አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#AGOA

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ተጠቃሚ ከነበረችበት የአሜሪካ የንግድ ችሮታ (AGOA) ማስወጣታቸውን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ማሳወቃቸውን ኋይት ሃውስን ዋቢ አድርጎ አል ዓይን ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ከንግድ ችሮታው እንዲትወጣ ፕሬዝዳንቱ ደብዳቤ የጻፉት ከሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ጋር ተያይዞ መሆኑንም ኋይት ሃውስ አስታውቋል።

አሜሪካ ፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር ጥልቅ ውይይቶች ተደርገው እንደነበር ገልጻለች።

ጆ ባይደን ከኢትዮጵያ በተጨማሪም ጊኒ እና ማሊም ከአሜሪካ የንግድ ችሮታ (አጉአ) እንዲወጡ ደብዳቤ መጻፋቸውንም ኋይት ሃውስ አስታውቋል።

ሀገራቱ ይህ የተወሰነባቸው #የአሜሪካን_ፍላጎቶች ማሟላት ባለመቻላቸው መሆኑንም አሜሪካ ገልጻለች።
tikvahethiopia
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፤ መንግስት በሽብር የጠረጠረውን ማንኛውንም ሰው በቁጥጥር ስር እንደሚያደርግ አስታወቀ

አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በ48 ሰዓታት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ የተገለጸ ሲሆን ተፈጻሚ የሚሆነው ግን ከዛሬ ጀምሮ ነው፡፡ዝርዝሩን ለማንበብ፡-https://am.al-ain.com/article/government-says-any-individual-suspected-of-terror-should-be-arrested-without-arrest-warrant
ዝርዝር መረጃ !

ከዛሬ ጀምሮ በመላ አገሪቱ በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተከለከሉ ተግባራትና ግዴታዎች ከላይ በዝርዝር ተቀምጠዋል ያንብቡ።
Tikvah
4_5767119666585537235.pdf
685.6 KB
Directive on state of emergency
Attorney

Goh Betoch Bank S.C

Addis Ababa

JOB DETAILS: Attorney Job Requirement • Educational Level and work Experience: LLB in Law and 3 years’ of related work experience Place of Work: Head Office Education Requirement: No Requirements Work Hours: 8 Experience in Months: 36

Job application procedure
Application Deadline: November 06, 2021.
• Interested and qualified applicants fulfilling the above criteria can apply in person at Head Office Abedruf Plaza located around Bole Ruanda –Japan Embassy. Goh Betoch Bank S.C Human Capital Management Department Addis Ababa

ALE (Alternative Legal Education) All in one, for all.🔴አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/lawsocieties/
መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። ግዴታዎችንና መብቶችን ይወቁ።
Attorney I

Berhan Bank S.C

Addis Ababa

Job Description - Place of Work:- Head Office - Salary as per the Bank's Scale Job Requirements - LLB in Law - Two years relevant experience having Banking experience is more advantageous How to Apply - Qualified applicants are invited to submit their application letter, curriculum vitae and copy of non-returnable supporting documents only through mail to Berhan Bank S.C Human Resource Operations and Development Department P.O.BOX 387 CODE 1110.

Berhan Bank S.C

ALE (Alternative Legal Education) All in one, for all.🔴አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/lawsocieties/
መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። ግዴታዎችንና መብቶችን ይወቁ።
Forwarded from አለሕግAleHig ️
proclamation no. 1249.pdf
1.2 MB
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌዎች
፩. አጭር ርዕስ

ይህ አዋጅ “የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ
አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር
፩ሺ፪፻፵፱
/፪ሺ፲፫" ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
#ETHIOPIA

ማንኛውም የፀጥታ ችግር እንቅስቃሴ ሲመለከቱ ወይም ደግሞ ጥቆማ ለመስጠት ከፈለጉ ከላይ በተቀመጡት የስልክ መስመሮች ፈጥነው እንዲደውሉ የፌዴራል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።
#ሼር #Share
tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ተጨማሪ አዳዲስ የደንብ ልብሶችን ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ አሳውቋል።

ነባሩን የደንብ ልብስ መጠቀም ማቆሙን ተቋሙ ገልጿል፡፡

ከዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አዳዲሶቹ የደንብ አልባሳትን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ እና ነባሩ የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ መቀየሩ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ አሮጌውን የደንብ ልብስ ለብሶ የተገኘ አመራር እና አባል ላይ ጠንከር ያለ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል ተብሏል።

ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አሮጌው የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ በአዳዲሶቹ መቀየሩን ተገንዝበው አሮጌውን የደንብ ልብስ የለበሰ የፖሊስ አባል ሲያጋጥማቸው መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ፖሊስ ስራ ላይ ካዋላቸው አዳዲስ የደንብ አልባሳት ጋር ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደገገ ስለሆነ ከአ/አ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#Share #ሼር
tikvahethiopia
የፍትሐብሔር ክርክር የፍርድ ቤት መጥሪያ አደራረስና ዉጤቶቹ
---------------------
1. መግቢያ
በፍትሐብሔር ክርክር ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ አውቆ መቃወሚያ፣ የመከላከለያ መልስ እና ማስረጃ የማቅረብ እና የመሰማት መብት አለው፡፡ አንድ ተከሳሽ ወደ ክርክር እንዲገባ መጥሪያ ሊደርሰዉ ይገባል፡፡ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ በትክክል መጥረያዉ መድረሱን ክርክሩ ከመጀመሩ በፊት ማረጋገጥ አለበት፡፡ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 70 መሰረት መጥሪያዉ መድረሱን ካረጋገጠ በኋላ ክርክሩ እንዲቀጥል ያደርጋል፡፡ በዚህ አጭር ጽሁፍ የመጥሪያ ምንነት እና ዓላማዉ፣ መጥሪያ ማን ያደርሳል፣ መጥሪያ የመስጠት ሂደት፣ የመጥሪያ አደራረስ ዘዴዎች እና የመጥሪያ አደራረስ ዉጤቶችን እንመለከታለን፡፡
2. የመጥሪያ ምንነት እና ዓላማዉ
መጥሪያ ማለት በፍርድ ቤት የሚዘጋጅ ህጋዊ ሰነድ ሲሆን ተከሳሽ በምን ጉዳይ እንደተከሰሰ፣ መቼና የት እንደሚቀርብ፣ ተከሳሽ ለቀረበበት ክስ የመከላከያ ማስረጃዉን በፅሁፍ እንዲያቀርብ የሚያዝ፤ መልሱን ባያቀርብም ጉዳዩ መሰማት እንደሚቀጥል (default proceeding) የሚገልፅ ሰነድ ነው (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 233) ፡፡ በዚህም ተከራካሪ ወገኖች እኩል የመከራከር መብት እንዲኖራቸው በማድረግ ጉዳዮ ፍትሐዊ በሆነ አካኋን እንዲወሰን ለማድረግ የሚያስችል ነው፡፡ መጥሪያ ለተከሳሽ የሚላክበት ዋና ዓላማ ተከሳሽ መከሰሱን አዉቆ ለቀረበበት ክስ የበኩሉን መከላከያ ለማቅረብ እንዲችል ዕድል ለመስጠት ነዉ፡፡ ተከሳሽ የተከሰሰበትን ጉዳይ እንዲያዉቅና በአግባቡ እንዲከላከል ሲመሰከረበት ለምስክሮች መስቀለኛ ጥያቄ በማቅረብና የራሱንም ምስክሮች የማሰማት መብት አለዉ፡፡ ስለዚህ ተከሳሽ ወደ ፍርድ ቤት ቀርቦ ራሱን ለመከላከል እንዲችል የቀረበበትን ክስና ይህንን ክስ ለመከላከል የትና መቼ መቅርብ እንዳለበት ሊያዉቅ ይገባል፡፡ ዳኝነት የሚሰጠዉ የአንድን ወገን አቤቱታ በመስማት ብቻ አይደለም፡፡
3. መጥሪያ ማን ያደርሳል
ለተከሳሽ የሚላከዉ መጥሪያ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 95 (1) መሰረት ፍርድ ቤቱ ባዘዘዉ ሰዉ ወይም በማንኛዉም ሰዉ በኩል ይላካል፡፡ ይህ ማለት ከሳሽ፣ ተከሳሹ የሚሰራበት የመንግስት ወይም የግል ድርጅት ኃላፊ፣ የቀበሌ/የወረዳ እና የፖሊስ አካላት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ተከሳሾች ብዙ ከሆኑ ለእያንዳንዳቸዉ በግል መጥሪያ ሊደርሳቸዉ ይችላል፡፡ በሀገራችን በተለምዶ ከሳሹ እራሱ እንዲያደረስ እየተደረገ ይገኛል፡፡
4. መጥሪያ የመስጠት ሂደት
ማናቸውም አይነት መጥሪያ እንዲስጥ የታዘዘ ሰው ተከሳሽን በአድራሻው ለማግኘት የሚችል በሆነበት መጠን መጥሪያውን የማድረስ ግዴታ አለበት፡፡ መጥሪያ ሰጪው መጥሪያውን ለተከሳሽ ለማድረሱ ማረጋገጫ እንዲሆን መጥሪያውን ሲሰጥ የፍርድ ቤቱን መጥሪያ ኮፒ አድርጎ ወይም በሌላ ወረቀት ላይ የተቀባዩን ስምና የተቀበለበትን ቀን በመጻፍ እንዲሁም ተቀባዩ ሲቀበል የነበሩ ምስክሮች ስም በዝርዝር ተጽፎ ማስፈረም አለበት፡፡ ይህንን ተቀባዩ መጥሪያውን ስለመቀበሉ የፈረመበት እና ራሱ ያረጋገጠበትን ለፍርድ ቤቱ ይመልሳል (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 104) ፡፡
በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 102 እንደተደነገገው መጥሪያ ሰጪው ለተከሳሽ፣ ለጠበቃው፣ ለወኪሉ ወይም መጥሪያውን ለመቀበል አግባብ ለሆነ ሰው በሚሰጥበት ወቅት ተቀባዩ የደረሰው ስለመሆኑ መፈረም አለበት፡፡ ተቀባዩም መጥሪያው ለእርሱ የተላከ መሆኑን፣ የተያያዙት ሰነዶችም በመጥሪያው ላይ በተገለጸው ብዛት መሆናቸውን በማረጋገጥ ፈርሞ መቀበል አለበት፡፡ መጥሪያ ሰጪው ተከሳሹ መጥሪያ ለመቀበል ፈቃደኛ ካልሆነ ወይም ለማግኘት ያልቻለ ከሆነ መጥሪያ ሰጪው ለፍርድ ቤት ይህንኑ በፅሁፍ በመግለጽ በቃለ መሃላ አስደግፎ ዋናውን መጥሪያ መመለስ ይኖርበታል፡፡ በመሆኑም ተከሳሽ በምትክ የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴ መጠራቱን እንዲያውቀው ይደረጋል፡፡
5. የመጥሪያ አደራረስ ዘዴዎች
አንድ የክስ ማመልከቻ ጉድለት የሌለዉ ከሆነ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለመስማት ቀጠሮ መያዝና ተከሳሹ በቀነ ቀጠሮዉ እንዲቀርብ መጥሪያ መላክ ይኖርበታል፡፡ ፍርድ ቤቱ በመጥሪያዉ ላይ ተከሳሹ ከመከላከያ መልሱ በተጨማሪ ለክርክሩ ይጠቅሙኛል የሚላቸዉን የሰዉና የሰነድ ማስረጃዎች ዝርዝር ሁሉ ይዞ እንዲቀርብ መግለጽ ይኖርበታል፡፡ አንዲሁም ተከሳሹ በቀነ ቀጠሮዉ የማይቀርብ ከሆነ ወይም የመከላከያ መልሱንና ማስረጃዉን ሳይዝ የሚቀርብ ከሆነ ጉዳዩ በህጉ መሠረት ተከሳሽ በሌለበት አይቶ እንደሚወስን በመጠሪያዉ ላይ መግለጽ ይኖርበታል፡፡ (የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 94 እና 233 ይመለከቷል)፡፡
ይህ የሚሆነው ደግሞ የፍርድ ቤቱ መጥሪያ የደረሰ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ መጥሪያው ለተከሳሽ በቀጥታ ለራሱ መስጠት፤ ይህ ካልተቻለ ደግሞ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህጉ ከቁጥር 96 እስከ 110 ላይ የተመለከቱትን የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴዎች በመጠቀም መጥሪያው ለተከሳሽ ማድረስ አለበት፡፡ በፍትሐብሔር በሥነ ሥርዓት ህጉ መሰረት በዋናነት አራት አይነት የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴዎች አሉ፡፡
እነዚህም፡-
 መጥሪያን ለተከሳሽ ለራሱ መስጠት፣
 አማራጭ የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴ፣
 ምትክ መጥሪያ አሰጣጥ ዘዴ እና
 በፖስታ የመላክ ወይም የጋዜጣ ማስታወቂያ ናቸው፡፡
5.1 መጥሪያን ለተከሳሽ ለራሱ መስጠት
የፍርድ ቤት መጥሪያ ለተከሳሽ ለራሱ መስጠት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህግ ቁጥር 95 (3) ላይ “… የሚቻል በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ መጥሪያ የሚሰጠው ለተከሳሹ ለራሱ ነው፡፡” በማለት ያስቀምጣል፡፡ መጥሪያው ለተከሳሹ ለራሱ እንደተሰጠ የሚቆጠረው መጥሪያውን ለተከሳሽ ለራሱ በእጅ በመስጠት ብቻ ሳይሆን ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 96 እስከ 98 በተገለፁት መንገዶች መጥሪያን ማድረስ ለተከሳሽ ለራሱ እንደ ደረሰው ወይም መድረሱን እንዳወቀ ይቆጠራል፡፡ እነዚህም መንገዶች፡-
 ተከሳሹ መጥሪያን ለመቀበል ስልጣን ለሰጠው ወኪል፣
 ለተከሳሽ ነገረፈጅ ወይም ጠበቃ ለራሱ በእጅ በመሰጠት ወይም ቢሮ በማስቀመጥ፣
 ክሱ በንግድ ድርጅት ላይ የቀረበ በሆነ ጊዜ ለድርጅቱ ዋና ፀሃፊ፣ ከዳይሬክቶሬቶቹ ለአንዱ ወይም ለድርጅቱ ሹማምንት ለአንዱ በመስጠት ወይም ድርጅቱ የተመዘገበበት አድራሻ ካለው ወስዶ በመስጠት ወይም በፖስታ በመላክ እና
 የንግድ ሸሪኮች በሽርክና የንግድ ድርጅታቸው ስም ሲከሰሱ ከሸሪኮች ለአንዱ ወይም ለተወሰኑት ወይም ለዋና መስሪያ ቤቱ መሪ ኃላፊ መስጠት ናቸው፡፡
5.2 አማራጭ የመጥሪያ አሰጣጥ
ይህ አማራጭ የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴ ተከሳሽን ለማግኘት ሰፊ እድል ላላቸው ብሎም የፍርድ ቤቱን መጥሪያ በአግባቡ ያደርሳሉ ተብሎ ለሚታመኑ ሰዎች መጥሪያው የሚሰጥበት አግባብ ነው፡፡ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ ከ99 እስከ 101 በተመለከተው መሰረት ክስ የቀረበው በንግድ ስራው ላይ ሆኖ ተከሳሽ ከፍርድ ቤቱ የስልጣን ክልል (የንግዱ ቦታ) ውጪ የሚኖር በሆነ ጊዜ የንግድ ስራው በኃላፊነት ለሚመራው ወኪል/ሥራ አስኪያጅ፣ ክሱ የቀረበው የማይንቀሳቀስ ንብረት አስመልክቶ በሆነ ጊዜ ለንብረቱ ጠባቂ ወይም በዚሁ ንብረት ላይ ለሚገኝ ሰው እና ክሱ የቀረበው ከእነዚህ ሁለት ጉዳዮች ውጭ ስለማናቸውም ክስ ተከሳሽን ለማግኘት ያልተቻለና ወኪል የሌለው ሲሆን አካለ መጠን (18 ዓመት ለሞላው) ለደረሰ የተከሳሹ የቤተሰብ አባል መጥሪያው በአማራጭ በመስጠት ለተከሳሽ እንዲደርስ ይደረጋል፡፡
5.3 ምትክ መጥሪያ
መጥሪያ ሰጪው ተገቢውን ጥረት አድርጎ መጥሪያን ለተከሳሽ በግል የመስጠት ወይም አማራጭ የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴን በመጠቀም ለማድረስ ያልተቻለ መሆኑን ወይም ተከሳሽ ወይም ወኪሉ ወይም ስለ እርሱ ሆነው መጥሪያውን መቀበል የሚገባው ማናቸውም ሰው መጥሪያ የደረሰው ስለመሆኑ ማረጋገጫ ለመፈረም እንቢተኛ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ በቃለ መሓላ አረጋግጦ መጥሪያውን ሲመልስ እንዲሁም ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ መጥሪያ እንዳይደርሰው ሆነ ብሎ የተሸሸገ ወይም መሰናከል ያደረገ መሆኑን ሲረዳ መጥሪያው በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ግልፅ በሆነ ስፍራ እና በተከሳሹ መደበኛ መኖሪያ ቤት ወይም በመጨረሻ ጊዜ ይኖርበት የነበረበት መኖሪያ ቤት ወይም የንግድ ወይም የስራ ቦታ እንዲለጠፍ በማድረግ ተከሳሹ መጠራቱን እንዲያውቀው ያደርጋል (በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 103 እና 105)፡፡
5.4 ፖስታ በመላክ ወይም በጋዜጣ ማስታወቂያ
የመጨረሻው የመጥሪያ ማድረስ አማራጭ ዘዴ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሹ በፖስታ ቤት አማካኝነት መጥሪያውን በመላክ ወይም በጋዜጣ ማስታወቂያ አማካኝነት ተከሳሹ መጠራቱን እንዲያውቀው ማድረግ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሹ በፖስታ ቤት አማካኝነት መጥሪያውን በመላክ ተከሳሹን ለማግኘት ሙከራ ይደረጋል፤ በዚህ ዘዴ ተከሳሽ መቅረብ ካልቻለ በመጨረሻው አማራጭ ፍርድ ቤቱ በጋዜጣ ማስታወቂያ አማካኝነት ተከሳሹ መጠራቱን እንዲያውቀው ያደርጋል፡፡
ፍርድ ቤቱ መጥሪያው በተከሳሹ ወይም በወኪሉ መደበኛ መኖሪያ ቤት ወይም በሚሰራበት የስራ አድራሻ በአደራ ፖስታ እንዲላክ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 106 (1) መሰረት ማዘዝ ይችላል፡፡ በዚሁ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 ስር በግልፅ እንደተደነገገው ፖስታ ቤቱ መጥሪያውን ያደረሰ መሆኑን ወይም ተከሳሹ ወይም ወኪሉ መጥሪያውን ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በፅሁፍ ሲያሳውቅ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሹ መጥሪያ እንደደረሰ ሊቆጥር ይችላል፡፡
ተከሳሹ የሚኖረው የመጥሪያ ትእዛዙን ከሰጠው ፍርድ ቤት የስልጣን ክልል ውጪ የሆነ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ በሚኖርበት ወይም በሚሰራበት ወይም በሚነግድበት ቦታ ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት መጥሪያውን እንዲያደርስ ሊልክ እንደሚችል በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 107 ላይ ተደንግጓል፡፡ መጥሪያው የተላከለት ፍርድ ቤት የወሰደውን እርምጃ በፅሁፍ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡ ከኢትዮጲያ ግዛት ውጭ ለሚኖር ተከሳሽ መጥሪያ የሚቀበል ወኪል የሌለው እንደሆነ በተከሳሹ ስምና አድራሻ ተጽፎ ለሚገኝበት ሀገር በፖስታ ይላካል፡፡ ከኢትዮጲያ ግዛት ውጭ የሚኖር ተከሳሽ አድራሻው የማይታወቅ ከሆነ ደግሞ ኢትዮጲያ ጋዜጣ ላይ የመጥሪያ ማስታወቂያ እንዲወጣ ፍርድ ቤቱ ለማዘዝ ይችላል (በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 108)፡፡
ከላይ የተገለጹትን የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴዎች በመጠቀም ማድረስ ያልተቻለ እንደሆነ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 105-109 በተደነገገዉ መሰረት መጥሪያ በፖስታ የማድረስ ዘዴና ምትክ መጥሪያ አሰጣጥ ዘዴንም መጠቀም ይቻላል፡፡ ከዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባዉ ጉዳይ እነዚህ የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴዎች ሥራ ላይ መዋል ያለባቸዉ መጥሪያን ለተከሳሽ በግል የመስጠት ዘዴን በመጠቀም ለማድረስ ያልተቻለ ወይም የማይቻል መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነዉ፡፡
6. የመጥሪያ አደራረስ ዉጤቶች
ከመጥሪያ አደራረስ ጋር ተያይዞ ሁለት ዓይነት ዉጤቶች ያሉ፡፡ እነሱም
• መጥሪያን በአግባቡ አለማድረስ ስለሚያስከትለዉ ዉጤት
• መጥሪያ በአግባቡ ደርሶት ያለመቅረብ ዉጤት
6.1 መጥሪያን በአግባቡ አለማድረስ ስለሚያስከትለዉ ዉጤት
የተለያዩ የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴዎችን በመጠቀም ተከሳሽ ስለተከሰሰበት ጉዳይ አዉቆ እራሱን እንዲከላከል ለመጥራት የሚቻል ሲሆን የመጥሪያ አደራረስ ዘዴዎቹን በቅደም ተከተል ጥቅም ላይ መዋል ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከላይ የተጠቀዉን የመጥሪያ ማድረስ ቅደም ተከተል ደረጃ በደረጃ በማከናወን መጥሪያዉ ለተከሳሽ እንዲደርስ ካላደረገ በበቂ ሁኔታ መጥሪያዉ ለተከሳሽ ሊደርሰዉ አልቻለም ተብሎ ይገመታል፡፡ በመሆኑም አግባብነት የሌለዉ የመጥሪያ አደራረስ ዘዴ በመጠቀም ተከሳሹ ስለተከሰሰበት ጉዳይም ሆነ ፍርድ ቤት ስላለበት ቀጠሮ እንዳያዉቅ በመከልከል ራሱን የመከላከል ዕድል መንፈግ ተገቢዉን የሕግ ሥርዓት የተከተለ አሠራር አይደለም፡፡ ስለሆነም በዚህ ዓይነት አድራጎት በተከሳሽ መብትና ጥቅም ላይ ሊደርስ የሚችለዉን አዳጋ ለመከላከል ሲባል ፍርድ ቤቶች መጥሪያዉ በአግባቡ ባልደረሰ ጊዜ የተለያዩ እርምጃዎችን ለመዉሰድ እንደሚችሉ የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 70(ሀ) (ለ) እና 78(2) ይደነግጋሉ፡፡ ይኸዉም፡- ክርክሩ እንዲሰማ በተወሰነዉ ቀነ ቀጠሮ ከሳሽ ቀርቦ ተከሳሽ ያልቀረበ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሹ የተላከለት መጥሪያ የደረሰዉ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ መጥሪያዉ በትክክል መድረሱ ያልተረጋገጠ ከሆነ ፍርድ ቤቱ ሁለተኛ መጥሪያ እንዲላክ ትዕዛዝ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ፍርድ ቤቱ ይህን ሳያደረግ በማለፍ ጉዳዩ ተከሳሽ በሌለበት አይቶ እንዲወሰን ትዕዛዝ ቢሰጥና በዚህ መሠረት ክርክሩ ተከሳሽ በሌለበት አይቶ በተከሳሽ ላይ ቢወሰንበት ተከሳሽ መጥሪያዉ በሚገባ ያልደረሰዉ መሆኑን ገልፆ ዉሳኔዉ ወይም ትዕዛዙ መሰጠቱን በተረዳ ጊዜ ዉስጥ ቀርቦ ትዕዛዙ ወይም ዉሳኔዉ እንዲነሳለት ማመልከት ይችላል፡፡ ይህም ሲሆን ፍርድ ቤቱ መጥሪያዉ ለተከሳሹ በአግባቡ ያልደረሰዉ መሆኑን ከተረዳ የተከሳሽ አቤቱታ ለከሳሽ እንዲደርስ ካደረገ በኋላ ብይኑን ወይም ትዕዛዙን በማንሳት ክርክሩን እንደገና ሰምቶ መወሰን እንዳለበት የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 78(2) ይደነግጋል፡፡ ስለሆነም መጥሪያን በተገቢዉ መንገድ ለተከሳሽ አለማድረስ የክርክሩን ዕድሜ ያለአግባብ ከሚያራዝምና ተከራካሪ ወገኖችን የሥራ ጊዜ ያለ አግባብ ከሚሻማ በቀር ብዙም ፋይዳ ያለዉ አለመሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡
6.2 መጥሪያ በአግባቡ ደርሶት ያለመቅረብ ዉጤት
ፍርድ ቤት አንድ ጉዳይ ለማየት እና ውሳኔ ለማስተላለፍ የተለያዩ ቀጠሮዎች እንደሚሰጥ የታወቀ ነው፡፡ የመጀመሪያ ተከሳሽ መከሰሱን አውቆ ለቀረበበት ክስ መከላከያ የሚሆኑ ማስረጃዎችን በፅሁፍ የሚያቀርብበት ነው፡፡ ፍርድ ቤት ተከሳሽ መጥሪያው በአግባቡ ደርሶት መልሱን ይዞ ከቀረበ ፍርድ ቤቱ በሥነ ሥርዓት ህጉ 241 እና ተከታዮቹ መሰረት ክሱን ለመስማት ይቀጥራል፡፡
ፍርድ ቤቱ ጉዳዩ ሊሰማ በተወሰነበት ቀነ ቀጠሮ ከሳሽ ቀርቦ ተከሳሽ ሳይቀርብ የቀረ እንደሆነ የፍርድ ቤቱ ቀዳሚ ስራ መጥሪያው ለተከሳሹ መድረሱን ማረጋገጥ ነው (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 70)፡፡ ፍርድ ቤቱ ለተከሳሽ የላከው መጥሪያ የደረሰው መሆኑን ካረጋገጠ በሌለበት ጉዳዩን መስማት ይቀጥላል፡፡ መጥሪያው ለተከሳሽ በአግባቡ ያልደሰረው መሆኑን ካረጋገጠ ወይም አጠራጣሪ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ሁለተኛ መጥሪያ እንዲላክ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡ አንድ እና ከዚያ በላይ ለሆኑ ተከሳሾች የተላከው መጥሪያ ለአንዱ ወይም ለአንዳንዶች ሳይደርስ የቀረው በከሳሽ ቸልተኘነት ወይም ጉደለት ከሆነ ፍርድ ቤቱ ከሳሽ መጥሪያ ባልደሰው ወይም ባልደረሳቸው ተከሳሾች ላይ ያቀረበውን ክስ ሊዘጋ ወይም ቀነ ቀጠሮ ሊቀይር ይችላል፡፡
ተከሳሽ የመከራከር መብቱን እንደተወው የሚቆጠረው መጥሪያው በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ በተዘረጋው ሥርዓትና ቅደም ተከተል መሰረት ደርሶት ክርክር ያለው መሆኑን እያወቀ ሳይቀርብ ሲቀር ብቻ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ በሕጉ የተዘረጋውን ስርዓት ተከትሎ አማራጭ የመጥሪያ አደራረስ ሥርዓት ከፈጸመ መጥሪያው ለተከሳሹ እንደደረሰ እንደሚቆጠርና ወደ ክርክሩ እንዲገባ የሚፈቀደው ላለመቅረቡ በቂና ሕጋዊ ምክንያት ካለው ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም የተከሳሽ የመከራከርና የመሰማት መብት እንዲጠበቅ በሥነ ሥርዓት ሕጉ በተዘረጋው ሥርዓት መሰረት መጥሪያው በሚገባ ሊደርስ እና ሊረጋገጥ ይገባል፡፡
ክርክሩ በሌለበት እንዲቀጥል የተወሰነበት ተከሳሽ በቀጣይ ቀነ ቀጠሮ ቀርቦ በቂ በሆነ ምክንያት በመጀመሪው ቀነ ቀጠሮ ያለመቅረቡን ካስረዳ መከላከያውን አቅርቦ የመከራከር መብት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 72 ይደነግጋል፡፡ እንዲሁም ክርክሩ ሊሰማ በተቀጠረበት ቀን ቀርቦ መልስ ሳይሰጥ ወይም መከራከሪያውን ሳያሰማ በሌለበት እንዲታይ ትዕዛዝ ወይም ውሳኔ መሰጠቱን ካወቀ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተከሳሽ መጥሪያው በሚገባ ያልደረው መሆኑን ወይም በቂ ምክንያት በማቅረብ ትዕዛዙ ወይም ውሳኔው እንዲነሳለት በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 78 መሰረት መጠየቅ ይችላል፡፡ በዚሁ ድንጋጌ መሰረትም ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ያቀረበውን አቤቱታ አግባብ መሆኑን ከተረዳ ለከሳሽ አቤቱታው እንዲደርሰው በማድረግ ትዕዛዙን ወይም ውሳኔውን በማንሳት ክርክሩን እንደገና ስምቶ ይወስናል፡፡
በአጠቃላይ መጥሪያው ለተከሳሽ በቀጥታ ለራሱ መስጠት፤ ይህ ካልተቻለ ደግሞ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ህጉ ከቁጥር 96 እስከ 110 ላይ የተመለከቱትን የመጥሪያ አሰጣጥ ዘዴዎች በመጠቀም መጥሪያው ለተከሳሽ መድረስ አለበት፡፡ የከሳሽ መጥሪያ ለተከሳሽ አለማድረስም ሆነ ተከሳሽ መጥሪያ ደርሶት ፍርድ ቤት አለመቅረብ የራሱ የሆነ ዉጤት እንዳለዉ ልንገነዘብ ይገባል፡፡

ALE (Alternative Legal Education) All in one, for all.🔴አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/lawsocieties/
መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። ግዴታዎችንና መብቶችን ይወቁ።
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ (መመሪያ ቁጥር 008/2013)

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያዘጋጀውን እና ያጸደቀውን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍትሐብሔር ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር መመሪያ ከዚህ ያግኙ፤

መመሪያው ስለ ግልጽ ችሎት እና ቀዳሚነት፣ የቀጠሮ ፖሊሲ፣ የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር እና የተለያዩ አካላት ተግባርና ኃላፊነት፣ የጉዳዮች እልባት የመስጫ ጊዜ ገደብ፣ ተጠባቂ ግብ እና የጊዜ ገደብ የአፈጻጸም መለኪያዎች መሰል ጉዳዮችን ይዟል።

ይህንን መመሪያ አስፈላጊነቱን በማመን በነጋሪ የስልክ መተግበሪያም አካትተናል።

https://www.abyssinialaw.com/online-resources/bench-books/bench-books/federal-courts-civil-case-flow-management-directive-directive-no-008-2013-amharic-version
Attorney II
Awash Bank

Addis Ababa
Full–time

Job Title: Attorney II Company: Awash Bank Location: Addis Ababa Deadline: November 14, 2021 Term of Employment : Permanent for all Positions Skills Requirement : Knowledge of computer operation is mandatory Salary & Benefits : As per the Bank’s Salary Scale & Benefits Package Qualification & Experience • LL. B Degree in Law plus a minimum of Four (4) years of relevant banking experience. Job Summary The Job holder is responsible for representing the Bank before judicial & quasi judicial tribunals, rendering advises and drafting contracts and other legal documents, preparation of cases (pleading, defenses and petition), handling & processing foreclosure cases. How to Apply Interested applicants, who fulfill the above requirement, are invited to apply only via Online Job Application System; https://jobs.awashbank.com. within 7 consecutive days from the first date of this announcement on the website. N.B √ Incomplete applications will not be considered. Awash Bank Deputy Chief – Human Capital Management Officer Office P.O. Box 12638
https://t.me/lawsocieties