕድገት በአገሪቱ እንዲጨምር ሊያደርግ ይችላል፡፡ አራተኛ ባለሀቶች ኩባያዎችን ሲያቋቁሙ መንግሥት ተገቢውን ቁጥጥር ለማድረግ አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡

በመሆኑም እነዚህን ጉዳዮች ታሳቢ በማድረግ አዲሱ የንግድ ሕግ ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንደ አንድ የንግድ ማህር አይነት እውቅና የሰጠበት ሁኔታ አለ፡፡
3. የማህበሩ ምንነት እና የተጠያቂነት ስርዓት

ባለ አንድ አባል ኀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ማለት አንድ ሰው በግሉ በሚሰጠው መግለጫ መሠረት የተቋቋመ የንግድ ማኅበር ነው ሲሆን ማኅበሩ ከአባሉ የተለየና የተነጠለ የራሱ የሕግ ሰውነት ያለው ነው ፡፡ ይህ ማለት አንድ ሰው ብቻ የሚመሰርተው የንግድ ማሀበር ሲሆን ይህ ማህበር ኃላፊነቱ ከተወሰነ የግል ማኅበር (private limited company) ጋር እጅግ ተመሳሳይ ነው። ከተጠያቂነትም አንቀፅር አባሉ ወይም መስራቹ የራሱን መዋጮ ሙሉ በሙሉ እስከ ከፈለ ድረስ ማኅበሩ ላይ ለሚፈለገው ዕዳ በግሉ ተጠያቂ አይሆንም ፡፡ የማህበሩ ባህርይ ኃላፊነቱ የተወሰነ በመሆኑ ማለትም የሚመጣ ተጠያቂነት በማህበሩ ሀብት ላይ ብቻ የተገደ በመሆኑ አባሉ ኃላፊነቱን ከተወጣ ማለትም መዋጮውን ሙሉ በሙሉ እና በወቅቱ እሰከከፈለ ድረስ ኃላፊነት የለበትም ማለት ነው፡፡

ከላይ እንደተመለከትነው ይህ ማህበር በአንድ ሰው የሚመሰረት በመሆኑ የምስረታ እና የአስተዳደር ስርዓቱ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ነው፡፡ ስለዚህ በመርህ ደረጃ አባሉ መዋጮውን በወቅቱ ከከፈል ለሚመጣው ተጠያቂነት በግሉ ኃላፊነት የለበትም ቢባልም፣ ተጠያቂ የሚሆንባቸው ሁኔታዎች ግን አሉ፡አባሉ ማኅበሩን፣ ወይም የማኅበሩን ገንዘብ ጠያቂዎች ጉዳት ላይ የሚጥል ህገ-ወጥ ድርጊት ሆን ብሎ ከፈፀመ፤ የባለ አንድ አባል ማኅበር ንብረትን ከራሱ ንብረት ጋር ከቀላቀለ፤ የባለ አንድ አባል ማኅበርን እና የራሱን ማንነት ካልነጣጠለ፤ ስለ ማኅበሩ የፋይናንስ አቋም የማኅበሩን ገንዘብ ጠያቂዎች ሊያሳስት የሚችል መረጃ ሆን ብሎ ካወጣ፤ ያለ ተመጣጣኝ ክፍያ የማኅበሩን ሀብት ለራሱ ወይም ለሶስተኛ ወገኞች የግል ጥቅም ካዋለ፤ በሕግ ሊከፈል ከሚችለው በላይ የትርፍ ክፍያ ከፈጸመ፤ ወይም ሌሎች ተመሳሳይ ተግባራትን ከፈጸመ ማንኛውም ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር አባል ወይም ማኅበሩ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ቁጥጥር ያለው ሌላ ሰው ከማኅበሩ ጋር በአንድነት እና በተናጠል ተጠያቂ እንደሚሆን ህጉ በግልፅ ደንግጓል ፡፡
እንደሚታወቀው ኃላፊነታቸው የተወሰኑ ኩባንያዎች ዋነኛ ባህርይ ዕዳቸው በኩባንያው ሀብት ላይ የተወሰነና ወደ አባላቱ ሀብት የማይሸጋገር መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የቁጥጥር ሥርዓቱ ደካማ ከሆነ የኩባንያው ብቸኛ ባለሀብት መሆኑን በመጠቀም በዕዳ ከመጠየቅ ለመሸሽ ሲባል የኩባንያውን ሀብት ወደ ግል ሀብት የማሸሽ አጋጣሚን ሊያሰፋ ይችላል፡፡ በተጨማሪም የኩባንያ መረጃዎች በአንድ ሰው ቁጥጥር ሥር ያሉ በመሆኑ በሦስተኛ ወገኖች ሊተላለፉና ሊታወቁ የሚገቡ መረጃዎች እንዳይታወቁ ሊደረግ የሚችልበት ዕድል ሊኖር ይችላል የሚል ሥጋት ያለ በመሆኑ ነው እንዲህ አይነት የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት ያስፈለገው፡፡

4. የማህበሩ አመሰራረት
እንደሌሎች ማህበሮች ሁሉ ባለ አንድ አባል ኃለፊነቱ የተወሰነ የንግድ ማህበር የሚቋቋመው በመመስረቻ ጽሑፍ ሲሆን በንግድ መዝገብ ውስጥ እንደተመገዘበ የህግ ሰውነት የሚያገኝ ሲሆን ፣ ማህበሩን ለመመስረት ዝቅተኛ ዋና ገንዘቡ ከብር 15,000 (አሥራ አምስት ሺ) ማነስ የለበትም ፡፡ ከላይ እንደተመለከተው ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሚመሰረተው አንድ ሰው በግሉ በሚሰጠው መግለጫ መሠረት ሲሆን አባሉ የሚሰጠው መግለጫ ሰነዶችን ለማረጋገጥ ሥልጣን በተሰጠው አካል ፊት መደረግና መግልጫውም በንግድ መዝገብ ውስጥ መግባት ያለበት ሲሆን መግለጫው የሚከተሉትን ነገሮች ማሳየት አለበት ማኅበሩ አንድ አባል ብቻ ያለው መሆኑን፤ የአባሉን ስም፤ዜግነትና አድራሻ፤ አባሉ የሞተ፣ የጠፋ ወይም በፍርድ የተከለከለ እንደሆነ ስለ ወራሾቹ ወይም ስለ አባሉ ሆኖ ሕጋዊ ተግባራትን እንዲፈጽም የታጨው የንብረት ጠባቂ ሰው ስም፤ ዕጩ ንብረት ጠባቂው ፍቃደኛ ሆኖ ኃላፊነቱን የተቀበለ መሆኑን፤ የማኅበሩን ስም፤ዋና መሥሪያ ቤት፤ ካሉትም ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶቹን፤ የማኅበሩን የንግድ ዓላማ፤ የማኅበሩ ዋና ገንዘብ መጠንና፤ይኼው በሙሉ የተከፈለ መሆኑን የሚያሳይ መግለጫ፤ በዓይነት የተከፈለ መዋጮ ካለ ግምቱን፤ የሥራ አስኪያጁን ስምና ሥልጣን፤ ካለ ኦዲተሩን፤ ማኅበሩ የሚቆይበትን ጊዜ፤ ማኅበሩ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የሚያስታውቅበተን መንገድና ጊዜ እና ሌሎች በሕግ ወይም በአባሉ እንዲካተቱ የተወሰኑ ጉዳዮችን ፡፡

ሌላው የምስረታው አካል የሆነው ጉዳይ እጩ ንብረት ጠባቂን በተመለከተ ነው፡፡ የማህበሩ አባል ወይም መስራች አንድ ሰው በመሆኑ ግለሰቡ በተለያዩ ምክንያቶች ስራውን መስራት ባይችል በህግ በግልፅ የተመለከተ አባሉን ተtክቶ የሚሰራ ሰው ከሌለ የንብረት ብክነትና መሰል ችግሮች ሊከሰቱ ስለሚችሉ በሶስተኛ ወገኖች ላይ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ባለአንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር በአንድ ሰው የሚመሰረት በመሆኑ አመራሩን በተመለከተ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ከላይ ተመልክተናል፡፡ ስለሆነም አባሉ በሌለ ጊዜ፣ ቢሞት፣ ቢጠፋ ወዘተ ለማህበሩ ሀላፊነት የሚወስድ ወይም የማህበሩን ንብረት የሚጠብቅ አካል ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም በህጉ ዕጩ ንብረት ጠባቂ የሚባል አካል ወይም ሰው እንዲኖር አስገዳጅ ድንጋጌ የገባ ሲሆን ዕጩ ንብረት ጠባቂው ዕጩነቱን የተቀበለ መሆኑን ሰነዶችን ለማረጋገጥ ሥልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካላረጋገጠ በስተቀር፤ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሊመሠረት አይችልም እንዲሁም አንድ ሰው በአንድ ጊዜ ለተለያዩ ባለ አንድ አባል ኃላፊነታቸው የተወሰነ የግል ማኅበራት የንብረት ጠባቂ ሆኖ መመረጥ አይችልም ፡፡
የንግድ ስራዎች በግለሰብ ነጋዴነት ከሚሰሩ ይልቅ በማህበርነት መሰራታቸው ለነጋዴውም ለሶስተኛ ወገኖችም የተሻለ ጥበቃ ስለሚሰጥ ግለሰብ ነጋዴዎች ወደ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር መለወጥ ስለሚችሉበት ሁኔታም በህጉ ተመልክቷል፡፡ በዚሁ መሰረት ግለሰብ ነጋዴ የንግድ ሥራውን ወደ ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርነት መለወጥ ይችላል፤ ሆኖም ግን ግለሰብ ነጋዴው ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ከመመሥረቱ በፊት ለገባበት ዕዳ ሁሉ ከማኅበሩ ጋር በአንድነት እና በተናጠል ኃላፊ ይሆናል ፡፡
5. የማህበሩ አመራር (Governance)
ባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲኖረው ሕጉ የሚያስገድድ ሲሆን አባሉ ራሱ ወይም ሌላ ሰው የማኅበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊሆን ይችላል ፤ ዋናው ሥራ አስኪያጁም አንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሥራ አስኪያጅ ያለው ሥልጣን እና ተጠያቂነት ይኖረዋል ፡፡ እንዲሁም ማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ የሚኖረው ሲሆን፣ የማኅበሩ አባል የአንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር አባላት ጠቅላላ ጉባዔ ያለውን ሥልጣን ይኖረዋል፤ አባሉ በጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣኑ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ቃለ-ጉባዔ ስብሰባው በተደረገ ከሦስት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በጽሑፍ ተዘጋጅተው የማህበሩ ማህደር ውስጥ መቀመጥ ይኖርባቸዋል፤ በማኅበሩ ምሥረታ ጊዜ በተሰጠ መግለጫ ውስጥ የተካተቱትን ነገሮች የሚለውጥ ማንኛውም ውሳኔ ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በንግድ መዝገብ ውስጥ መግባት አለበት እንዲሁም የአባሉ ውሳኔዎች የዚህን አንቀጽ ድንጋጌዎች ያላሟሉ ቢሆኑ እንኳን በሕግ ፊት የጸኑ ናቸው፤ ሆኖም ጉድለቱ በሦስተኛ ወገኖች ላይ ለሚያደርሰው ጉዳት አባሉና ማኅበሩ በአንድነት እና በተናጠል ተጠያቂ ይሆናሉ ፡፡

6. የማህበሩ መፍረስ
ማህበሩ እንደአግባብነታቸው በንግድ ሕጉ ጠቅላላ ክፍል የተመለከቱት ለማህበራት መፍረሻ ምክንያቶች በሚያገጥሙበት ጊዜ ሊፈርስ የሚችል ሲሆን የፈረሰው ማህበር አባል ያለበትን ዕዳ በሙሉ የከፈለ ከሆነ የማኅበሩ ሀብት ሳይጣራና ባለበት ሁኔታ በጠቅላላው ለአባሉ ይተላለፋል ፤ ምክንያቱም ማህበራት ሲፈርሱ ኦዲት የሚደረጉት በሁለት ምክንያች ሲሆን አንደኛው የማህበራትን አባላት መበት ለመጠበቀ ነው፣ ሁለተኛው ደግሞ የሶስተኛ ወገኖችን መብት ለመጠበቅ ነው፡፡ በባለ አንድ አባል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ግን አባሉ አንድ ስለሆነ የአባላጥ ጥቅም የሚባለ ነገር የማይነሳ ሲሆን፣ ሶስተኛ ወገኖችን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚለው ነጥብ ደግሞ እዳ እንደሌለበት መረጋገጥ እንዳለበት ህጉ ያስቀምጣል፣ ሆኖም በማናቸውም ምክንያት ማኅበሩ ከፈረሰ በኋላ ገንዘብ ጠያቂዎች የቀረቡ እንደሆነ አባሉ በግሉ ተጠያቂ ይሆናል፡፡ አባሉን ተጠያቂ ለማድረግ የሚቀርብ ክስ ገንዘብ ጠያቂው የማኅበሩን መፍረስ ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ በአምስት ዓመት ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል፤ የማኅበሩ ሀብት ለአባሉ ከተላለፈ ከአሥር ዓመት በኋላ ምንም ዓይነት ክስ ሊቀርብ አይችልም ፡፡ ማህበሩ በሚፈርስበት ጊዜ አባሉ አባሉ በራሱ ምርጫ መደበኛውን የሒሳብ ማጣራት ሂደት ለመከተል ይችላል ፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
ከወቅታዊ ሀገራዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተገናኘ መረጃና ጥቆማዎችን ለፖሊስ ለማድረስ እና የፖሊስ አገልግሎት ቢያስፈልጎት በ816 ወይም 991 በነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል 24 ሰዓት አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ::
Terms of Reference /ToR/ to Legal Service Officer

Ethiopian Charities and Societies Forum (ECSF)
Addis Ababa

Job Description ABOUT THE ECSF The Ethiopian Civil Society Organizations Forum (ECSF has been established as a non-partisan, independent, inclusive and voluntary national platform with a focus on the common concerns and challenges of the Civil Society sector in Ethiopia. The Forum's operational scope is at federal and regional levels with a focus on legal, institutional and operational issues and processes that commonly concerned the civil society sector in Ethiopia. The various Networks and Consortia of Civil Society organizations (named as 'Civil Society Organizations' in the recently ratified Proclamation No. 1113/2019) operating at Federal and Regional level thus came together and established the) ECSF in May 2013. Vision ECSF envisions seeing a strong and vibrant civil society sector for sustainable development. Mission ECSF aspires to ensure the existence of enabling environment for civil society organizations sector through strong representation, constructive dialogue and partnership using consortiums and other legal establishments as platform for action. ABOUT THE PROJECT • Title of the project: Request for Applications (RFA) 1/2020 to improve citizen engagement in the legal and judicial reforms in Ethiopia • Implementing partner: Ethiopian Civil Society Organization's Forum /ECSF/ • Funding Partner: Feteh (Justice) Activity • Objectives of the project: Overall Objective: The project is aimed to enhance the ability of civil society organizations (CSOs) engagement in the legal and judicial reforms process. • Reports to: Program Manger JOB SUMMARY Under the supervision of the Program Manager, the Legal Services Officer (LSO) will coordinate the work of the ECSF legal works and facilitate project specific activities. He/she will play a leading role in both long-term strategic planning processes as well as in short-term project planning. The LSO will provide key legal expertise, including by analyzing and promoting media laws which are in conformity with the both international and national litigation, research and writing, training, policy development and standard-setting, campaigning and monitoring new developments. The LSO will be directly responsible for the implementation of one or more projects. Major Duties and Responsibilities Organizational Aspects: • Advise the executives and employees on changes to the laws affecting ECSF. • Review and advise management on legal implications of internal policies and procedures. Review and provide legal advice on Memorandum of Understanding [MOUs], Contract management, and tender documents preparations. • Review internal policies and ensure that they are in compliance with all statutory or legal requirements in Ethiopia. • Be actively engaged in the (i) strengthening networks of CSOs representing women, youth and/or PWD, (ii) Monitoring draft legislation for compliance with the rights of women, youth & PWD, (iii) Developing comprehensive report on overview of the proclamations/regulations enacted during the project's term, (iv) developing MoU for the key activities executed with other stakeholders, • Take active role in the facilitation of discussion forums/events/forum/workshop in cooperation and consultation with relevant organs, such as Federal Attorney General Office, ACSO, HoPR, DI, relevant CSOs etc • Review ongoing cases and advice management accordingly. Oversee lawsuits, possibly acting as chief litigator. • Communicate with relevant departments to ensure that where legal risks have been identified, appropriate courses of action have been taken. • Provide legal protection and risk management advice to management especially on contract management. • Provide and interpret legal information, conduct training and disseminate appropriate legal requirements to staff. • Review progress of outstanding litigation issues.
• Formulate legal compliance check-lists for all the countries to be used for the purpose of ensuring that all information required is provided accordingly. • Continuously monitor compliance with statutory obligations in the countries and advise the ECSF management accordingly.
• Prepare monthly and quarterly reports for the department for executive management meetings.
• Other tasks may be assigned as necessary according to organizational needs. Project Aspects:
• Support implementation of project activities as directed by the program Manager, based on approved work plan(s), budgeting, and other relevant framework;
• Provide input into the annual work plan drafting process;
• Contribute to regular programmatic reports to donors including monthly and quarterly performance reports;
• Contribute regularly to monitoring & evaluation data collection;
• Maintain crucial project documents which track project progress, file all project documents in an appropriate database, ensure that all documents are accurate and have been accepted by supervisor; • Identify any potential issues or risks that could affect the progression of the project, communicate these items with supervisor, and work to identify potential solutions;
• Closely monitor the project schedule, monitoring deadlines for each project task, raise potential delays with the Project Manager;
• Maintain and develop productive working relationships with partner organizations;
• Other duties as assigned. Job Requirements Profile, Required Qualifications and Skills
• First degree in Law (LLB), Master's degree is a plus.
• 3 -5 years of experience in providing legal services to civil society organizations in Ethiopia. Experience with international NGOs is a plus.
• Demonstrate knowledge of and experience with laws dealing with civil societies in Ethiopia.
• Experience working on USAID-funded programs, preferred
• In-depth knowledge of regulatory laws (both national and International).
• Excellent communication, negotiation and diplomatic skills.
• Excellent command of English.
• Proficiency in Word, Power point, Outlook and Excel
• Real interest to work in civil society environment.
• Demonstrated ability to draft memos, analysis and manuals in Amharic and English;
• Experience working on research, analysis or content work in the law or related field
. • Demonstrated professional experience and knowledge in election administration preferred;
How to Apply
Interested applicants can submit their CV and Application letter within 7 working days to the Ethiopian Civil Society Organizations Forum /ECSF/ Office in Addis Ababa: Bole Sub-City, Around 22 Mazoriya, 100 mt from Awraris Hotel to the West, Next to Oasis Apartment Hotel; P. O. Box: 1270 code 100; E-mail: , , Website: . For any further information about this announcement, call @ 0912852814 or 0912375041

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
ክፍት የስራ ማስታወቂያ ለህግ ባለሞያዎች

ከሰኞ ህዳር 20 ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት የስራ ቀናት ማስረጃችሁን በተጠቀሰው አድራሻ በማስገባት መወዳደር ትችላላችሁ

#risetothetop #bottledwater #topwater #betop #Ethiopia #topforareason #jobopportunity #vacancies #addisababa

🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የሲቪል ህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የሰላምና ልማት ማዕከል የምዝገባ ፈቃድ ሰረዘ።

በባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ጂማ ዲልበ ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚገልፀው የድርጅቱ ፍቃድ የተሰረዘው የአሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ባሳለፈው ውሳኔ ነው።

ፈቃዱ ስለተሰረዘበት ምክንያት በደብዳቤው ላይ እንደሚከተለው ሰፍሯል፦

"በአገር ህልውናና ሉዓላዊነት ላይ የተደቀነን አደጋ ለመከላከል በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንቀፅ 4 ንዑስ አንቀፅ 9 መሰረት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ የአገርን ህልውናና ሉዓላዊነት እንዲሁም የሰላማዊ ዜጎችን ለመጠበቅ አስፈላጊ ነው ብሎ ሲያምን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሽብር ቡድኖች የሞራልም ሆነ የቁሳቁስ ድጋፍ ያደርጋል ብሎ የሚጠረጥረውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ፈቃድ እንዲሰረዝ ሊያዝ ይችላል ተብሎ ተደንግጓል።

በዚህም መሰረት ከላይ የተጠቀሰው (የሰላም እና ልማት ማዕከል) ድርጅት ፈቃድ እንዲሰረዝ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ ውሳኔ ያሳለፈ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር በቁጥር ፍ/ሚ-01/ባሰ-9/500773 ሕዳር 17/2014 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አሳውቋል።

በዚሁም መሰረት የሰላምና ልማት ማዕከል የተባለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት የምዝገባ የምስክር ወረቀት (ፈቃድ) ከዛሬ ህዳር 17 ጀምሮ የተሰርዟል"

ባለስልጣን መ/ቤቱ የሲ/ማ/ድ/ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አግባብነው ካለው አካል ጋር በመቀናጀት አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ የድርጅቱን ንብረት እንዲረከብ ትዕዛዝ መተላለፉም በደብዳቤው ላይ ተገልጿል።

ድርጅቱ ከሰሞኑን በፕ/ር ኤፍሬም መሪነት ከህወሓት ጋር ግንኝኑት ያላቸው አምባሳደር ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ጨምሮ፣ እነዶ/ር እሌኒ ገ/መድህንና ሌሎች የውጭ ዜጎች የተካፈሉበት የኦንላይን ውይይት አዘጋጅቶ ነበር።
vi #tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ ለቀጣይ 3 ወራት የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ማስለቀቅ ተከለከለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ቢሮ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ፤" ያለንበት ወቅት አገርን ከተጋረጠባት የህልዉና አደጋ የማዳን በመሆኑ ውሳኔውን ለቀጣይ ሶስት ወራት ባለበት እንዲጸና ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል" ብሏል።

በመሆኑም ከሕዳር 17 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሶስት ወራት የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ማስለቀቅ ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን ገልጿል።

የከተማ አስተዳደሩ ከዚህ ቀደም ለሶስት ወረት የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከተከራየበት ቤት ማስለቀቅ እንደማይቻል ውሳኔ ማተላለፉ ይታወሳል።

የአል ዐይን
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
4_5810203540093667932.pdf
1.7 MB
Share '4_5810203540093667932.pdf'
ብሔራዊ ባንክ የብድር ክልከላውን ሙሉ በሙሉ አነሳ

ለባለፉት አራት ወራት ተግባራዊ የነበረው የብድር ክልከላ ሙሉ በሙሉ መነሳቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ አስታወ።

ብሔራዊ ባንክ ባንኮች ብድር አገልግሎት ለሁሉም ደንበኞቻቸው እንዲሰጡ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ሪፖርተር ከምንጮቹ አረጋግጧል።

ክልከላው የተጣለው "የኢኮኖሚ አሻጥርን" ለመከላከል እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ተግባራዊ ተድርጎ የነበረው በትይዩ እና በህጋዊ የውጭ ምንዛሬ ግብይት ላይ ያለው ልዩነት መስፋቱን ተከትሎ ነበር።

Reporter
21 በሳይንስ የተረጋገጡ የማር ጥቅሞች

1.አለርጂን ይከላከላል
2.ሀይል ይሰጣል
3.የማስታወስ ችሎታን ይጨምራል
4.ሳልን ይከላከላል
5.የዕንቅልፍ እጦትን ያስወግዳል
6.ፎሮፎርን ይከላከላል
7. ቁስልና በቃጠሎ የተጎዳ የሰውነት ክፍል በፍጥነት እንዲያገግም ያደርጋል
8.በሰውነት ላይ የሚወጣን ሽፍታ ያስወግዳል
9.የቆዳ ድርቀትን ይከላከላል
10.የጨጓራ አሲድ ሾልኮ ወደ ሌላ አካል እንዳይሄድ ይከላከላል።
11.የሰውነት የበሽታ መከላከል አቅምን ይጨምራል
12.ካንሰርን ይከላከላል።
13.ሀንግኦቨርን ወይም የዞረድምርን ይከላከላል
14.ብጉርን ያጠፋል።
15.ስንፈተ-ወሲብን ይከላከላል
16.ሳይነስና ከሳይነስ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ህመሞች ይከላከላል።
17. የፈንገስ ኢንፌክሽንን ለማከም ያስችላል
18.የድድ ህመምን ለማከም ያገለግላል
19.የሰውነት የቆዳ መቆጥቆጥ ህመምን ያስወግዳል
20.ኮሌስትሮልን ይከላከላል።
21.ምርጥ የተፈጥሮ ማጣፈጫ ነው፡፡
═══════❁✿❁ ═══════
📚📚🗞🗞 ጠቃሚና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ሊንክ በመጫን ውድ የኛ ቤተሰብ ይሁኑ ። ቴሌግራም ቻናላችን👇
https://t.me/lawsocieties
HUJL_Call_For_Papers_2022.pdf
291.2 KB
Share 'HUJL_Call_For_Papers_2022.pdf'
Dear Colleague,
Hawassa University Journal of Law (HUJL) is now accepting submissions for its Volume VI in the form of peer-reviewed articles, notes/reflections, book reviews and comments for publication in July 2022. (Flyer attached to this email)
THE JOURNAL INVITES ENTRIES IN THE FOLLOWING CATEGORIES

Ø  Articles: 4000 – 12000 words

Ø  Comments: 1000 – 4000 words

Ø  Book Reviews: 1000 – 3000 words

Ø  Notes/Reflections: 3000 – 5000 words

All entries, except for book reviews, must be accompanied by an abstract of a maximum of 200 words and a list of keywords. 
LANGUAGE OF PUBLICATION
* The Journal accepts and publishes contributions in English and Amharic. 

* Contributions in Amharic shall be accompanied by an English abstract.
All interested contributors can submit their scholarly work at Hawassa University Journal of Law website (https://journals.hu.edu.et/hu-journals/index.php/hujl). In order to make the online submission, authors need to first register with the journal. If already registered, authors can simply log in and begin the five-step process. HUJL recommends that you review the About the Journal page for the journal's section policies, as well as the Author Guidelines before making your online submissions. Interested contributors can be provided with detailed submission guidance upon request. Please email us of your queries at hujl.editorial@gmail.com or hu.journaloflaw@hu.edu.et
Submission Deadline: January 30, 2022
Please feel free circulate this call with your networks as well
With Kind Regards
The HUJL Team