አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት፣ መገልገል እና የወንጀል ተጠያቂነት
1. ሀሰተኛ ሰነድ እና አይነቱ
ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሀገርን ኢኮኖሚ እንዲሁም የዜጎችን መብትና ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ የወንጀል ተግባር ነው፡፡ ሀሰተኛ ሰነዶች ዝግጅት በረቀቀና እውነተኛውን በሚመስል መንገድ የሚፈፀም በመሆኑ ይህን ከባድ ወንጀል ለመከላከልና አጥፊዎችን ለመቅጣት ብሎም ህብረተሰቡ ከዚህ ወንጀል እራሱን እንዲጠብቅ ግንዛቤ መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱ በመንግስታዊና ህዝባዊ ድርጅቶች ሰነዶች ላይ የሚፈፀም ከሆነ በሙስና ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው፡፡ መንግስታዊ ሰነድ ሲባል የሚኒስቴር መስሪያ ቤት ወይም የክልል ቢሮዎችና በየደረጃው ያሉ አስተዳደር መስሪያ ቤቶች የወጡ በማስመሰል የሚዘጋጅ ሲሆን ለምሳሌ የንግድ ወይም ኢንቨስትመንት ፈቃድ ወረቀቶች፣ የይለፍ ወረቀቶች፣ የብቃት ማረጋገጫዎች፣ የስራ ፈቃድ ወረቀቶች፣ የስራ ልምድ፣ የክፍያ ማዘዣዎች፣ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ወይም ሊብሬዎች፣ ወዘተ የሚያካትት ነው፡፡ የህዝባዊ ድርጅቶች ሰነድ ደግሞ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወይም ተቋማት ሰነዶች ለምሳሌ የመጋዘን ደረሰኝ፣ የእቃ ማውጫ ፈቃድ፣ የትምህርት ማስረጃ፣ የባንክ ክፍያ ሰነዶች እና መሰል በእነዚህ ተቋማት የሚሰጡ ሰነዶችን የሚመለከት ነው፡፡ እነዚህን ሰነዶች ማዘጋጀትና መገልገል የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነት ከዚህ እንደሚከተለው በዝርዝር ይቀርባል፡፡

2. ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት፣ መገልገል እና የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት
ማንኛውም ሰው የሌላውን ሰው መብት ወይም ጥቅም ለመጉዳት ወይም ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ተገቢ ያልሆነ ማናቸውም መብት ወይም ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ አንድ ፅሁፍ፣ መዝገብ ወይም ማንኛውም ሰነድ የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት በማስመሰል ያዘጋጀ ወይም የፈጠረ፤ በመንግስት ወይም በህዝባዊ ድርጅት መዝገብ፣ ፅሁፍ ወይም ሰነድ የሰፈረን እውነተኛውን ፅሁፍ በመለወጥ ወይም በመደለዝ፣ በሀሰተኛ ፊርማ፣ በእጅ በተደረገ ምልክት ወይም በጣት ፊርማ፣ በማህተም ወይም የሌለውን ስልጣን ወይም ችሎታ እንዳለው አስመስሎ በመፈረም ሀሰተኛ ሰነድ የፈጠረ እንደሆነ፤ አንድን የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰነድ በተለይ የፈራሚውን ስም ወይም ፊርማ ወይም የሰነዱን ይዘት፣ አሃዝ፣ ፍሬ ነገር ወይም ዝርዝር መግለጫ በሙሉ ወይም በከፊል በመለወጥ፣ በማሻሻል፣ በመቀነስ ወይም በመጨመር ወይም በማጥፋት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም ማናቸውንም ሀሰተኛ ፍሬ ነገር ያስገባ ወይም እንዲገባ ያደረገ እንደሆነ በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 23 መሰረት ከሶስት አመት እስከ አስር አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ያስቀጣል፡፡
በተጨማሪም የዚህ ወንጀል አፈፃፀም በሚከተለው ሁኔታ ሊከብድ የሚችል ሲሆን ይኽውም ሰነዶቹን እንዲያዘጋጅ፣ እንዲመዘግብ እንዲጠብቅ ወይም ከነዚሁ ውስጥ ቅጂዎችን እንዲሰጥ ሀላፊነት በተሰጠው የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ እንደሆነ ወይም ሰነዱን በመገልገል የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት ወይም በግለሰብ፣ በመንግስት ወይም በህዝባ ድርጅት ወይም በህዝብ ጥቅም ላይ ያደረሰው ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ ቅጣቱ ከአምስት አመት እስከ ሀያ አምስት አመት የሚደርስ እስራት ያስቀጣል፡፡

ሌላው መገንዘብ የሚገባን ጉዳይ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 23 (4) መሰረት በወንጀል የሚያስጠይቀው ሀሰተኛ ሰነዶችን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ይዞ መገኘትና መገልገል ጭምር ሲሆን በዚህም መሰረት ወደ ሀሰት የተለወጠ ወይም በሀሰት የተዘጋጀ ሰነድ በቤቱ፣ በተሽከርካሪው፣ በኪሱ ወይም በማንኛውም አግባብ በቁጥጥሩ ስር የተገኘ እንደሆነ ከላይ በተጠቀሰው ቅጣት ጋር ተመሳሳይ በሆነ ይቀጣል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም ሰው ወደ ሀሰት በተለወጠ ወይም በሀሰት በተዘጋጀ ሰነድ እያወቀ የተገለገለበት እንደሆነ በተመሳሳይ ይቀጣል፡፡

በሉላ በኩል ከግብር አከፋፈል ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሰው ሆን ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ለገቢዎች ሚኒስቴር የተጭበረበሩ ሰነዶችን ያቀረበ በፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 118 መሰረት ከሶስት እስከ አስራ አምስት አመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል፡፡ በአንቀፅ 119 መሰረት ደግሞ እነዚህን የተጭበረበሩ ደረሰኞችን ያዘጋጀ፣ ያተመ፣ የሸጠ ወይም ያሰራጨ ወይም የተጠቀመ ከሰባት አመት እስከ አስር አመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል፡፡ የዚህን ወንጀል አፈፃፀም ለመከላከል ሲባል የተደነገገ ሌላ ጥፋት ሀሰተኛ ደረሰኞችን ለመስራት፣ ለማዘጋጀት ወይም ለማተም የሚያገለግል ማሽን፣ መሳሪያ ወይም ሶፍትዌር የያዘ፣ የሸጠ፣ ያከራየ ወይም በሌላ መንገድ ያቀረበ ማንኛውም ሰው ከአስር እስከ አስራ አምስት አመት እስራት እንደሚቀጣ በህጉ መደንገጉ ነው፡፡ በተመሳሳይ እነዚህን ሀሰተኛ ደረሰኞችን የያዘ፣ ያስቀመጠ፣ ለሽያጭ ያመቻቸ ወይ ሀሰተኛ ደረሰኞችን ጥቅም ላይ እንዲውሉ ያደረገ ከሶስት እስከ አምስት አመት እስራት ይቀጣል፡፡

ከጉምሩክ መንግስታዊ ስራዎች ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሰው በጉምሩክ ኮሚሽን ላይ ጉዳት ለማድረስ ወይም ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ኮሚሽኑ የሚጠቀምበትን ቅፅ፣ ማህተም፣ መታወቂያ፣ አርማ፣ የጉምሩክ ማሸጊያ ወይም ማናቸውም ሰነድ ወይም ምልክት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም አስመስሎ የሰራ ወይም ይህንኑ ያከፋፈለ፣ የተጠቀመ ወይም ለመጠቀም የሞከረ ወይም ለጉምሩክ ስነ ስርአት የሚቀርቡ ሰነዶችን የሰረዘ፣ የደለዘ፣ የፋቀ ወይም አስመስሎ የሰራ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 አንቀፅ 167 እና በጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ 1160/2011 አንቀፅ 169(4) መሰረት ከአምስት እስከ አስር አመት እስራት ይቀጣል፡፡

ከላይ ከተመለከቱት መንግስታዊና ህዝባዊ ሰነዶችን ማዘጋጀትና መገልገል ወንጀል በተጨማሪ በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴ የምንጠቀምባቸውን ግላዊ ሰነዶችን በሀሰተኛ መንገድ ማዘጋጀትና መገልገል ከለይ ከተመለከተው ከባደ ሁኔታ ዝቅ ባለ በመለስተኛ ደረጃ በወንጀል የሚያስጠይቅ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅም ወይም መሻሻልን ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ተገቢ መብት ለማስገኘት የሚችሉ ፅሁፎችን፣ ግላዊ ሁኔታን የሚገልፁ ማስረጃዎችን ወይም ምስክርነትን ማስረጃዎችን ወይም ማናቸውንም አይነት ጉዳይ የሚመለከቱ የምስክርነት ማረጋገጫ ሰነዶችን ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም አስመስሎ የሰራ ወይም እያወቀ ይህን የመሰለውን ሰነድ እንዲገለገልበት ለሌላ ሰው መስጠት በ1996 ዓ/ም የወንጀል ህግ አንቀፅ 385 መሰረት በቀላል እስራት ወይም መቀጮ ያስቀጣል፡፡ ይህ ሰነድ የግል ጉዳይን የያዘ እንደሆነ ከአንድ አመት ባልበለጠ እስራት፣ ወይም ሰነዱ ህዝባዊ ባህሪ ያለው ሆኖ እንደመታወቂያ ወረቀት ወይም የልደት ምስክር ወረቀት ወይም የችግርተኛነት፣ የመልካም ጠባይ፣ የብቁነት ወይም ብቁ አለመሆን ማረጋገጫ ምስክርነት ወይም የህዝብ መዝገብ ወይም መቆጣጠሪያ ቅጂ እንደሆነ ከሶስት ወር በማያንስ እስራት ያስቀጣል፡፡

በሌለ በኩል ወንጀሉን የፈፀመው እነዚህን ሰነዶች እንዲያዘጋጅ፣ እንዲያስቀምጥ፣ እንዲጠብቅ ወይም እንዲሰጥ ሀላፊነት በተሰጠው የመንግስት ሰራተኛ እንደሆነ እና ይህን ወንጀል ያደረገው በሌላ ሰው መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ ሳያስብ እንደሆነ ከስድስት ወር እስከ አምስት አመት በሚደርስ እስራት ወይም በመቀጮ ወይም በሁለቱም ያስቀጣል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሀኪም፣ የጥርስ ሀኪም፣ የመድሀኒት ቅመማ ባለሙያ፣ የእንስሳት ሀኪም፣ አዋላጅ ወይም በህክምና ሙያው ህክምናን በሚመለከት የምስክር ወረቀት ለመስጠት መብት ያለው ማንኛውም ሌላ ሰው የምስክር ወረቀት ስራ ላይ እንደሚውል እያወቀ ለተቀባዩ ሰው የማይገባ ጥቅም ለማስገኘት የሚችል ወይም የሌላውን ሰው ህጋዊ ጥቅም የሚጎዳ ሀሰተኛ የህክምና ምስክር ወረቀት አዘጋጅቶ ፅፎ የሰጠ በወንጀል ህግ አንቀፅ 387 መሰረት በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል፡፡ ይህ ወንጀል በመንግስት ሰራተኛ ከተፈፀመ ወይም ወንጀሉ በስጦታ ወይም በሌላ ጥቅም የተፈፀመ ከሆነ ቅጣቱ ከአስር እስከ አስራ አምስት አመት እስራት ይደርሳል፡፡ በመጨረሻም ማንም ሰው ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ሊገለገልባቸው በማሰብ ኦፊሴላዊ ፅሁፎችን፣ የምስክር ወረቀቶችን፣ ዲፕሎማዎችን ወይም ሰነዶችን ወደ ሀሰተኛነት ለመለወጥ ወይም በሀሰት ለመፍጠር የሚያገለግሉ መሳሪያዎችንና መስሪያዎችን ወይም ቁሳዊ ነገሮችን የሰራ፣ በእጁ ያስገባ፣ የያዘ፣ የሰጠ ወይም ለሽያጭ ወይም ለስጦታ ያቀረበ እንደሆነ በአንቀፅ 390 መሰረት ከአምስት አመት በማይበልጥ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል፡፡

በአጠቃላይ ከላይ ከተመለከቱት የሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል ወንጀሎች ሰፊ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገባና ህብረተሰቡ ከእነዚህ ወንጀሎች እራሱን ማራቅና መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ እነዚህ ወንጀሎች በሀገርና በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሱ ሲሆን የዜጎችን መብትና ጥቅም በማጭበርበር የሚያሳጡ ናቸው፡፡ በህግም የሚያስከትሉት ተጠያቂነት ሰፊና ከባድ ነው፡፡ ስለሆነም ሀሰተኛ ሰነዶች ከማዘጋጀት፣ እንዲዘጋጅ ከማድረግ፣ ይዘን ከመገኘት፣ ከመገልገል፣ ሀሰተኛ ሰነድ መስሪያ መሳሪያዎችን ይዞ ከመገኘት መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም እንዲህ ያለ ጥፋት መፈፀሙን ስናስተውል ለህግ አስከባሪ አካላት ማሳወቅ እና ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ መተባበር ያስፈልጋል፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
በነጋሪ መተግበሪያ አዲሱን የፌዴራል ጠበቆች አዋጅን (አዋጅ ቁጥር 1249/2013) አካትተናል፤ ይህ አዋጅ የቀድሞ የፌዴራል የጥብቅና አዋጅ አዋጅ ቁጥር 199/1992 ሽሮ በአዲስ የተካ ሲሆን ይህ አዋጅ በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ አዳዲስ ሐሳቦችን ያካተተ ሲሆን ከዚህ አዋጅ ጋር ራስዎን ያስተዋውቁ፤

አዋጅ ቁጥር 1249/2013 - የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ
http://negari.abyssinialaw.com/laws?id=1973
https://t.me/casemanagers
ጉዳይዎን እናስፈፅምልዎ ከግል ተቋማት ሆነ ከግለሰብ፣ ከመንግስት መስሪያቤት ጋር በተያያዘ ያሰቡትን እንፈፅምልዎ።
@Casemanager_bot
Screenshot_20211119-145340.jpg
269.3 KB
አዲሱን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1234/2013) በነጋሪ አንድሮይድ መተግበሪያ አካትተናል፤

ይህ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 25/1988 እና ማሻሻያ አዋጆቹን አዋጅ ቁ. 138/1991፣ አዋጅ ቁ. 254/1993፣ አዋጅ ቁ. 321/1995 እና አዋጅ ቁ. 454/1997 በሙሉ ሽሮ በአዲስ መልክ የወጣ ነው።

አዋጅ ቁጥር 1234/2013 - የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ
http://negari.abyssinialaw.com/laws?id=1983