አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ (Baraki Belay)
Francis_Fukuyama_Identity_The_Demand_for_Dignity_and_the_Politics.pdf
1.9 MB
Description:
TheNew York Timesbestselling author ofThe Origins of Political Orderoffers a provocative examination of modern identity politics: its origins, its effects, and what it means for domestic and international affairs of state

In 2014, Francis Fukuyama wrote that American institutions were in decay, as the state was progressively captured by powerful interest groups. Two years later, his predictions were borne out by the rise to power of a series of political outsiders whose economic nationalism and authoritarian tendencies threatened to destabilize the entire international order. These populist nationalists seek direct charismatic connection to "the people," who are usually defined in narrow identity terms that offer an irresistible call to an in-group and exclude large parts of the population as a whole.
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ (Baraki Belay)
Criminal Procedure Code Draft.pdf
1.9 MB
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዐት እና የማስረጃ ሕግ
Forwarded from 🇪🇹የሕግ ጉዳይ (Baraki Belay)
Ethiopian_Criminal_Procedure_pdf.pdf
1.1 MB
CRIMINAL PROCEDURE LAW
PRINCIPLES, RULES AND PRACTICES
Simeneh Kiros Assefa
(LL. B., Addis Ababa University, 1998; LL. M., University of Pretoria, 2002; LL. M., Kyushu University, 2006; LL. M., University of San Francisco, 2008)
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ሺህ 700 በላይ መዝገቦች በእርቅ መቋረጣቸውን ገለጸ!

በደቡብ ክልል የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ2012 በጀት ዓመት ከ1 ሺህ 700 በላይ መዝገቦች በእርቅ መቋረጣቸውን ገልጿል፡፡የዞኑ ህዝብ ለባህላዊ የሙግት፣ ዕርቅ እና ይቅር ባይነት ያለው እምነት የፀና ነው ያሉት የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝደንት አቶ መኩሪያ ፈለሃ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 1 ሺህ 764 የወንጀልና የፍትሐብሔር ጉዳዮች በእረቅ እንዲቋረጡ መደረጉን አስታውቀዋል።

@BBC amharic
የዳኝነት ነፃነት ይበልጥ እውን እንዲሆን ከተፈለገ በኢትዮጵያ ውስጥ የሕግ ሞያ ነጻ መሆን አለበት። ነጻ ያልሆነ የሕግ ባለሞያ ዳኛ ሆኖ በነጻነት ለመሥራት ብዙ ፈተና ይገጥመዋል። ስለዚህ ሙያውን ነጻ የሆነ የሙያ ማህበር እንዲቆጣጠረው በሕግ በአዋጅ መብት ሊሰጠው ይገባል። ዳኞችም በዋናው የሕግ ባለሞያ ማሕበር ውስጥ የሚሳተፉበት ሁኔታ ሊመቻች ይገባል። የነጻ ሙያ ማህበር አባል ያልሆነ፣ በሙያው ሥነ ምግባር ደንብ ለመገዛት ግዴታ ገብቶ ያልፈረመ፣ ለሙያው ብቻ ተገዢ ለመሆን ቃል ኪዳን ያልገባ፣ ከሙያው በላይ ሌላ አለቃ ያለው ዳኛ የግል ስብዕና ጥንካሬ ከሌለው በስተቀር ለሙያው ተገዢ ለመሆን በጣም ፈተና ያጋጥመዋል። ለሁለት ጌታ መገዛት አይቻልም። ዳኛ መገዛት ያለበት ለሙያው ብቻ ነው። በሌላ አባባል ዳኛ ለሕግ ተገዢ መሆን የሚችለው ለሙያው ብቻ ተገዢ ሲሆን ነው። ይህ ይበልጥ እውን የሚሆነው ዳኛው የነጻ ሙያ ማህበር አባል ሲሆንና ነጻው የሙያ ማህበር የዳኛውን አሿሿም፣ ስነምግባር፣ መብት፣ ጥቅም እና ስንብት መቆጣጠር እና መከታተል ሲችል ብቻ ነው። ስለዚህ ፍርድ ቤቱ፣ ዳኞች፣ የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ፣ ጠበቆች፣ የሕግ ባለሞያዎች በሙሉ፣ መንግሥት፣ የፖለቲካ ድርጅቶች እና ህዝብ ለዚህ እውን መሆን ቢሠሩ ጥሩ ነው።
በታምራት ኪዳነማሪያም
@lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
የድምፅ ብክለት

(ከኪዳኔ መካሻ)

አንድ እለት ከአንድ ወዳጄ ጋር አመሻሹ ላይ ሜክሲኮ አካባቢ ስናልፍ ጎን ለጎን ሆነን መደማመጥ አቃተን። የታክሲ ረዳቶች ጥሪ፣ የመኪና ጥሩንባ፣ ለእንቶኔ ህክምና እርዳታ ስጡ ብሎ በትልቅ ድምፅ ማጉያ የሚማፀን ድምፅ፣ የዘማሪት አገሊት መዝሙር በሲዲ ግዙ የሚል ጆሮ የሚበጥስ ማስታወቂያ፣ የመንገድ ላይ እቃ ነጋዴዎች እና የሌሎችም የድምፅ ውርጅብኞች ከጆሮ አልፎ ልብን ያስጨንቃሉ።

ወዳጄ ከረብሻው ድምፅ እስክንርቅ እያጣደፈኝ ጥቂት ራቅ ካልን በኋላ
‘‘በዚህ አያያዛችን ከጥቂት አመታት በኋላ በከተማችን አዋጩ ሸቀጥ ፀጥታ ይሆናል፡፡ አይገኝም እንጂ በመሀል ከተማ ፀጥ ብለህ መንፈስህን የምታረጋጋበት ቦታ ከተገኘ ላለማበድ ስትል የተጠየከውን ትከፍላለህ።’’ አለኝ።
ትንሽ አጋነንከው ብለውም የከተማችን ድምፆች ጤና አጥተው ጤና እያሳጡን መምጣታቸው ላይ ግን የወዳጄን ሀሳብ ተጋርቻለሁ፡፡

ለመሆኑ የድምፅ ብክለትን ሀይ ባይ ሕግ የለም እንዴ?

መኖርስ አለ።ያው ሕጉን ባግባቡ የሚያስከብር ነው የጠፋው።

የድምፅ ብክለት ጤናማ ህይወት ለመምራት የሚስፈልገንን ጤናማ አካባቢ በመበከል ስነልቦናዊ እና አካላዊ ጤናችን እንዲጓደል ያደርጋል።
በሕገ መንግስታችን አንቀ 44 ላይ ጤናማና ንፁህ የሆነ አካባቢ ውስጥ የመኖር መብት አለን፡፡በአንቀጽ 92 ላይም መንግስት ጤናማና ንፁህ አካባቢ እንዲኖረን የአቅሙን ጥረት የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎበታል።
ሌሎች ለጉዳያቸው በሚያወጡት ድምፅ አካባቢያችን እንዳይበከል ከአካባቢው መራቅ ወይም የፀጥታ ያለህ ማለት ይጠበቅብንም በድምፅም አለመረበሽ ህገ መንግስታዊ መብታችን ነው፡፡

በ1952 ዓ.ም የወጣው የፍትሀ ብሔር ሕጋችን በቁጥር 1225 ላይ ማንኛውም ሰው ጎረቤቶቹችን እንዲያስብ አስጠንቅቋል፡፡በይዞታችሁና በንብረታችሁ ስተጠቀሙ ከመጠን አልፎ የጎረቤታችሁን ጥቅም እንዳይቀንስ ወይም እንዳይጎዳ አድርጉ ብሏል፡፡ በተለይ ጢስ፣ ጥላሸት፣ጎረቤት ሊታገሰው ከሚችለው በላይ ሽታ፣ ጩኸት ፣ንውፅታ ( የድምፅ ብክለት) ጎረቤት ላይ መፍጠር እንደማይቻል ደንግጓል፡፡

የአካባቢ ብክለት መቆጣጠሪያ አዋጅ ቁጥር 300/1995 ላይ አካባቢ በካይ ከሚባሉት ነገሮች መሀል ጤናን የሚጎዱና የሚያውኩ ድምፅና ንዝረቶችን ተካተዋል። በአንቀጽ 3 ላይ ማንም ሰው የተቀመጠውን የአካባቢ ጥበቃ ደረጃ በመተላለፍ በድምፅም ሆነ በሌሎች ነገሮች አካባቢን መበከል እንደማይችል ደንግጓል፡፡

የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ደግሞ የዓለም የጤና ድርጅት ባስቀመጠው መለኪያ መሰረት ከፍተኛውን የሚፈቀድ የድምፅ መጠን አስቀምጧል፡፡
ለመኖሪያ አካባቢ ማታ 55 ቀን 45 ዴሲብል፤
ለንግድ አካባቢ ማታ 65 ቀን 55 ዴሲብል፤ ለኢንዱስትሪ አካባቢ ምሽት 75 ቀን 70 ዴሲብል በላይ ድምፅ ማውጣት አካባቢን ይበክላል ብሏል።

ይህ መለኪያ ምን ያህል የድምፅ መጠን ነው? የሚለውን በፅሁፍ ለማሳየት ቢያስቸግርም፤ እንደየ አካባቢው አገልግሎትና ድምፅ እንደሚወጣበት ጊዜ ከተቀመጠው የድምፅ መጠን በላይ መጠቀም በድምፅ ያለመበከል መብታችንን መጣስ መሆኑንና ለድምፅም የተቀመጠ ገደብ መኖሩን ያሳያል፡፡የድምፁ መጠን በሕግ ከተፈቀደው በላይ መሆኑንም በዘርፉ እውቀቱ ያላቸው ባለሙያዎች ልኬቱን እንዲያካሂዱ በማድረግ ማስረዳት ይቻላል። እንደ ግለሰብ ግን በአንድ አካባቢ ላይ የሚሰማው ድምፅ ጤናማ ኑሮን ለመምራት በሚፈጥርብን መታወክ የድምፅ ብክለት እንዳለ ለማወቅ አይከብድም።

በማስታወቂያ ሰበብ የድምፅ ማጉያ መሳሪያ በመጠቀም ከተቀመጠው የድምፅ መጠን ገደብ በላይ ተጠቅሞ አካባቢን መበከልም በማስታወቂያ አዋጁ 759/2004 አንቀጽ 7(7) ላይ በሕገ ወጥ ተግባርነቱ ተከልክሏል፡፡

የድምፅ ብክለትን መፈፀም በአካባቢ ብክለት መቆጣጠሪያ አዋጁ አንቀጽ 16 ከ1ሺ - 10 ሺ ብር መቀጮ ወይም ከ1-10 አመት እስር ሊያስቀጣ እንደሚችልና ለጥፋቱ የዋለው ንብረት እደሚወረስ ብክለቱን ግለሰቡ /ተቋሙ/ እንዲያቆም ወይም ተገቢውን ካሳ እንዲክስ ፍ/ቤቶች ሊወሰኑ እንደሚችሉም ተደንግጓል፡፡
ከተፈቀደው ድምፅ በላይ በመጠቀም ማስታወቂያ ያስተዋወቀም በማስታወቂያ አዋጁ አንቀጽ 34(ሐ) መሠረት ከ20ሺ-150 ሺ ብር ቅጣት ይቀጣል፡፡

ከላይ የጠቀስኳቸው ሕጎች የወጡት ከመጠን ባለፈ ድምፅ እንዳንታወክ ጥበቃ ሊያረጉልን ነው። ሆኖም አንዳንድ ግለሰቦች፣የመንግስትና የግል ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማትና ሌሎችም እነዚህን ሕጎች ችላ በማለት በሚጠቀሟቸው ድምፆች አካባቢያችንን ሲያውኩ ይስተዋላል፡፡
የሚመለከታቸው የደንብ ማስከበርና የአስተዳደር አካላት ተገቢውን ግንዛቤ መፍጠር ይጠበቅባቸዋል። የድምፅ ብክለት የሚፈፅሙ ሰዎችንም የየአካባቢው ነዋሪዎች ለሕግ አካላት ጥቆማ መስጠት ሰላማዊና ጤነኛ የመኖሪያ አካባቢ እንዲፈጠር እገዛ ማድረግ አለባቸው።

መብትን ማስከበር መብትን ከማወቅ ይጀምራልና ፅሁፉን ለወዳጆቻችሁ አጋሩት። እነዚህ ሕጎችና ገደቦች እያሉ መረን በተለቀቀ ድምፅ መረበሽና መታወክ አለብን?
🎤 ❤️በምትችለው ሁሉ ለወከለህ ህዝብ መታገል ትልቅ ጀግንነት ነው‼️‼️
ሜክሲኮ ውስጥ ነው። አንድ የፓርላማ አባል ድንገት በጦፈ ክርህር ውስጥ ልብሱን አውልቆ በመጣል ለፓርላማ አባላቱ እንዲህ ሲል በስሜት ይናገራል። "የእኔ በዚህ ቦታ ራቁቴን መታየት ያሳፍራችሁ ይሆናል፤ ነገር ግን ገንዘባቸውና ሀብታቸው የዘረፋቹሁባቸው ዜጎች ጎዳና ላይ ራቁታቸው ሆነው፣ ተስፋን ቆርጠው፣ ስራ አጥ ሆነው ተርበዋል! እናንተ ግንሲል ለፓርላማው ተናግሯል፡፡ የኛዎቹስ ትግላቸው እስከምን ድረስ ነው.
የግል ክብር ከህዝብ አደራ ቃል አይበልጥም‼️‼️
@lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በችሎቶች እና ጉዳዮች ድልድል ላይ የተደረገ ማስተካከያ
********************************************
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 11 ችሎቶች አደራጅቶ በይግባኝና በሰበር የሚቀርቡለትን ጉዳዮች እየተመለከተ ውሳኔ ይሰጣል፡፡ እያንዳንዱ ችሎት የሚመለከታቸው የጉዳዮች ዓይነት ላይ መለስተኛ ማስተካከያ የተደረገ ሲሆን ዝርዝር መረጃው እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
በ1ኛ ሰበር ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከቤተሰብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከውርስ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከንግድና ሌሎች ማህበራት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከግብርና እና ከጉምሩክ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከላይ ከተመለከቱት ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ2ኛ ሰበር ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከጠቅላላ ውልና ልዩ ልዩ ውሎች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከውል ውጪ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከአሰሪና ሰራተኛ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከመንግስት ሰራተኛ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ለ1ኛ ሰበር ችሎት እና ለ3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ያልተደለደሉ ጉዳዮች፣
 ከላይ ከተመለከቱት ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ3ኛ ሰበር ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከንብረት ጋር የተያያዙ ክርክሮች (ቤት፣ተንቀሳቃሽ ንብረትና የከተማ ቦታ ይዞታ)፣
 ከእርሻ መሬት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች (ይዞታና ሁከት ይወገድ)፣
 ከወንጀል ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከጥብቅና ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከላይ ከተመለከቱት ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ1ኛ አጣሪ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከእርሻ መሬት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች (ይዘትና ሁከት ይወገድ)፣
 ከውል ውጪ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከንግድና ሌሎች ማህበራት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከአሰሪና ሰራተኛ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከመንግስት ሰራተኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከአፈጻጸም ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ለ2ኛ ሰበር አጣሪ ችሎት በግልጽ ያልተደለደሉ ጉዳዮች፣
 ከላይ ከተዘረዘሩት ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ2ኛ አጣሪ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 የወንጀል ጉዳዮች
 ከጠቅላላ ውልና ልዩ ልዩ ውሎች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከባንክና ኢንሹራንስ ውል ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከቤተሰብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከንብረት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከውርስ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከግብርና እና ጉሙሩክ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከላይ ከተዘረዘሩት ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
 ከይዞታ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ሁከት ይወገድ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
በ1ኛ ፍትሐብሔር ይግባኝ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከጠቅላላና ልዩ ልዩ ውሎች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከውል ውጪ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ለዚህ ችሎት ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ2ኛ ፍትሐብሔር ይግባኝ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከግንባታ ውል (ኮንስትራክሽን)ውል ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከንግድና ሌሎች ማህበራት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከአሰሪና ሰራተኛ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከመንግስት ሰራተኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከአፈጻጸም ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ለችሎቱ ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ3ኛ ፍትሐብሔር ይግባኝ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 ከውርስ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከቤተሰብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከግብርና እና ጉምሩክ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከስልጣን ይለይልኝ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣
 ከንብረት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች(ቤት፣ተንቀሳቃሽ ንብረት፣ከተማ ቦታ ይዞታ)
 ለ1ኛ እና ለ2ኛ ፍታሐብሔር ይግባኝ ሰሚ ችሎት በግልጽ ያልተደለደሉ ሌሎች ጉዳዮች፣
 ለችሎቱ ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
በ1ኛ ወንጀል ይግባኝ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 የሙስና ወንጀል(አዋጅ ቁጥር 881(2007)፣
 የእምነት ማጉደል ወንጀሎች፣
 የማታለል ወንጀሎች(ከአንቀጽ 692 እስከ 75 ድረስ የተመለከቱት)፣
 የኮምፒውተር ወንጀሎች(አዲሱ አዋጅ)፣
 በመንግስት የኢኮኖሚና የገንዘብ ጥቅሞች የሚደረጉ ወንጀሎች፣
 ከታክስና ከግብር ጋር የተያያዙ ወንጀሎች፣
 የጉምሩክ ወንጀሎች፣
 በታወቁ ገንዘቦች፣የግዴታ ወይም የዋስትና ሰነዶች፣ማህተሞች፣ቴምብሮች ወይም መሳሪያዎች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 በህዝብ ፀጥታና በማጓጓዣዎች ደህንነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 ለችሎቱ ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የዋስትናና ጊዜ ቀጠሮ ጉዳዮች፣
 ለችሎቱ ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮች፣
 ለ2ኛ ወንጀል ችሎት በግልጽ ያልተደለደሉ ሌሎች የወንጀል ጉዳዮች፣
 ለሁለቱም ችሎቶች የተደለደሉ ጉዳዮች ተቀላቅለው በአንድ ላይ የቀረቡ ጉዳዮች ይመለከታል፡፡
በ2ኛ ወንጀል ይግባኝ ችሎት የሚታዩ ጉዳዮች
 በመንግስት፣በአገርና በዓለም አቀፍ ጥቅሞች ላይ የሚደረጉ ወንጀሎች(ከወንጀል ህግ አንቀጽ 238 እስከ 283 ድረስ ያሉት)፣
 ሽብርን ለመከላከል የወጣ አዋጅ ድንጋጌዎችን በመተላለፍ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር፣
 በሰው ህይወት የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 በሰው አካልና ጤና ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 የሰውን ህይወት፣አካል ወይም ጤንነት ለአደጋ በማጋለጥ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 በሰው የግል ነጻነቶች የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 በክብር ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች(ስድብ፣ስም ማጥፋት)፣
 በመልክ ፀባይና በቤተዘመዳሞች የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 የውንብድና ወንጀሎች፣
 የስርቆት ወንጀሎች፣
 በፍትህ አስተዳደር ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣
 ለችሎቱ ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የዋስትናና ጊዜ ቀጠሮ ጉዳዮች፣
 ለችሎቱ ከተደለደሉ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ የማስፈቀጃ ጉዳዮችን ይመለከታሉ፡፡
ፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሬጂስትራር ጽ/ቤት
16/10/2020
Specialist, Policy and Aid Effectiveness

United Nations Development Programme (UNDP) UNDP, Addis Ababa, Ethiopia

FULL_TIME Economics Jobs in Ethiopia Management Jobs in Ethiopia NGO Jobs in Ethiopia United Nations / UN Jobs in Ethiopia
Job Description
Duties and Responsibilities
Summary of Key Functions:

Policy and technical advisory support to the DPG as well as Government of Ethiopia’s (GoE) Aid Effectiveness Task Force;
Advisory and Technical Support to Ministry of Finance (MoF);
Advisory Support for aid management and effectiveness portfolio;
Strengthen UNDP Senior Management’s understanding and support to aid effectiveness under the UN Delivering as One Reform in the context of DPG’s partnership and aid effectiveness agenda;
Contribute to UNDP’s work on aid coordination and effectiveness matters;
Contribute to aid effectiveness knowledge creation and management.

Duties and Responsibilities:

1. Policy and technical advisory support to DPG:

Provide advisory, analytical and technical support to DPG, including the Aid Effectiveness Taskforce, on issues related to aid coordination and effectiveness as well as to the strengthening of development partnership in Ethiopia;
Provide technical and analytical support to work relating to aid coordination, management and effectiveness, strategic partnerships and resource mobilization to strengthen UNDP’s coordination support function to DPG;
Provide technical and advisory support to DPG structures to facilitate effective policy dialogue on a number of overarching development policy issues through, among others, DPG dialogue meetings and discussions on issues of development aid issues as agreed upon with GoE;
In partnership with staff of the MoF, act as a member of the joint secretariat for the in-country dialogue structure. This includes advisory and technical support to the High Level Forum (HLF) Secretariat and Annual Progress Review (APR) meetings of the national development plan of Ethiopia.
Produce high quality and regular policy advisory briefs or papers on aid coordination, management and effectiveness to support national processes and development policy discourse in this area;
Provide technical support to OECD-DAC country-level activities, including coordination of in-country case studies, evaluations, and surveys among others;
Provide technical support to the Aid Effectiveness Task Force.

2. Advisory and Technical Support to MoF:

Advise MoF on the development and implementation of appropriate strategies and interventions for enhancing aid effectiveness and strengthening Government capacities for effective aid management;
Provide strategic advisory support to the MoF on the implementation and possible development of Ethiopia’s aid policy, including providing advice on the process and content in the development of an ODA manual, and strengthening and roll-out of the Aid Management Platform (AMP);
Provide professional technical advice to both GoE and DPG on the implementation of mechanisms and approaches aimed at promoting mutual accountability in aid relations;
Provide advisory support to the MoF to enhance its capacity and leadership in OECD-DAC related activities;
Procure and coordinate on behalf of DPG the provision of other technical support as needed.

3. Advisory Support for the Aid Management and Effectiveness Programme portfolio:

Provide advisory and management support on programme implementation with specific focus on aid coordination, harmonization, alignment and effectiveness;
As Policy and Aid Effectiveness Specialist for the DPG Secretariat, meet project oversight and management responsibilities for the strengthening of the DPG Secretariat project and manage day-to-day functions of the DPG Secretariat, including leading the work planning process.
Supervise staff reporting directly to the Policy and Aid Effectiveness Specialist;
Provide advisory support to the Aid Management and Effectiveness Programme portfolio.
4. Provide advisory support to UNDP Senior Management on aid effectiveness in the context of the UN Delivering as One reforms:

Analytical support the UN Resident Coordinator and UN Country Team in ensuring strategic engagement of DPG with the UN;
Assist with coordinating the contributions of UN agencies under Delivering as One to support the aid effectiveness agenda in Ethiopia.

5. Contribution to UNDP’s work on aid coordination and effectiveness matters:

Support UNDP’s capacity and positioning in terms of donor coordination and the aid effectiveness agenda;
Provide strategic advisory support to UNDP on aid effectiveness issues;
Deliver effective development partnership and incrementally higher levels of aid effectiveness for Ethiopia;
Foster higher levels of understanding and deeper knowledge among Development Partners; (including UN agencies) of the aid architecture in Ethiopia.

6. Contribution to aid effectiveness knowledge creation and management:

Regularly contribute to aid effectiveness knowledge platforms, including teamworks and communities of practice, by sharing best practices and results;
Generate and manage local aid effectiveness documents and actively support their publication and dissemination.

Competencies
Core Competencies:

Demonstrates integrity by modeling the UN’s values and ethical standards;
Displays cultural, gender, religion, race, nationality and age sensitivity and adaptability;
Treats all people fairly without favoritism;
Promotes ethics and integrity, creating organizational precedents;
Builds support and political acumen;
Builds staff competence, creating an environment of creativity and innovation;
Builds and promotes effective teams;
Creates and promotes an enabling environment for open communication;
Creates an emotionally intelligent organization;
Leverages conflict in the interests of setting standards;
Shares knowledge across the organization and builds a culture of knowledge sharing and learning;
Fair and transparent decision making; calculated risk-taking;
Prince2 training and certification, RMG.

Functional Competencies:

Advocacy/Advancing A Policy-Oriented Agenda:

Creates effective advocacy strategies;
Performs analysis of political situations and scenarios, and contributes to the formulation of institutional responses.

Results-Based Programme Development and Management:

Provides information for linkages across programme activities to help identify critical points of integration;
Provides information and documentation on specific stages of projects/programme implementation;
Provides background information to identify opportunities for project development and helps draft proposals;
Participates in the formulation of project proposals.

Building Strategic Partnerships:

Effectively networks with partners seizing opportunities to build strategic alliances relevant to strategic donor coordination agendas;
Identifies needs and interventions for capacity building of counterparts, clients and potential partners.

Innovation and Marketing New Approaches:

Seeks a broad range of perspectives in developing project proposals;
Identifies new approaches and promotes their use in other situations;
Creates an environment that fosters innovation and innovative thinking;
Makes the case for innovative ideas from the team with own supervisor.

Resource Mobilization:

Analyzes information on potential bilateral donors and national counterparts to recommend strategic approaches;
Identifies and compiles lessons learned;
Develops a resource mobilization strategy at the country level.

Promoting Organizational Learning and Knowledge Sharing:

Makes the case for innovative ideas documenting successes and building them into the design of new approaches;
Identifies new approaches and strategies that promote the use of tools and mechanisms.

Job Knowledge/Technical Expertise:
Understands more advanced aspects of primary area of specialization as well as the fundamental concepts of related disciplines;
Keeps abreast of new developments in area of professional discipline and job knowledge and seeks to develop him/herself professionally;
Demonstrates comprehensive knowledge of information technology and applies it in work assignments;
Demonstrates comprehensive understanding and knowledge of the current guidelines and project management tools and utilizes these regularly in work assignments.

Global Leadership and Advocacy:

Performs analysis of political situations and scenarios and contributes to the formulation of institutional responses;
Uses the opportunity to bring forward and disseminate materials for global advocacy work and adapts it for use at country level.

Client Orientation:

Anticipates client needs;
Works towards creating an enabling environment for a smooth relationship between the clients and service provider;
Demonstrates understanding of client’s perspective;
Solicits feedback on service provision and quality.

Required Skills and Experience
Education:

Master’s Degree or equivalent in International Development, International Relations, Public Administration, Economics, Political Sciences, Social Sciences or related field.

Experience:

A minimum of 7 years of relevant experience in development cooperation in governmental, multilateral or civil society organizations in a multicultural setting;
3 or more years of senior-level management responsibilities of similar size and complexity;
In-depth understanding of global developments and best practices in the area of aid effectiveness, combined with demonstrated experience in supporting aid coordination and management at the programme country level;
Prior work experience with UN agencies or other international organizations will be an asset;
Knowledge of the mandate and role of the UNDP in aid coordination and relevant experience in developing countries will be an asset.

Language Requirements:

Fluency in English is required. Fluency in additional UN languages (French, Spanish, Russian, Chinese) is desirable.

About United Nations Development Programme (UNDP)
Company Profile
Share this job: https://t.me/lawsocieties
የቤት ኪራይ ውል በኢትዮጵያ ህግ
___________

ሰላም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የፌስ-ቡክ ገጻችን ተከታታዮች ይህ የናንተን የህግ ግንዛቤ ለማሳደግ በየሳምንቱ አርብ የምናቀርብላችሁ የህግ ማብራሪያ ሲሆን በዛሬው ጽሁፋችን የቤት ኪራይ ውል በኢትዮጵያ ህግ በሚል ርዕስ ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያ አቅርበንላችኋል መልካም ንባብ!

የውል ምንነት፡-
------------
ዉል ምንድን ነዉ? ከሚለዉ ፅንሰ-ሀሳብ ስንነሳ “ዉል አንድን ግዴታ ወይም ከዚሁ ግዴታ ጋር የተያያዙ ሌሎች በርከት ያሉ ግዴታዎችን የሚያቋቁም ተግባርን የሚያመለክት አነጋገር ነዉ” በማለት ፕ/ር ጥላሁን ተሾመ ተርጉመውታል፡፡ በዚህ ግዴታ ባለገንዘብ የሆነዉ ወገን አንድ ነገር እንዲፈጸምለት የመጠየቅ መብት የሚኖረዉ ሲሆን ባለዕዳዉ ደግሞ አንድን ነገር የመፈጸም ግዴታ ይጠበቅበታል” በማለት አብራርተዉ ገልፀዉታል፡፡

እንዲሁም በፍ/ሕ/ቁ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡

የዉል አመሠራረት፡-
-------------
በፍ/ሕ/ቁ 1678 መሰረት በሕግ ፊት የሚፀና ውል የሚከተሉትን ማሟላት አለበት፡- ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል ጉድለት የሌለው ስምምነት መኖር፣ ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል፣ ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆን የገባዋል፣ የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ በህግ (ፎርም) ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጥ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም የማያስፈልግ መሆኑ፡፡

ከዚህ በላይ የተመለከትነዉ የዉል ትርጉም እና የዉል አመሰራረት ለሁሉም አይነት ዉሎች (የቤት ኪራይ ውል ጨምሮ) የሚያገለግል ደንብ ነዉ፡፡ ይህም የዉል ጠቅላላ ደንብ በመባል ይጠራል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ይህ ደንብ ለጠቅላላ ዉልም ይሁን ለልዩ ዉሎች የሚያገለግል ስለሆነ ነዉ፡፡

የቤት ኪራይ ዉል
----------
በህጋችን ላይ የቤት ኪራይ ዉል ትርጉም ባይሰጠዉም ከህጉ ድንጋጌዎች በመነሳት “አንድ የቤት ወይም ህንፃ ባለቤት ወይም ባለይዞታ የሆነ ሰዉ ቤቱን ወይም ህንፃዉን ሙሉ በሙሉ ወይም የተወሰኑ ክፍሎችን ወይም አንዱን ክፍል ለሌላ ሰዉ ከነዕቃዉ ወይም ባዶዉን የተወሰነ የኪራይ ዋጋ በመቀበል ለተወሰነ ጊዜ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ አስተላልፎ መስጠት /ማከራየት/” ማለት ነዉ በማለት በግርድፉ ትርጉም ሊሰጠዉ ይችላል፡፡ ነገር ግን የሆቴል ክፍልን ለተወሰነ ጊዜ ተከራይቶ መኖርን አያካትትም፡፡ (ፍ/ሕ/ቁ 2945)

የኪራዩ ክፍያ መጠን እና ጊዜ፡-
--------------
ተዋዋዮቹ ለፈለጉት ጊዜ ያህል በዉላቸዉ እንዲቆይ፣ በፈለጉት ዋጋ እና በተስማሙበት ጊዜ ክፍያዉ እንዲፈፀም በዉላቸዉ ዉስጥ ሊስማሙ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን በዉላቸዉ ዉስጥ እነዚህን ነገሮች ካልገለፁ በህጉ የተቀመጠው ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ በፍ/ሕ/ቁ 2950(2) ላይ ተዋዋይ ወገኖች በዉላቸዉ ዉስጥ የኪራዩን መጠን ካላስቀመጡ ወይም በሚያጠራጥር ጊዜ የማዘጋጃ ቤት ባለስልጣናት በወሰኑት ታሪፍ መሠረት ወይም የተወሰነ ታሪፍ ከሌለ የቦታዎቹን ልማድ በመከተል የሚወሰን መሆኑ ተደንግጓል፡፡ የዉሉን ቆይታ ጊዜ በተመለከተ ለተወሰነ ጊዜ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ሊሆን እንደሚችል በዚሁ ሕግ ተመላክቷል፡፡

የኪራዩ ዋጋ የሚከፈልበትን ጊዜ በተመለከተ በፍ/ሕ/ቁ 2951 ላይ ተዋዋይ ወገኖቹ በዉላቸዉ ዉስጥ ያልተስማሙበት ከሆነ፡- የቤት ኪራይ ዉሉ ለአንድ ወይም ለብዙ አመታት ተደርጎ እንደሆነ ኪራዩ በየሶስት ወሩ መጨረሻ የሚከፈል ይሆናል፡፡ የቤት ኪራይ ዉሉ በጣም አጭር ለሆነ ጊዜ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ተደርጎ እንደሆነ በየወሩ መጨረሻ ላይ የሚከፈል ይሆናል፡፡

የተከራዩትን ቤት ስለማደስ፡-
------------------
ተዋዋይ ወገኖች በቤት ኪራይ ዉሉ ዉስጥ የቤቱን እድሳት በተመለከተ ከተስማሙ በዉሉ መሰረት የቤቱ እድሳት ይፈፀማል፡፡ ነገር ግን ተዋዋዩቹ ስለ ቤቱ እድሳት በዉላቸዉ ላይ የገለፁት ነገር ከሌለ ማደስ ማለት የቤቱ መዝጊያዎችን ወይም መስኮቶችን፣ የቤቱን ወለሎችን ወይም ንጣፎችን፣ የዉሃ መስመሮችንና የፍሳሽ ማስወገጃዎችን ማደስ እና ቤቱን የማፅዳት እና በደንብ መያዝ መሆኑን በፍ/ሕ/ቁ 2954 ላይ ተደንግጓል፡፡ ተከራዩ ሊያድሳቸዉ የሚገባዉን የተከራያቸዉን ቤቶች በራሱ ኪሳራ ለማደስ ይገደዳል በማለት በፍ/ሕ/ቁ 2953 ላይ ተደንግጓል፡፡ ይህም ማለት ተከራዩ በኪራይ ዉሉ ዉስጥ ለማደስ በተስማማዉ መሰረት በራሱ ወጭ ለማድስ ይገደዳል ማለት ነዉ፡፡

የተከራዩትን ቤት ስለማከራየት፡-
-------------------
ሁለቱም ወገኖች ከተስማሙ የተከራየ ቤት ለሌላ ሰው መልሶ ሊከራይ ይችላል፡፡ ቢሆንም የቀድሞ ግዴታዎች ቀሪ አይሆኑም፡፡ (የፍ/ሕ/ቁ 2960)

የቤት ኪራይ ክፍያን በጊዜዉ አለመክፈል ዉጤት፡-
-------------------
ተከራይ የሆነዉ አካል የቤት ኪራይ ክፍያዉን በጊዜዉ ያልከፈለ እንደሆነ ወይም ሳይከፍል የቆየ እንደሆነ የሚያስከትለዉ ዉጤት በፍ/ሕ/ቁ 2952 ላይ ተቀምጧል፡፡ በዚሁ መሠረትም፡- ዉሉ ለአንድ ዓመት ወይም ከዛ ለበለጠ ጊዜ የተደረገ ከሆነ የሠላሳ ቀን ማስጠንቀቅያ፣ ለአጭር ጊዜ የተደረገ ከሆነ አከራዩ የአስራ አምስት ቀን ማስጠንቀቅያ በመስጠት፣ በዚህ ጊዜ ካልተከፈለ ዉሉን የሚያቆርጥ መሆኑን መንገር ይችላል፡፡

የቤት ኪራይ ዉል የሚፈርስባቸው ምክንያቶች፡-
-------------------
ተዋዋይ ወገኖች ያደረጉት የቤት ኪራይ ዉል በተለያየ ሁኔታ ሊቋረጥ ይችላል፡፡ እነዚህም፡- የቤት ኪራይ ዉሉ ጊዜዉ ሲያበቃ፣ ተዋዋይ ወገኖች በስምምነት ዉላቸዉን ለማቋረጥ ሲስማሙ፣ ተከራይ ኪራዩን በጊዜዉ ባለመክፈሉ አከራዩ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥቶት በዚህ ጊዜ ዉስጥ ሳይከፍል በመቅረቱ አከራዩ ዉሉን ካቋረጠዉ፣ አከራዩ ቤቱን ሲያድስ ለተከራዩና ለቤተሰቡ አስፈላጊ የሆነዉን መኖሪያ ሊጠቀምበት የማይችል ያደረገዉ እንደሆነ ተከራይ አከራዩን በመጠየቅ ውሉን ሲያፈርስ (ቁ. 2956/2/)፣ አከራይ ቤቱን ፈልጎት ለተከራይ ማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ወይም ተከራዩ ቤቱን መልቀቅ ፈልጎ ለአከራዩ ማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ሲያቋርጥ፡፡

ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ምክንኛቶች አንድ የቤት ኪራይ ዉል ሊቋረጥ ይችላል፡፡ ነገር ግን አከራይ ቤቱን ፈልጎት ለተከራይ ማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ሲያቋርጥ አከራዩ ሊሰጥ የሚገባዉ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ምንያክል መሆን አለበት የሚለዉ በህጉ መልስ አልተሰጠዉም፡፡ ይህ ጉዳይ በህብረተሰቡ ዉስጥም የተለያየ ዉዥንብር እና ጭቅጭቅ ሲፈጠር ይታያል፡፡ በፍትሐ ብሔር ጉዳያች ህግን ስንተረጉም ከምንከተላቸዉ መርሆች አንዱ ለተመሳሳይ ጉዳይ ተመሳሳይ ሁኔታን (አናሎጂ) በመጠቀም መተርጎም ይቻላል፡፡

በዚሁ መሰረትም አከራይ ቤቱን ፈልጎት ለተከራይ ማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ሲያቋርጥ አከራዩ ሊሰጥ የሚገባዉ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ተከራዩ ኪራዩን በጊዜዉ ባለመለክፈሉ አከራዩ በፍትሐ ብሔር ህግ ቁጥር 2952 መሠረት የሚሰጠዉ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ለዚህም
ተግባራዊ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህም ማለት፡- የቤት ኪራይ ዉሉ ለአንድ ዓመት ወይም ከዛ በላይ ጊዜ ተደርጎ እንደሆነ አከራዩ የሠላሳ ቀን ማስጠንቀቅያ በመስጠት፣ የቤት ኪራይ ዉሉ ለአጭር ጊዜ ተደርጎ እንደሆነ አከራዩ የአስራ አምስት ቀን
ማስጠንቀቅያ በመስጠት፣ ዉሉን ሊያቋርጥ ይችላል፡፡ ወሉ ላልተወሰነ ጊዜ የተደረገ ከሆነ ግን ሕጉም ስላልመለሰው ለክርክር ሊዳርግ እንደሚችል መገንዘብ ይቻላል፡፡
የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች በአምስት ተከፍለዋል፡

፩ የምርምር ዩኒቨርስቲዎች ፡

የአዲስ አበባ፣ አርባ ምንጭ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ ሀረማያ፣ ሀዋሳ፣ ጅማ እና መቀሌ

፪ የአፕላይድ ዩኒቨርስቲዎች፡

የአክሱም፣ አምቦ፣ አርሲ፣ አሶሳ፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ፣ ዲላ፣ ድሬዳዋ፣ ጅግጅጋ፣ ኮተቤ፣ ሰመራ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ወልቂጤ፣ ወለጋ እና ወሎ ዩኒቨርስቲ

፫ አጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች፡

አዲግራት፣ ቦንጋ፣ ቦረና፣ ቡሌ ሆራ፣ ደባርቅ፣ ደብረ ታቦር፣ ድምቢ ዶሎ፣ ጋምቤላ፣ እንጅባራ፣ ጂንካ፣ ቀብሪ ደሃር፣ መዳ ወላቡ፣ መቅደላ አምባ፣ መቱ፣ ሚዛን ቴፒ፣ ኦዳ ቡልቱም፣ ራያ፣ ሰላሌ፣ ዋቸሞ፣ ወራቤ እና ወልዲያ

፬ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች፡

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ

፭ ቴክኒካል ዩኒቨርስቲ ፡

የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና
https://t.me/lawsocieties