#Suicide #Abrham_Duressa
ዛሬ የደረሰን መረጃ ልባችንን ሰብሮታል
ነገሩ እንዲህ ነው #አብርሃም_ዱሬሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል ነበር እናም ፈተናውን ማክሰኞ፣ረቡዕ እና ሀሙስ በሰላም ተፈትኖ የመጨረሻው የፈተና ዕለት ማለትም አርብ የመፈተኛ ኮዱን ረስቶ ወደ ስድስት ኪሎ FB ኮሌጅ ይሄዳል ካለ መፈተኛ ኮዱ መግባት ስለማይችል ወደ ቤቱ ሽሮ ሜዳ ተመልሶ የመፈተኛ ኮዱን ይዞ ሲመጣ የመፈተኛ ሰዓት አልፏል ይባላል ፤ ፈተናው 3፡30 የሚጀመር ሲሆን #አብርሃም ግን 3፡40 ይደርሳል። ሱፐርቫይዘሩ መግባት እንደማይችል ሲነግረው ስላረፈደበት ምክንያት ሊያስረዳ ይሞክራል ተማሪ #አብርሃም_ዱሬሳም በተለያየ መንገድ ይማፀናል #አይነ_ስውር መሆኑን ታሳቢ አድርገው እንዲተባበሩት ቢለምንም ፈተናውን እንዲወስድ ግን አልፈቀዱለትም ።
ፈተናውን መፈተን ባለመቻሉ ሲያለቅስ ፥ ሲበሳጭ ይውላል ምሽት ላይ ወደ ቤቱ በመግባት በራሱ ላይ የወሰደው እርምጃ ህይወቱን እንዳሳጣው የቻናላችን ቤተሰብ የሆነ የ#አብርሃም_ዱሬሳ ጓደኛ የነገረን ሲሆን ተማሪ #አብርሃም_ዱሬሳ ፈተናውን ባለመውሰዱ እጅግ ተበሳጭቶ ሲያለቅስ ይውልና ምሽት ላይ ቤቱን ዘግቶ በራሱ ላይ ጋዝ አርከፍክፎ ከፍተኛ ቃጠሎ እንደደረሰበትና በኋላም ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ተወስዶ ቃጠሎው ከፍተኛ ስለነበር ህይወቱ እንዳለፈ ከጓደኛው ሰምተናል።
📌ጉዳዩን ለማጣራት ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደውለን ነበር ተማሪው የመጨረሻውን ፈተና እንዳልወሰደና ሲያለቅስም እንደነበረ አረጋግጠውልን ከግቢ ውጭ ስለተፈጠረው ጉዳይ ግን መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።
📌ጉዳዩን ለማጣራት ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ለመደወል እየሞከርን ሲሆን ምላሻቸውን የምናሳውቅ ይሆናል።
#Suicide
🧿የተማሪ አብርሃም ዱሬሳ ጓደኛ ስለ ጉዳዩ ዝርዝር መረጃውን ነግሮናል ያድምጡ
📌ወንድማችን የላከልንን ፎቶ አስፈላጊ መስሎ ስላልተሰማን እኛው ጋር አስቀርተነዋል።
via Amharic tutorial class
ዛሬ የደረሰን መረጃ ልባችንን ሰብሮታል
ነገሩ እንዲህ ነው #አብርሃም_ዱሬሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት የመውጫ ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል ነበር እናም ፈተናውን ማክሰኞ፣ረቡዕ እና ሀሙስ በሰላም ተፈትኖ የመጨረሻው የፈተና ዕለት ማለትም አርብ የመፈተኛ ኮዱን ረስቶ ወደ ስድስት ኪሎ FB ኮሌጅ ይሄዳል ካለ መፈተኛ ኮዱ መግባት ስለማይችል ወደ ቤቱ ሽሮ ሜዳ ተመልሶ የመፈተኛ ኮዱን ይዞ ሲመጣ የመፈተኛ ሰዓት አልፏል ይባላል ፤ ፈተናው 3፡30 የሚጀመር ሲሆን #አብርሃም ግን 3፡40 ይደርሳል። ሱፐርቫይዘሩ መግባት እንደማይችል ሲነግረው ስላረፈደበት ምክንያት ሊያስረዳ ይሞክራል ተማሪ #አብርሃም_ዱሬሳም በተለያየ መንገድ ይማፀናል #አይነ_ስውር መሆኑን ታሳቢ አድርገው እንዲተባበሩት ቢለምንም ፈተናውን እንዲወስድ ግን አልፈቀዱለትም ።
ፈተናውን መፈተን ባለመቻሉ ሲያለቅስ ፥ ሲበሳጭ ይውላል ምሽት ላይ ወደ ቤቱ በመግባት በራሱ ላይ የወሰደው እርምጃ ህይወቱን እንዳሳጣው የቻናላችን ቤተሰብ የሆነ የ#አብርሃም_ዱሬሳ ጓደኛ የነገረን ሲሆን ተማሪ #አብርሃም_ዱሬሳ ፈተናውን ባለመውሰዱ እጅግ ተበሳጭቶ ሲያለቅስ ይውልና ምሽት ላይ ቤቱን ዘግቶ በራሱ ላይ ጋዝ አርከፍክፎ ከፍተኛ ቃጠሎ እንደደረሰበትና በኋላም ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ተወስዶ ቃጠሎው ከፍተኛ ስለነበር ህይወቱ እንዳለፈ ከጓደኛው ሰምተናል።
📌ጉዳዩን ለማጣራት ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደውለን ነበር ተማሪው የመጨረሻውን ፈተና እንዳልወሰደና ሲያለቅስም እንደነበረ አረጋግጠውልን ከግቢ ውጭ ስለተፈጠረው ጉዳይ ግን መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።
📌ጉዳዩን ለማጣራት ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ለመደወል እየሞከርን ሲሆን ምላሻቸውን የምናሳውቅ ይሆናል።
#Suicide
🧿የተማሪ አብርሃም ዱሬሳ ጓደኛ ስለ ጉዳዩ ዝርዝር መረጃውን ነግሮናል ያድምጡ
📌ወንድማችን የላከልንን ፎቶ አስፈላጊ መስሎ ስላልተሰማን እኛው ጋር አስቀርተነዋል።
via Amharic tutorial class