አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
New vacancy
Legal Officer
Berhan Insurance S.C

Addis Ababa (+1 other)

Apply


Job Requirement • Educational Qualification: LLB Degree from a recognized University or College • Experience: Minimum 2 years of relevant work experience Place of work: Addis Ababa How to Apply NB: Only short listed candidates will be communicated. Interested and qualified applicants may submit their application letter, curriculum vitae and other credentials in person or through the following addresses within 7 (seven) working days from the date of this announcement. Address: Berhan Insurance S.C. at Beklo Bet Yeshitam Building 4th floor, around Global Hotel near Garad Mall. P.O.Box 9266, Addis Ababa. Email: hr@berhaninsurance.com

Join..........

❤️Via Telegram channel❤️ https://t.me/lawsocieties
የሕግ የበላይነት እንዲከበር ዜጎች ለሕግ ተገዥ መሆን እንዳለባቸው ተገለጸ
__________________

የሕግ የበላይነትና የሕግ ተገዥነት በሚል ርዕስ እና ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በሚመለከት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የአራዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለክፍለ ከተማው የተለያዩ የህብረተስብ አባላት የንቃተ ህግ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ አቶ ሹመት ጌትነት ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት እንደተናገሩት ሕግ የሰው ልጆችን መብትና ግዴታዎች ዘርዝሮ የሚያቀርብ ሁሉንም ዜጎች ያለ ልዩነት የሚመራና የሚዳኝ እንደሆነ እና ሕጎች ሲወጡ ለረዥም ጊዜ ተብለው ቢሆንም ከህብረተሰቡ የኑሮ ሁኔታ ለውጦች ጋር ተያይዞ ሊሻሻሉ እንደሚችሉ ገልጸው የፍትሀ-ብሄርና ወንጀል ህጎችን በዝርዝር ለሰልጣኞቹ አብራርተዋል፡፡

ዐቃቤ ሕጉ በገለጻቸው ሕጎች አለም አቀፍና ብሄራዊ በሚል ተፈጻሚነት እንዳላቸው እና ማንም ሰው ከህግ በታችና በህግ ፊት እኩል በመሆኑ የተቀመጡ የህግ ስርዓቶችን ለማስፈን ስልጣን በመገደብና የስልጣን ክፍፍል እንዲኖር በማድረግ የህግ የበላይነት እንደሚረጋገጥ ገልጸዋል፡፡

የሕግ ተገዥነት የሚፈጸመው በተግባራችን ሕጉ የሚፈቅደውን ስናደርግ፣ ሕግ አክብረን መብታችን ማስከበር ስንችል የሌሎችን መብት ሳንገፋ ሕግ አስከባሪዎችን ማክበር ስንችል ነው ያሉት ዐቃቤ ሕጉ የሰዎች ተግባር ከሕጉ ጋር አለመገናኘትና አለመፈጸም የሕግ ተገዥ አለመሆን የሚያስከትል ስለሆነ መብትና ግዴታዎችን የሚያውቅ ዜጋ ለመፍጠር ስልጠናው አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ዐቃቤ ህግ አቶ ሳሙኤል ገዳሙ በአንድ ሀገር ላይ የዲሞክራሲ መገለጫ የሚሆነው ሰብዓዊ መብቶች ሲከበሩ በመሆኑ ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ህገ-መንግስቱ እንዲቆም ያደረጉ መሰረታዊ መብቶች ናቸው ብለዋል፡፡

አቶ ሳሙኤል አክለውም ሰብዓዊ መብቶች ሰዎች ሰው በመሆናቸው ያለ ልዩነት የሚሰጣቸው መብቶች መሆናቸውን እና ዲሞክራያዊ መብቶች ደግሞ ህዝቦች ያላቸውን ተሳትፎ የሚያሳዩበት እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሀገራችን ያሉ ህጎች መልካም ቢሆኑም ህብረተሰቡ ህጉን አውቆ ተጠያቂ እዲሆን የህግ አካላት ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
Jan 03, 2021
Manager, Legal Division
Zemen Insurance SC Addis Ababa, Ethiopia
FULL_TIME Insurance Jobs in Ethiopia Legal Jobs in Ethiopia
Job Description
Job Requirement
Education Qualifications: LLB in Law
Work Experience: 8.5 years of relevant work Experience
Place of work: Addis Ababa

How to Apply
Dead line for Application: 6 working days from the date of this Vacancy Announcement

Place of application: Zemen Insurance Share Company Bole Road, Alem Building second Floor.

Interested Applicants should apply in person, post office and email Address along with non-returnable updated CV and copies of relevant credentials from the date of this vacancy announcement until January 9/2021. Post office

Address: Zemen Insurance S.C.

PO.Box 23029 Addis Ababa, Ethiopia
ምንም እንኳን በወንጀል ባያስጠይቅም, የፍትሀቤር ክስ ለማንሳት ግን ከበቂ በላይ ነው. በምንም አይነት ሁኔታ ቢፈጠር, damage should be made irrespective of intention or fault. ከዚህ በዘለለ እንኳን በወንጀል ለመጠየቅ እንደማይችል የወንጀለኛ መቅጫ ህጉን አንቀጽ 57-59 እና አንቀጽ 23-24 በአንድነት በማንበብ በወንጀል ለመጠየቅ መሟላት ያለባቸው elements አለመሟላታቸውን ማወቅ ይቻላል. ይሁንና እንደመብት ጥሰት ለዚያውም ሰብኣዊ መብት ጥሰት በመቁጠር, ቢያንስ ከዚህ አስቀያሚ ድርጊቱ እንዲታቀብና ሌላ አይነስውር በትምኅርት ላይም ሆነ በስራ ላይ መሰል አጋጣሚ እንዳይገጥመው/ማት መንግስትን ልንሞግት ይገባል እላለው. ለዚህም እኛ ማየት የተሳነን ራሳችንን ለትግልና ለስኬት ማነሣሳት አለብን. የተቀራችሁት የማህበረሰቡ አካላትም ድጋፋችሁን እንሻለን.
Forwarded from Deleted Account
እንደ አንድ የሕግ ባለሙያ የወንድማችንን አብርሃም ዱሬሳ ጀግንነት የማደንቅለት ማየት የተሳነው አካል ጉዳተኛ ሆኖ ሳለ ብዙ ውጣ ውረ ዶችን ተጋፍጦ ሕግን የሚያክል ውስብስብ ትምህርት ተምሮ እዚህ ደረጃ መድረሱ ሲሆን ግን ይህን የኛን ጋወን ተረክብ በሰለጠነ የሕግ ችሎታ ፍትሕን ሊያስቀጥል ቢሮአችን በር ላይ በክብር የመጣውን ውድ እግዳችንን ስብዕና በጎደላቸው ግለሰቦች አተነዋል እጅግ ያስቆጫል..አንድ ማየት የተሳነው አካል ጉዳተኛ.ተንበርክኮ አልቅሶ ለመናቸው ..ከ ዚህ በላይ ምን ማድረግ ይችላል ..?ሥንት ዘመን ሙሉ በዳበሳ ተምሮ እዚህ የደረሰው ወንድማችን ፍቅር ና ፍትሕን አንድ ላይ ሲነፈግ ብቻውን ሲቀር እጅግ ደከመው በፍቅር ቃል ወቅሶንር ድካሙን፣ተስፋውን፣ልጆቹን ጥሎልን ሄደ....ይህን ያክል መጨካከኑ..ምን ትርፍ ያስገኛል..... ብዙዎች የሕግ ትንታኔ የመስጠት ብቃት አላቸው...ትልቁ ችግር ግን ፍትሕ የመ ሥጠት ጉዳይ ነው...አብርሃም ብቻ አይደለም የሕግ ምሁራንን የሚያሳትፍ በርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች አሉ..ግን መልስ የለውም..ለምሳሌ፦ እጅግ አሳዛኙ ብሔር ተኮር ጭፍጨፋዎች፤አባይ ወንዝ...በተመለከተ ችግኙን የተከለው የኢትዮጲያ ሕዝብ ውሃው ይገባናል የሚለው ግን ሌላው ክፍል...በተለይ ግብፅ..አንድ ችግኝ ተክላ የማታውቅ ሀገር ..ውሃው ህልውናችን ነው ሥትል ትንሽ አታፍርም...የሕግ ክፍሉ ምን ይላል ..እኛ ያስፈለገን አለም አቀፍ እውቅና ያለው በሀገር መብት ሽንጡን ገትሮ የሚከራከር የሕግ ማህበር አስፈልጎናል....የአብርሃም ጉዳይ ሀገራችንን ጭምር ሊያስተች እንደሚችል ማወቅ አለብን ...ጉዳዩ ኢትዮጲያን ለማስወቀስ ከፍተኛ የሚዲያ ሽፋን እየተሰጠው ነው.ወገን አንተ.የምክንያትና..የውጤት ግንኙነት እያክ በሃገሪቱ ሕግ ስትሟገት.."ኢትዬጲያ ለአካል ጉዳትኞች ትኩረት አትስጥም..." ለማስባል ና በዓለም ለማስተቸት አደገኛ አካሄድ እየተኬደ ነው ..ጉዳዩ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ትኩረት ካገኘ ተጎጂዎች ነን....ልጁ ሶስት ቀን በጥሩ ዲሲፒሊን ተፈትኗል፤ አራተኛው ቀን የተፈጠረው ክፍተት ልጁ ማየት የተሳነው አካል ጉዳተኛ መሆኑ ከግምት አስገብቶ እንዲገባ ማድረግ ሲቻል ጥረት አልተደረገም፤ በዛ ላይ አንድ አካል ጉዳተኛ ተንበርክኮ ሲለምንህ ቆሞ ማየትና ምላሽ አለመስጠት.. ክብር እንደሌለን ያሳያል...የሟች ሁኔታ ሲታይ ደግሞ የሕግ ባለሙያ..በደሉን ያስተናገደው በሕግ ክፍል..የሞተበት ሁኔታ ደግሞ ራሱን በእሳት አቃጥሎ...የምንተችበት አንዱና ትልቁ በር የሀገሪቱ የሕግ ክፍል እንኲን ለአካል ጉዳተኞች መብት እውቀት የለውም...በየትኛውም የዓለም ሀገር ላይ ያሉት አካል ጉዳተኞች እኩል መብት ነው ያላቸው...በአካል ጉዳተኝነት ዙሪያ....ዓለም ዓቀፍ እውቅናን ከሚያሳጡ ጉዳዮች አንዱ የአካል ጉዳተኞች መብት ጉዳይ ነው..ሌላው ዓለም ላይ ቢሆን አብርሃም በእንክብካቤ ጭምር ነበር ፈተናውን የሚወስደው ፈተናቸውም ለብቻው ነው ሚታረመው ..ምክንያቱም የአካል ጉዳተኞች አይምሮ በተደረገባቸው ጥናት ከፍተኛ የሆነ እንክብካቤ ና ፍቅር ይፈልጋል...ትንሽ ከነካኸው አደገኛ ውሳኔ ይወስናል..ለዚህም ነው ሁል ጊዜ ሞራላቸው ይጠበቃል..የተለየ እንክብካቤ ነው ሚደረግላቸው..ሁሌም ሚጠብቁት ቃል..አይዞህ በርታ ጎበዝ..ስራቸውን በትተደጋጋሚ ማድነቅ.. አለብህ..ፍቅር ማብዛት ግድ ይልሃል..ትንሽ ከተበሳጩ ውሳኔያቸው የመጨረሻው ደርጃ ነው..የእነሱ የአይምሮ ክፍላቸው መኖር የሚችለው በብዙ እንክብካቤ ብቻ ነው...።አብርሃም አንተንም ሆነ ጉዳዮቹን ሚያየው በጆሮው በሚስማው ድምፅ ና በእጆቹ እየዳበሰነው...ሞራሉን ሚነካ ድምፅ ከሰማ አይምሮውን እጅግ ያስጨንቀዋል.. ታዲያ ጭንቀታቸውን ለማምለጥ የሚወስኑት ውሳኔ አደገኛ.ነው።እናም ሁላችንም ለአካል ጉዳተኞች ፍቅር፣ሞራል ና ክብር ከጎናቸው ልንሆን ይገባል..የአብርሃም ውሳኔ ብዙ የአካል ጉዳተኞችን ጭንቀት ውስጥ ይከታል...ጥንቃቄ ማድረግ አለብን...ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል እንክብካቤ ና ፍቅር ካገኙ የማይታመን ድንቅ ችሎታ አላቸው..አስገራሚ ነገር ያሳዩሃል...እኔ በግሌ ለአካል ጉዳተኞች ልዩ ፍቅር አለኝ ..የተለየ ሚመስጥ ነገር አላቸው..እንቅረባቸው...እናክብራቸው..እንውደዳቸው...
Forwarded from Ni ጋቱ
Hello ! Ale families I hope u r doing very fine,
Share me notes on how to prepare effective term paper !....
regardingly ...thanks .
የ2013 ተመራቂ ተማሪወች‼️

ባለው ተጨባጭ ሁኔታ በሁሉም ዩንቨርስቲወች ወጥ የሆነ አሰራር ለማስፈን አዳጋች በመሆኑ:ነገሮች ተስተካክለው ወደ ቀድሞው የአሰራር ሂደት እስከሚመለስ ድረስ Research እና Apparent በሚመለከት ዩንቨርቲወች ያላቸውን ሁኔታ ከግምት በማስገባት በግል እንዲወስኑ የተተወ በመሆኑ ለዝርዝር ጉዳዬች ተማሪወች ከዩንቨርስቲያችሁ ጋር ተነጋገሩ:: አዲስ መረጃ ካለ የምናሳውቅ ይሆናል::

በኢትዮጵያ የህግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳት አኒሳ

Ethiopian law school students Union (ELSSU) president Anisa

@lawsocieties

https://t.me/lawsocieties
Forwarded from Deleted Account
ይህን ፔጅ መጠቀም ምፈልገው ለሕግ ና ለሕግ ዕውቀት ብቻ ነው..ብዙ ነገር ረድቶኛል...በጣም ጠቅሞኛል...አሁንም..ወደፊትም...የሕግ ጉዳዮችን በተሻለ መልክ ልንጠቀምበት የምንችልበት ትልቅ መድረክ ነው....አዘጋጅ ክፍሉን ሳላመሰግን አላልፍም... አዘጋጅ ክፍሉ ሰፋ ያሉ የሕግ ጉዳዮችን...ቢያቀርብልን..ይበልጥ ያምራል...ብዬ አምናለው....
Hello how are you doing every body currently there is on legal issue that becomes hot and some lawyers raise your stand here like wise as a lawyer i try to put my legal stand here first of all i wanna to say God put his soul in heaven next when i come to the legality of the act of supervisor i think the supervisor is not being liable under The FDRE criminal law b/c firstly there is no the direct casual relation ship b/n the acts of supervisor and Abriham death b/c the cause that makes Abriham suicide him self is his late from the exam mean if abriham arrive in the class exam on time he did not suicide him self there fore it is possible to say that the cause for the death of abriham is his lateness to arrive in the exam class then the supervisor is not criminally liable as long as there is no casual relation ship b/n the acts of the supervisor and Abriham secondly the supervisor is on the state of performing his duty according to the exam rule and regulation the examiner can not take the exam if they are not arrive in the exam class then Abriham did not arrive in the class exam that is decided by the pretiant body then the supervisor is not being liable under our criminal law thirdly ; to say a certian person is liable under criminal law the mental element of the criminal must be full filled mean the supervisor does not cause for the death of Abriham either intentionally or negligent illy Fourthly as i told before The supervisor is on the state of performing is state duty then according to art 68 of the criminal code he is not being liable fifthly all moral wrongs are not crime morally speaking it is shamfull prohibit Abriham to take the exam but legally speaking it is true prohibit him to take the exam as long as he did not arrive at the time which is decided by the pretiant body To sum up plc see all if you art 23,24,57-59,2,&68of the criminal code the thing what i wanna ask this group is some of you stands international law in which Ethiopia is signed there fore what international law make the supervisor being criminally liable. sorry plc enter the word not from being liable on the line 9
Thanks too
via Abebaw sisay Law🔴
የፌደራል_ዳኞች_የሥነ_ምግባርና_የዲስፕሊን_ክስ_ሥነ_ሥርዓት_ደንብ_ቁጥር_1_20013.pdf
1.8 MB
የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የዳኝነት ተጠያቂነት ስርዓት ወጥ እና አለም አቀፍ መስፈርትን ባሟላ መልኩ ለመዘርጋት ያስችል ከዚህ በፊት ያለውን ደንብ በማሻሻል ዝርዝር ይዘት ያለው የፌደራል ዳኞች የሥነ-ምግባርና የዲስፕሊን ክስ ሥነ-ሥርዓት ደንብ ቁጥር 1/20013 አጽድቆ ስራ ላይ እንዲውል አድርጓል፡፡ ውድ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ማህበረሰብ እና ተገልጋዮች ጉባዔው ያጸደቀውን ደንብ ለግንዘቤዎ በያሉበት ይድረሳችሁ ብለናል፡፡
https://t.me/lawsocieties
ከህግ መውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ የተከሰተውን
ችግር ትክክለኛ መረጃ የሚመለከታቸው አካላት በአስቸኳይ አጣርተው ለህዝብ ይፋ እንዲያደርጉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዘዘ

በምክር ቤቱ የሰው ሃብትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከሰሞኑ ከህግ መውጫ ፈተና ጋር በተገናኘ ህይወቱን ያጠፋውን አይነ ስውር የህግ ተማሪ አብርሃም ደሬሳ መነሻ ችግር ላይ የሚመለከታቸውን ጠርቶ ማብራሪያ ጠይቋል።

ችግሩ የፈተናዎች ኤጀንሲ የህግ መውጫ ፈተና ከሰጠባቸው አንዱ በሆነው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጊቢ ውስጥ የተከሰተ ነው።

አብርሃም ዱሬሳ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ትምህርት ቤት የመጀመሪያ ዲግሪውን እንዳገኘ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት የመውጫ ፈተና
በመውሰድ ላይ እንደነበር ተነግሯል።

የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ ፈተናውን በ2012 ዓ.ም ግንቦት ወር ላይ ለመስጠት ቢታቀድም በኮቪድ-19 ወረርሽኝና በተወሰኑ አካባቢዎች በነበረው የጸጥታ ችግር ሳይሰጥ
መቅረቱን አውስተዋል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደፈተና ጣቢያ ማገልገሉን ጠቅሰው ፤ ለአይነ ስውራን አንባቢ ማዘጋጀንት ጨምሮ ፈተናውን መስጠት የሚያስች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች መደረጉን ጨምረው ገልጸዋል።

ለተማሪ አብርሃምም ኤጀንሲው በተመደበው አንባቢ አማካኝነት ከታህሳስ 13 እስከ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የሚሰጠውን ፈተና የመጀመሪያዎቹን 3 ቀናት በሰላም መውሰዱን አብራርተዋል።

ይሁን እንጂ በፈተናው የመጨረሻ ቀን ፈተናው የሚጀመረው 3 ሰአት ቢሆንም አንባቢው ፈተናው ከተጀመረበት እስከ 45 ደቂቃ ድረስ ሊያገኘው እንዳልቻለ አስረድተዋል።

ከ45 ደቂቃ በኋላ አንባቢውን ማግኘቱንና በፈተና መመሪያ መሰረት አንድ ተማሪ ማርፈድ የሚችለው 30 ደቂቃ በመሆኑ ፈተናውን መቀመጥ አለመቻሉን
ገልጸዋል።

ተማሪው በወቅቱ የፈተና ጣቢያ ሃላፊንና ፈታኙን አግኝቶ ከጊቢው እንደወጣና ህይወቱን ማጥፋቱን በመገናኛ ብዙሃን እንደማንኛውም ሰው መስማታቸውን ዋና ዳሬክተሩ በማብራሪያቸው አንስተዋል።

ዋና ዳሬክተሩ ይህን ይበሉ እንጂ የኢትዮጵያ አይነ ስውራን ብሔራዊ ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ወሰን አለሙ ተማሪ አብርሃም ዩኒቨርሲቲ ጊቢ የደረሰው 3 ሰዓት መሆኑን ማህበሩ መረጃ እንዳለው ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ የፈተና ኮድ ባለመያዙ ምክንያት ወደ ቤቱ መመለሱንና የፈተና ኮድ ይሁን ወይንም መታወቂያ ግን መረጃ እንዳሌላቸው አስረድተው በ40 ደቂቃ ውስጥ መመለሱን ጨምረዋል።

በዚህ ጊዜ የተማሪው አይነ ስውርነት ከግምት ውስጥ ገብቶ ፈተናውን እንዲወስድ ማድረግ ይቻል እንደነበር ጠቅሰው፤ መመሪያ ካልፈቀደም ክፍተቱ
የመመሪያ መሆኑን ገልጸዋል።

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በፍትህ ማሻሻያ መርሃ ግብር ውስጥ ከታዩ ጉዳዮች አንዱ የህግ መውጫ ፈተና መሆኑን በሰጡት ማብራሪያ ጠቅሰዋል።

ተማሪ አብርሃም ዱሬሳ ፈተናውን የወሰደው ለሶስተኛ ጊዜ እንደሆነና ፈተናው በዚህ አመት የተሰጠው በ2012 ዓ.ም መፈተን ለነበረባቸው መደበኛና ከዚህ በፊት ባሉት አመታት ፈተናውን ማለፍ ላልቻሉ እንደ ተጨማሪ እድል ተሰጥቶ
መሆኑን አብራርተዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና በበኩላቸው በጉዳዩ ላይ ዩኒቨርሲቲው ያለአግባብ ስሙ ተነስቷል ሲሉ ቅሬታቸውን ተናግረዋል።

ፈተና በሚሰጥበት የዩኒቨርሲቲ ጥበቃዎች ተማሪውን እንዳይገባ አለመከልከላቸውን እንዳጣሩ ጠቅሰው፤ ይሁን እንጂ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን
ዩኒቨርሲቲው ጥፋተኛ እንደሆነ ተደርጎ መቅረቡ አግባብ አለመሆኑን ጨምረዋል።

ቋሚ ኮሚቴው የተሰጠውን ማብራሪያ መሰረት በማድረግ ትክክለኛውን መረጃ ለህዝብ ይፋ ለማድረግ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ኮሚቴ በማቋቋም በአስቸኳይ አጣርተው እንዲያቀርቡ ቋሚ ኮሚቴው አዝዟል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ተወካይ አቶ ማዘንጊያ እያቶ "ለችግሩ አንዱን ከሳሽ አንዱ ተከሳሽ ማድረግን ትቶ" በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መሪነት ጉዳዩን በማጣራት ለህዝብ ይፋ እንዲሆን አሳስበዋል።

በዚህም ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲና በአካል ጉዳተኞች ላይ ከሚሰሩ ማህበራት ኮሚቴ በማቋቋም በትክክል የተፈጠረውን ሪፖርት እንደሚያቀርቡ አስገንዝበዋል።

በማውቅም ይሁን ባለማወቅ ችግር የፈጠሩ አካላት ላይ አስተዳራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰድ እንዳለበትም ማስገንዘባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ከዚህ በመነሳት ለቀጣይ ትምህርት እንዲሆን አሰራሮችና አዋጆች መፈተሽ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

#ዳጉ_ጆርናል