ከክስ በፊት እግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን በሚል የሚቀርብ አቤቱታ ተከሳሽ የሆነ ወገን ላይ ያልተገባ የመብት ገደብ እንዳይደረግበት ጊዚያዊ እግድ የሚጠይቀው ወገን ክስ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንደሆነና ለክስ ዝግጅቱም ተጨማሪ ጊዜ የሚያስፈልግበትን ምክንያት ማስረዳት የሚጠበቅበት ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ክሱ እስኪቀርብ ድረስ የዕግድ ትዕዛዙ ባይሰጥ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ማሳየትና ማረጋገጥ የሚጠበቅበት ሲሆን ፍርድ ቤቱም ክሱን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምክንያታዊ ጊዜ ብቻ በመወሰን የእግድ ትዕዛዝ ሊሰጥ የሚገባ ስለመሆኑ በሰ/መ/ቁ.191402 ቅፅ 25 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ተሰጥቶበታል።
💎💎💎💎💎💎✏️✏️✏️
አመልካች በሠበር አቤቱታው ለግልግል ጉባዔ የሚገቡንን ክፍያዎች በተመለከተ ክስ እስከምናቀርብ ድረስ ዋስትናዎች እንዳይከፈሉ ታግዶ እንዲቆይ ሊደረግ ይገባል ያለ በመሆኑ ለክርክሩ አወሳሰን ዋናው ጭብጥ ክስ ባልቀረበበት ሁኔታ የእግድ ጥያቄ ሊቀርብ ይችላልን? ዋስትናዎቹ ያለቅድመ ሁኔታ የሚከፈሉ መሆናቸው ሲታይ እግድ ሊሰጥባቸው ይችላል ወይስ አይችልም? የሚለውን መመርመር ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ 1ኛ ተጠሪ የሚከራከረው የእግድ ጥያቄ የሚቀርበው ዋና ክርክር ወይም ክስ ኖሮ ክርክሩ በፍርድ ቤት እስኪወሰን ድረስ ለጊዜው የሚሰጥ ትዕዛዝ ነው፡፡ ዋና ክርክር በሌለበት ገና ለገና ጉዳዩ በግልግል እስኪታይ ድረስ እግድ ይሰጥልኝ ብሎ ዳኝነት መጠየቅ በሕግ ያልተፈቀደ ነው በማለት ነው፡፡
የእግድ ትዕዛዝ በመርሕ ደረጃ የቀረበ ክስን መሠረት ያደረገ እና በሥነ-ሥርዓት ሕጉ አግባብ በተመለከቱት መስፈርቶች የሚሰጥ ነው፡፡ ዓላማው ደግሞ ክሱ ያለ ውጤት እንዳይቀርና ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜም የሚፈጸምበት ንብረት እንዲኖርና ዜጎች መብታቸውን ማስከበር የሚችሉበትን ዕድል የሚፈጥርና በሂደቱም ፍርድ ቤቶች ላይ ያላቸውን እምነት የሚጨምር ነው፡፡ በመሆኑም ሠዎች ክስ ከማቅረባቸው በፊት ነገር ግን በክስ ዝግጅት ላይ እያሉ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ጉዳዩን በመረዳት ክስ ሲቀርብ ክሱ ውጤት እንዳይኖረው በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 154(ለ) እንደተመለከተው ተግባሮችን እየፈጸመ ከሆነ፤ ተግባሩን አለመከላከል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የተቀረጸበትን ዓላማ እንዳይሳካ ያደርገዋል፡፡ ነገር ግን እግዱ እንዲሰጥ የተጠየቀው ክስ ሳይቀርብ ከሆነ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ላይ ያልተገባ የመብት ገደብ እንዳይደረግበት፤ ጊዜያዊ እግድ የሚጠይቀው ወገን ክስ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንዳለ፣ የክስ ዝግጅቱ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈለገበትን ምክንያት፣ ክሱ እስኪቀርብ ድረስ የእግድ ትዕዛዙ ባይሰጥ የሚያስከትለው ጉዳት ማሳየት ያለበት ሲሆን ፍርድ ቤቱም ክሱን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምክንያታዊ ጊዜ ድረስ ብቻ በጊዜ ገደብ የተገደበ የእግድ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ቁጥር #191402 #የሕግ_መረጃ #እግድ
💎💎💎💎💎💎✏️✏️✏️
አመልካች በሠበር አቤቱታው ለግልግል ጉባዔ የሚገቡንን ክፍያዎች በተመለከተ ክስ እስከምናቀርብ ድረስ ዋስትናዎች እንዳይከፈሉ ታግዶ እንዲቆይ ሊደረግ ይገባል ያለ በመሆኑ ለክርክሩ አወሳሰን ዋናው ጭብጥ ክስ ባልቀረበበት ሁኔታ የእግድ ጥያቄ ሊቀርብ ይችላልን? ዋስትናዎቹ ያለቅድመ ሁኔታ የሚከፈሉ መሆናቸው ሲታይ እግድ ሊሰጥባቸው ይችላል ወይስ አይችልም? የሚለውን መመርመር ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ 1ኛ ተጠሪ የሚከራከረው የእግድ ጥያቄ የሚቀርበው ዋና ክርክር ወይም ክስ ኖሮ ክርክሩ በፍርድ ቤት እስኪወሰን ድረስ ለጊዜው የሚሰጥ ትዕዛዝ ነው፡፡ ዋና ክርክር በሌለበት ገና ለገና ጉዳዩ በግልግል እስኪታይ ድረስ እግድ ይሰጥልኝ ብሎ ዳኝነት መጠየቅ በሕግ ያልተፈቀደ ነው በማለት ነው፡፡
እግድ በሠው የንብረት መብት አጠቃቀም ላይ ገደብ የሚፈጥር ነው፡፡ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(1) ላይ ጥበቃ የተደረገለት ንብረት መብት ላይ ገደብ ለማድረግ ደግሞ በሕግ በግልጽ በተመለከተ፣ ውስን ጉዳይና አፈጻጸሙም መብቱን መልሶ የመውሰድ ያህል ውጤት በማይፈጥር ሁኔታ ውስጥ ብቻ ሊሆን ይገባል የሚለው ስለሠብዓዊ መብት ጥበቃ የተደረጉ የሥምምነት ድንጋጌዎች ሆነ በሕገ-መንግሥቱ ውስጥ የተቀረጸ የሕግ መርሕ ነው፡፡ በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 151 መሠረት ከፍርድ በፊት ንብረት ተከብሮ እንዲቆይ (attachment) የሚደረግበትን ሥርዓትና ሁኔታ የሚመለከተው ሆነ በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 154 መሠረት ነገሩ በፍርድ እስኪወሰን ወይም ሌላ ትዕዛዝ እስኪሰጥ ድረስ ንብረቱ እንዳለ እንዲቆይ፣ ከመጥፋት እንዲድን ወይም እንዳይበላሽ፣ ለሌላ ሰዉ ተላልፎ እንዳይሰጥ፣ ወደ ሌላ ስፍራ እንዳይዛወር ወይም እንዳይባክን የእግድ ትዕዛዝ የተጠየቀው ለጥያቄው መሠረት የሆነው ክስ ቀርቦ ከሆነ እግድ መሰጠቱ የተከሳሹ ወገን የንብረት መበት አጠቃቀም ላይ የሚያስከትለውን ውጤት በመረዳት በጥንቃቄ መታየት ያለበት ነው፡፡
የእግድ ትዕዛዝ በመርሕ ደረጃ የቀረበ ክስን መሠረት ያደረገ እና በሥነ-ሥርዓት ሕጉ አግባብ በተመለከቱት መስፈርቶች የሚሰጥ ነው፡፡ ዓላማው ደግሞ ክሱ ያለ ውጤት እንዳይቀርና ፍርድ በሚሰጥበት ጊዜም የሚፈጸምበት ንብረት እንዲኖርና ዜጎች መብታቸውን ማስከበር የሚችሉበትን ዕድል የሚፈጥርና በሂደቱም ፍርድ ቤቶች ላይ ያላቸውን እምነት የሚጨምር ነው፡፡ በመሆኑም ሠዎች ክስ ከማቅረባቸው በፊት ነገር ግን በክስ ዝግጅት ላይ እያሉ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ጉዳዩን በመረዳት ክስ ሲቀርብ ክሱ ውጤት እንዳይኖረው በፍብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 154(ለ) እንደተመለከተው ተግባሮችን እየፈጸመ ከሆነ፤ ተግባሩን አለመከላከል ሥነ-ሥርዓት ሕጉ የተቀረጸበትን ዓላማ እንዳይሳካ ያደርገዋል፡፡ ነገር ግን እግዱ እንዲሰጥ የተጠየቀው ክስ ሳይቀርብ ከሆነ ተከሳሽ የሚሆነው ወገን ላይ ያልተገባ የመብት ገደብ እንዳይደረግበት፤ ጊዜያዊ እግድ የሚጠይቀው ወገን ክስ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንዳለ፣ የክስ ዝግጅቱ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈለገበትን ምክንያት፣ ክሱ እስኪቀርብ ድረስ የእግድ ትዕዛዙ ባይሰጥ የሚያስከትለው ጉዳት ማሳየት ያለበት ሲሆን ፍርድ ቤቱም ክሱን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ምክንያታዊ ጊዜ ድረስ ብቻ በጊዜ ገደብ የተገደበ የእግድ ትዕዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡
በሰ/መ/ቁ.191402 ቅፅ 25 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ተሰጥቶበታል።
Alternative legal enlightenment & Service
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
https://t.me/AleHig
#የሕግ_እውቀት alehig.com
#አለሕግ #ህግ #ሰበርመዝገብ #ቁጥር #191402 #የሕግ_መረጃ #እግድ
👍18❤8