አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.84K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
If Gaddafi was the problem as the western dictators claimed, why did Libya crumbled and became a failed state after they assassinated Gaddafi?

Now Libya's gold reserves are gone, billions of dollars is missing in Libya's foreign reserves and the same people who invaded Libya are now scrambling for Libyan oil 🛢

GADDAFI WAS THE PROBLEM??
Via Desalegn Kebede
🔴🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/lawsocieties/
የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 03/2011
#AddisAbaba
ከትላንት ጥቅምት 22 ጀምሮ በአዲስ አበባ የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ የሰዓት ገደብ ክልከላ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል።

የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለሱን ተከትሎ ለአፈፃፀም ይረዳ ዘንድ መመሪያ 03/2011 በመጫን አቅም ልክ መጠን ከባድና ቀላል ተሽከርካዎች በማለት የሰዓት ገደብ ክልከላውን ለይቶ አስቀምጧል፡፡

በመመሪያው መሰረት ማንኛውም የጭነት፣ የማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካሪዎች ከማለዳ 12፡30 እስከ ረፋዱ 4፡00 ሰዓት እንዲሁም ከቀኑ 10፡00 እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ እንዲሁም ጭነት መጫንና ማራገፍ አይችሉም።

በመመሪያው ክፍል ሁለት ስለሰዓት ገደብ እና ስለፈቃ በሚያትተው ጽሁፍ መሰረት ማናቸውም ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች ማለትም ከ25 እስከ 35 ኩንታል (ከ2.5 እስከ 3.5 ቶን) የመጫን አቅም ያላቸው ተሽከርካሪዎች ከጠዋቱ 12፡30 እስከ ረፋዱ 4፡00 እንዲሁም ከቀኑ 10፡00 እስከ ምሽቱ 2፡00 እንቅስቃሴ የሚገደቡ ይሆናል፡፡

ይህ ማለት ከሰዓት ክልከላው ውጭ ያለው ጊዜ ከረፋዱ 4፡00 እስከ ከቀኑ 10፡00 ድረስ መንቀሳቀስ የሚችሉ ይሆናል፡፡

በተጓዳኙ ከባድ ተሽከርካሪዎች ማለትም ከ35 ኩንታል (ከ3.5 ቶን) በላይ የመጫን አቅም ያላቸው ተሽከርካሪዎች ደግሞ ከማለዳው 12፡30 እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ወደ ከተማ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ እንዲሁም ጭነት መጫንና ማራገፍ እንደማይቻሉ በመመሪያው ተቀምጧል፡፡

የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 03/2011 በሰኔ 2011 ዓ.ም ፀድቆ ተግባራዊ መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡

#AATB
via tikvahethiopia

ቅጣትን በተመለከተ ፦

" የሰዓት ክልከላውን የሚጥሱ አካላት ከ5 መቶ እስ 6 ሺህ በገንዘብ እና ከ1 ወር እስከ 3 ወር መንጃ ፈቃድ በማገድ ያስቀጣል " - አአትቢ

የጭነት፣ ማሽነሪዎችና መሰል ተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለሱን ተከትሎ ክልከላውን በሚጥሱ አካላት ላይ ከ5 መቶ እስ 6 ሺህ በገንዘብ እና ከ1 ወር እስከ 3 ወር የመንጃ ፈቃድ እገዳ ያስጥላል።

አሽከርካሪዎች በተለይ የከባድ ጭነት፣ ማሽነሪዎችና መሰል ተሽከርካሪዎችን የሚነዱ በሙሉ መረጃውን በማወቅ መመሪያውን እንዲያከንሩ ተብሏል።

የህግ አስከባሪዎችም መመሪያውን በሚጥሱ አካላት ላይ በተቀመጠው የቅጣት ወሰን መሰረት እንዲፈፀም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

* ቅጣትን በተመለከተ ከላይ በዝርዝር ይመልከቱ።

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ
አዲሱን የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2013 አተገባበር የሚያስተባብር ኮሚቴ በፍትሕ ሚኒስትሩ ተሰይሞ ሥራ ጀመረ
***********
የጥብቅና አገልግሎት ተጠቃሚዎች (ደንበኞች) እና የጠበቆችን መብት በተሻለ ሁኔታ ለማስከበር፣ የጥብቅና ሙያ አገልግሎት በአንድ አገር የፍትሕ ሥርዓት ዉስጥ ያለዉን የጎላ ሚና እና የሚያስፈልገዉን የሙያ ነጻነት ከግምት ዉስጥ በማስገባት እንዲሁም አገራችን የደረሰችበትን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖሊቲካዊ ዕድገት ታሳቢ ያደረገ የመንግስትና የባለሙያዉን ተዋፅኦ ያማከለ የጋራ አስተዳደር ሥርዓት መዘርጋትን ዓላማ ያደረገ አዲስ የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1249/2013 በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ፀድቆ ከሐምሌ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ ሆኗል፡፡

በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 57 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት ፈቃድ የተሰጣቸዉ ሁሉንም የፌዴራል ጠበቆች እና የጥብቅና ድርጅቶች በአባልነት ያቀፈ የኢትዮጵያ ጠበቆች ማህበር የተቋቋመ ሲሆን በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 57 ንዑስ አንቀጽ 4 መሰረት ደግሞ ማንኛዉም ፈቃድ የወሰደ ጠበቃና የጥብቅና ድርጅት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የማህበሩ አባል እንደሚሆን ሕጉ በአስገዳጅ ሁኔታ አስቀምጧል፡፡ በዚህም መሰረት ማህበሩ የጥብቅና ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር ሥራን በጋራ ለመምራት ይችል ዘንድ ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት አመራሮቹን መምረጥና የተለያዩ አሰራሮችና አደረጃቶችን ቀርጾ ወደ ሥራ መግባት ይጠበቅበታል፣

ፍትሕ ሚኒስቴር አዋጁ ከፀናበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠር 6 ወር ጊዜ ዉስጥ የመጀመሪያዉን የማህበሩን ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ የመጥራት እና ማህበሩ በአግባቡ ተደራጅቶ ሥራ እስከሚጀምር ድረስ ለመነሻ የሚሆን በጀት የመመደብ፣ ጽ/ቤት የማዘጋጀት እና በሰለጠነ የሰዉ ሃይል ማደረጀትን ጨምሮ የተለያዩ ግብዓቶችን የማሟላት እንዲሁም ማህበሩን ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ የተለያዩ አደረጃጀቶችና ኮሚቴዎችን አቋቁሞ የሽግግር ሥራዉን የማሳለጥ ኃላፊነት ተሰጦታል፡፡
ስለሆነም ሚኒስቴር መ/ቤቱ በሕግ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በሽግግር ወቅት ያለዉን የአዲሱን አዋጅ አፈጻጸም የሚከታተል ቀደም ሲል ሥራ ላይ ከነበሩ የተለያዩ የሕግ ባለሙያ አደረጃጀቶች የተወከሉ ጠበቆችን በዋናነት ያካተተ አስተባባሪ ኮሚቴ ጥቅምት 19 ቀን 2014 ዓ.ም በፍትሕ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡

የመንግስት ሕግና ፍትሕ አገልግሎት ሚኒስትር ድኤታ እና የአስተባባሪ ኮሚቴዉ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አለምአንተ አግደዉ እንደገለጹት ኮሚቴዉ የሽግግር ጊዜ ሥራዎችን የማስተባበር፣ በሂደቱ ዉስጥ የእያንዳንዱን ጠበቃ ተሳትፎ የማረጋገጥ፣ ለዚሁ ሥራ የሚሆን በጀትና ግብዓት የማሟላት ሥራዎችን በአጭር ጊዜ በማከናወን ማህበሩ ሥራዉን የሚጀምርበትን ሁኔታ የማመቻቸትና አዋጁ የወጣበትን ዓላማ ለማሳካት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ማህበሩ ኃላፊነቱን ተረክቦ ሥራ እስከሚጀምር ድረስ በአዲሱ የፌዴራል ጥብቅና አገልግሎት ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር1249/2013 አንቀጽ 98(2)፣ አንቀጽ 98፣ አንቀጽ 100 እና አንቀጽ 101 መሠረት የፍትሕ ሚኒስቴር ቀደም ሲል የተዘረጉ አሰራሮችና አደረጃጀቶችን በመጠቀም ነገር ግን አዲሱን አዋጅ እና ከአዲሱ አዋጅ ጋር የማይቃረኑ በቀድሞዉ አዋጅ መሰረት የወጡ ደንቦችና መመሪያዎችን መሰረት በማድረግ የጥብቅና ፈቃድ አሰጣጥና አስተዳደር ሥራዉን ሲያከናዉን እንደሚቆይ ሚኒስትር ድኤታዉ ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም የአዲሱ አዋጅ ተግባራዊነት ለጥብቅና አገልግሎት ተጠቃሚዎች ፣ ለጠበቆች ለራሳቸዉ እና አጠቃላይ ለፍትሕ ሥርዓቱ ዉጤታማነት ካለዉ ፋይዳ አንጻር እያንዳንዱ ጠበቃ በሽግግር ወቅት በሚከናወኑ ሥራዎችና ሁነቶች ላይ በንቃት እንዲሳተፍ፤ የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ እና አጋር አካላትም ተገቢዉን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉ አቶ ዓለምአንተ አግደዉ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
(Source: Ministry of Justice)
Breaking: #Ethiopia's Council of Ministers has declared nationwide state of emergency, party affiliated FanaBC reports. Minister of Justice Gedion Timoteos is currently briefing local media on the details, FanaBC said.
#BREAKING

በመላ ሀገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በመላ ሀገሪቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል።

የፍትህ ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌዴዎን ጢሞቴዎስ አሁን መግለጫ እየሰጡ ነው።
#AGOA

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ተጠቃሚ ከነበረችበት የአሜሪካ የንግድ ችሮታ (AGOA) ማስወጣታቸውን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ማሳወቃቸውን ኋይት ሃውስን ዋቢ አድርጎ አል ዓይን ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ከንግድ ችሮታው እንዲትወጣ ፕሬዝዳንቱ ደብዳቤ የጻፉት ከሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ጋር ተያይዞ መሆኑንም ኋይት ሃውስ አስታውቋል።

አሜሪካ ፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር ጥልቅ ውይይቶች ተደርገው እንደነበር ገልጻለች።

ጆ ባይደን ከኢትዮጵያ በተጨማሪም ጊኒ እና ማሊም ከአሜሪካ የንግድ ችሮታ (አጉአ) እንዲወጡ ደብዳቤ መጻፋቸውንም ኋይት ሃውስ አስታውቋል።

ሀገራቱ ይህ የተወሰነባቸው #የአሜሪካን_ፍላጎቶች ማሟላት ባለመቻላቸው መሆኑንም አሜሪካ ገልጻለች።
tikvahethiopia
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፤ መንግስት በሽብር የጠረጠረውን ማንኛውንም ሰው በቁጥጥር ስር እንደሚያደርግ አስታወቀ

አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በ48 ሰዓታት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ የተገለጸ ሲሆን ተፈጻሚ የሚሆነው ግን ከዛሬ ጀምሮ ነው፡፡ዝርዝሩን ለማንበብ፡-https://am.al-ain.com/article/government-says-any-individual-suspected-of-terror-should-be-arrested-without-arrest-warrant
ዝርዝር መረጃ !

ከዛሬ ጀምሮ በመላ አገሪቱ በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተከለከሉ ተግባራትና ግዴታዎች ከላይ በዝርዝር ተቀምጠዋል ያንብቡ።
Tikvah
4_5767119666585537235.pdf
685.6 KB
Directive on state of emergency
Attorney

Goh Betoch Bank S.C

Addis Ababa

JOB DETAILS: Attorney Job Requirement • Educational Level and work Experience: LLB in Law and 3 years’ of related work experience Place of Work: Head Office Education Requirement: No Requirements Work Hours: 8 Experience in Months: 36

Job application procedure
Application Deadline: November 06, 2021.
• Interested and qualified applicants fulfilling the above criteria can apply in person at Head Office Abedruf Plaza located around Bole Ruanda –Japan Embassy. Goh Betoch Bank S.C Human Capital Management Department Addis Ababa

ALE (Alternative Legal Education) All in one, for all.🔴አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/lawsocieties/
መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። ግዴታዎችንና መብቶችን ይወቁ።
Attorney I

Berhan Bank S.C

Addis Ababa

Job Description - Place of Work:- Head Office - Salary as per the Bank's Scale Job Requirements - LLB in Law - Two years relevant experience having Banking experience is more advantageous How to Apply - Qualified applicants are invited to submit their application letter, curriculum vitae and copy of non-returnable supporting documents only through mail to Berhan Bank S.C Human Resource Operations and Development Department P.O.BOX 387 CODE 1110.

Berhan Bank S.C

ALE (Alternative Legal Education) All in one, for all.🔴አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/lawsocieties/
መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። ግዴታዎችንና መብቶችን ይወቁ።
Forwarded from አለሕግAleHig ️
proclamation no. 1249.pdf
1.2 MB
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌዎች
፩. አጭር ርዕስ

ይህ አዋጅ “የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ
አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር
፩ሺ፪፻፵፱
/፪ሺ፲፫" ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
#ETHIOPIA

ማንኛውም የፀጥታ ችግር እንቅስቃሴ ሲመለከቱ ወይም ደግሞ ጥቆማ ለመስጠት ከፈለጉ ከላይ በተቀመጡት የስልክ መስመሮች ፈጥነው እንዲደውሉ የፌዴራል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።
#ሼር #Share
tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ተጨማሪ አዳዲስ የደንብ ልብሶችን ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ አሳውቋል።

ነባሩን የደንብ ልብስ መጠቀም ማቆሙን ተቋሙ ገልጿል፡፡

ከዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አዳዲሶቹ የደንብ አልባሳትን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ እና ነባሩ የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ መቀየሩ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ አሮጌውን የደንብ ልብስ ለብሶ የተገኘ አመራር እና አባል ላይ ጠንከር ያለ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል ተብሏል።

ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አሮጌው የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ በአዳዲሶቹ መቀየሩን ተገንዝበው አሮጌውን የደንብ ልብስ የለበሰ የፖሊስ አባል ሲያጋጥማቸው መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ፖሊስ ስራ ላይ ካዋላቸው አዳዲስ የደንብ አልባሳት ጋር ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደገገ ስለሆነ ከአ/አ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#Share #ሼር
tikvahethiopia